30/05/2026
የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፣ከአብክመ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን እና ከባህር ዳር ከተማ መንግስታዊና የልማት ድርጅቶች ሹፌሮች አንድነት ማህበር ጋር በጋራ በመተባበር ለኮሚሽኑ ስትራቴጅክ አመራሮችና ሹፌሮች በትራንስፖርት ሚኒስትር የሚሻሻሉ ህጎች ረቂቅ እና የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የቴክኒክ ክህሎት ዙሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠ።
ግንቦት 22/2018 ዓ/ም የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን /ባህር ዳር /
በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ እንዳሉት ይህ ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ የተሰጠ መሆኑን አመላክተው አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር ከሁላችን የሚጠበቅ ተግባር ነው የትራፊክ ህጎችንና ደንቦችን በማክበር በትራንስፖርት ሚኒስተር የሚሻሻሉ ህጎች ረቂቅ እና የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የቴክኒክ ክህሎት ዙሪያ የሚሰጠው ስልጠና ለቀጣይ ለሚደረገው የብቃት ማረጋገጫ ምዘና የሚያግዝ ስልጠና መሆኑን አመላክተዋል ።ኮሚሽነሩ አክለውም ስልጠና የቀለም ትምህርት ብቻ አይደለም የማሽከርከር ብቃት የሚወሰነው ትግስትና የባህሪ ለውጥ ማምጣትና ቅድሚያ ለእግረኛ በመስጠት በሌሎች ብቃት ማነስ ችግር ሊደርስ የሚችል አደጋን በመከላከል የማሽከርከር ብቃት ነው ብለዋል። አያይዘውም የሚሰጠውን ስልጠና ወደ ተግባር መቀየር ከሁላችንም የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል ።
የስልጠና ሰነዱን ያቀረቡት የአብክመ የትራንፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን በመንገድ ደህንነት የስልጠናና የግንዛቤ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበበ አላምረው የመጀመሪያውን የመወያያ ሰነድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን ከቀረቡት መካከል የአሽከርካሪዎች ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለመደንገግ የወጣ አዋጅ 1074/2010 ዓ/ም የሚሻሻሉ ህጎች እረቂቅ አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር ስልት ምንነትና ተግባራት እንዲሁም ፣የተሽከርካሪ አይነቶችና ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች መመሪያ በተመለከተ በዝርዝር ለተሳታፊዎች አቅርበዋል ።
ሁለተኛውን የስልጠና ሰነድ ያቀረቡት የአብክመ የትራንፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን በመንገድ ደህንነት የስልጠናና የግንዛቤ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ሽበሽ የተሽከርካሪ አያየየዝና አጠቃቀም የቴክኒክ ክህሎት ምንነት ፣ የአሽከርካሪ ብቃት መመዘኛ መስፈርቶች ፣የተሽከርካሪ ጎማ ጥቅምና አያያዝ ፣አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር፣የፍጥነት ወሰን ገደቦችና መሰል ጉዳዮችን በተመከተ በዝርዝር ለተሳታፊዎች አቅርበዋል ።
የአማራ ክልል መንግታዊና የልማት ድርጅቶች ሹፌሮች አንድነት ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ እሱባለው አዱኛው ኮሚሽኑ በጀት በማመቻቸት ይህ ስልጠና በተሳካ ሁኔት እንዲሰጥ በማድረጉ በማህበሩ ስም አመስግነው ስልጠናውን ለወሰዱ የኮሚሽኑ አሽከርካሪዎች የምስክር ወረቀት ሰርተፍኬት ሰጥተዋል ።
በመጨረሻም በቀረቡት የመወያያ ሰነዶች ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች የቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ስልጠናውን በሰጡት ባለሙያዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል ።
ለዘገባው :- ከህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት