ANRS Prison Commission

ANRS Prison Commission Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ANRS Prison Commission, Government Organization, Bahir Dar.

ANRS Prison Commission is a Government Organization works with the federal prison commission under the mission to administer prisoners and make them skilled, patriotic and horned citizen.

የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፣ከአብክመ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን እና ከባህር ዳር ከተማ መንግስታዊና የልማት ድርጅቶች ሹፌሮች አንድነት ማህበር ጋር በጋራ በመተባበር ለኮሚሽ...
30/05/2026

የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፣ከአብክመ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን እና ከባህር ዳር ከተማ መንግስታዊና የልማት ድርጅቶች ሹፌሮች አንድነት ማህበር ጋር በጋራ በመተባበር ለኮሚሽኑ ስትራቴጅክ አመራሮችና ሹፌሮች በትራንስፖርት ሚኒስትር የሚሻሻሉ ህጎች ረቂቅ እና የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የቴክኒክ ክህሎት ዙሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠ።
ግንቦት 22/2018 ዓ/ም የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን /ባህር ዳር /
በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ እንዳሉት ይህ ስልጠና ለሁለተኛ ጊዜ የተሰጠ መሆኑን አመላክተው አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር ከሁላችን የሚጠበቅ ተግባር ነው የትራፊክ ህጎችንና ደንቦችን በማክበር በትራንስፖርት ሚኒስተር የሚሻሻሉ ህጎች ረቂቅ እና የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የቴክኒክ ክህሎት ዙሪያ የሚሰጠው ስልጠና ለቀጣይ ለሚደረገው የብቃት ማረጋገጫ ምዘና የሚያግዝ ስልጠና መሆኑን አመላክተዋል ።ኮሚሽነሩ አክለውም ስልጠና የቀለም ትምህርት ብቻ አይደለም የማሽከርከር ብቃት የሚወሰነው ትግስትና የባህሪ ለውጥ ማምጣትና ቅድሚያ ለእግረኛ በመስጠት በሌሎች ብቃት ማነስ ችግር ሊደርስ የሚችል አደጋን በመከላከል የማሽከርከር ብቃት ነው ብለዋል። አያይዘውም የሚሰጠውን ስልጠና ወደ ተግባር መቀየር ከሁላችንም የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል ።

የስልጠና ሰነዱን ያቀረቡት የአብክመ የትራንፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን በመንገድ ደህንነት የስልጠናና የግንዛቤ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበበ አላምረው የመጀመሪያውን የመወያያ ሰነድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን ከቀረቡት መካከል የአሽከርካሪዎች ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለመደንገግ የወጣ አዋጅ 1074/2010 ዓ/ም የሚሻሻሉ ህጎች እረቂቅ አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር ስልት ምንነትና ተግባራት እንዲሁም ፣የተሽከርካሪ አይነቶችና ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች መመሪያ በተመለከተ በዝርዝር ለተሳታፊዎች አቅርበዋል ።
ሁለተኛውን የስልጠና ሰነድ ያቀረቡት የአብክመ የትራንፖርትና ሎጀስቲክ ባለስልጣን በመንገድ ደህንነት የስልጠናና የግንዛቤ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ሽበሽ የተሽከርካሪ አያየየዝና አጠቃቀም የቴክኒክ ክህሎት ምንነት ፣ የአሽከርካሪ ብቃት መመዘኛ መስፈርቶች ፣የተሽከርካሪ ጎማ ጥቅምና አያያዝ ፣አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር፣የፍጥነት ወሰን ገደቦችና መሰል ጉዳዮችን በተመከተ በዝርዝር ለተሳታፊዎች አቅርበዋል ።

የአማራ ክልል መንግታዊና የልማት ድርጅቶች ሹፌሮች አንድነት ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ እሱባለው አዱኛው ኮሚሽኑ በጀት በማመቻቸት ይህ ስልጠና በተሳካ ሁኔት እንዲሰጥ በማድረጉ በማህበሩ ስም አመስግነው ስልጠናውን ለወሰዱ የኮሚሽኑ አሽከርካሪዎች የምስክር ወረቀት ሰርተፍኬት ሰጥተዋል ።
በመጨረሻም በቀረቡት የመወያያ ሰነዶች ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች የቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ስልጠናውን በሰጡት ባለሙያዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል ።

ለዘገባው :- ከህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ያቋቋመው የድጋፍ ቴክኒክ ኮሚቴ  ቡድን ከአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የማኔጅመንት አመራሮች ጋር  ውይይት አካሄደ ። ግንቦት 21/2018 ዓ/ም የአማራ ክልል ማ...
29/05/2026

የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ያቋቋመው የድጋፍ ቴክኒክ ኮሚቴ ቡድን ከአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የማኔጅመንት አመራሮች ጋር ውይይት አካሄደ ።
ግንቦት 21/2018 ዓ/ም የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን /ባህር ዳር /
የውይይት መድረኩን የመሩት የፍትህ ቢሮ አማካሪ የሆኑት
አቶ ዝጋለ ገበየሁ ይህ የድጋፍ ቴክኒክ ኮሚቴ ቡድን እና የኮሚሽኑ የማኔጅመንት አመራሮች ጋራ በመሆን የተቋም ተግባራትና አሰራሮችን በሚመለከት በቼክሊስት የተደገፈ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ የተገኘ መሆኑን አመላክተው ውይይት ከተደረገባቸው የውይይት ነጥቦች መካከል
የሰው ሀብት ልማትና ተቋማዊ ግንባታ አኳያ ፣ ተቋማዊ አደረጃጀትን በተመለከተ፣ አሰራሮችን መመሪያዎች ደንቦችን በማሻሻልና በማዘመን ፤ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ያለን ድርሻ ከፍትህ አካላት ጋር እየተደረገ ያለ እንቅስቃሴ ፣
የተቋሙን ጥበቃና ደህንነት ለማጠናከር ቴክኖሎጂን በመጠቀም ማረሚያ ቤትን ከማጠናከር አኳያ ያለው ሁኔታ ምን ድረስ ነው ፣ መሰረታዊ ፍላጎት ከማሟላት አኳያ በጤናው ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎችን በተመለከተ እና የሰብዓዊ መብት አያያዝን ለማስከበር የማረሚያ ቤቶቻችን ምን ቁመና ላይ ናቸው ፣የማረምና ማነፅ ተግባሮቻችን የህግ ታራሚዎች በስነ ምግባር ግንባታና ያላቸው የባህሪ ለውጥ በተመለከተ፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የቁልፍ ተግባራት ኪፒ አይ ስታንዳርዳችን ምን ድረስ ነው በሚሉ የቸክሊስት መመዘኛ ነጥቦችን ለውይይት ተሳታፊዎች በዝርዝር አቅርበዋል ።

የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለፁት የፍትህ ቢሮ ያቋቋመው የድጋፍ ቴክኒክ ኮሚቴ ቡድን አመራሮች ከኮሚሽኑ የመኔጅመንት አመራሮች ጋር በአካል በመገኘት ላደረጋችሁልን ድጋፍና ክትትል በተቋሙ ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። ኮሚሽነሩ አያይዘውም ዋና ዋና የተቋሙን ቁልፍ ዝርዝር ተግባራትን በሚመለከትና በቀጣይ ከፍትህ ቢሮ የሚጠበቁ ተግባራትን በዝርዝር አቅርበዋል ።
በመጨረሻም በቀጣይ መስተካከልና መጨመር ያለባቸውን ተግባራት ከኮሚሽኑ የማኔጅመንት አመራሮችና የፍትህ ቢሮ ያቋቋመው የድጋፍ ቴክኒክ ኮሚቴ ቡድን አመራሮች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ በፍት ቢሮ አማካሪ በሆኑት በአቶ ዝጋለ ገበየሁና በአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል ።
ለመረጃው :- ከህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

ቀን 17/9/2018 ዓ/ምየአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለኮሚሽኑ አመራሮች አባላትና ሲቪል ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አድሀ /አረ...
25/05/2026

ቀን 17/9/2018 ዓ/ም
የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለኮሚሽኑ አመራሮች አባላትና ሲቪል ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አድሀ /አረፋ/ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሲል ኮሚሽኑ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ።

🕌መልካም የአረፋ በዓል🕌
"የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን "

22/05/2026
በአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት የተዘጋጀ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ውይይት ተደረገ።የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ እና የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በተዘጋጀው ረቂቅ መተዳደሪያ ደ...
21/05/2026

በአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት የተዘጋጀ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ውይይት ተደረገ።

የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ እና የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በተዘጋጀው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ላይ አቶ ወንዳቸው ሠራው የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ፣ ምክትል ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም የሁለቱም ተቋማት የስራ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ረቂቅ መተዳደሪያ ደንቡ በአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ የህግ ምክር፣ማርቀቅ እና ማጠቃለል ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ ሲሆን በዳይሬክቶሬቱ ዐቃቤ ህግ አቶ ዮናታን ጠብቀው ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል።

ረቂቅ መተዳደሪያ ደንቡን ማዘጋጀት ያስፈለገበት ምክንያት፦
~ በየደረጃው የሚገኙትን የክልሉን ማረሚያ ቤቶች ፖሊስ አባላት ምልመላ፣ ሥልጠና፣ ቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ የደረጃ ዕድገትና ስንብት የሚወስን ክልል አቀፍ የመተዳደሪያ ደነብ አውጥቶ በሥራ ላይ ማዋል በማስፈለጉ፤

~ የማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት ሥራቸውን በታማኝነትና በኃላፊነት ስሜት ይፈጽሙ ዘንድ መብትና ግዴታቸውን በዝርዝርና በግልጽ ማስቀመጥ ለመልካም አስተዳደር ሥራዎች በእጅጉ አስፈላጊ በመሆኑና የሽልማት ማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት ከሥራ ውጤታማነት አኳያ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑ ስለታመነበት፤

~ በሥራ ላይ የቆየው የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ከመሻሻሉ የተነሳ አሁን በስራ ላይ ያለውን ደንብ ቁጥር 176/2010 ዓ/ም ይዘት ከዚሁ አዋጅ ድንጋጌዎች ጋር እንዲጣጣም ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
እንደሆነ በተዘጋጀው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ተገልጿል።

ከዚህ ባሻገርም ረቂቅ የመተዳደሪያ ደንቡ ዝርዝር ጉዳዮች በአቅራቢው ቀርበው የሚያጠናክሩ ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቷል።

በመጨረሻም የሚያጸድቀው አካል እንዲያጸድቀው መግባባት እና ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ዘገባው :- የፍትህ ቢሮ ነው ።
ለመረጃው :- ከህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

21/05/2026
20/05/2026
20/05/2026
20/05/2026

Address

Bahir Dar
6000

Telephone

+251582202608

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Prison Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share