22/08/2026
የታራሚዎችን አካላዊና ስነ _ልቦናዊ ጤና ለመጠበቅ ያለመ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተካሔደ።
ጎንደር :ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ታራሚዎች አምራች እና ጤናማ ዜጋ ሁነዉ እዲወጡ በተለያየዮ የስፖርት ዘርፎች አየተሣተፉ መሆኑን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ማረሚያ ቤት መምሪያ ሀላፊ ኮማደር ጀማል ሰይድ ገልጸዋል።
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ማረሚያ ቤት መምሪያ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ጃንተከል ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው ውድድር የህግ ታራሚዎች በዋነኛነት በእግር ኳስ እንዲሁም በመረብ ኳስ፣ቸዝ ፣ጠረጴዛ ቴንስ እና ዳርት ጨዋታዎች እንደየ ፍላጎት እና ችሎታቸው እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
ሀምሌ 2018 ዓ/ም የጀመረው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በታራሚዎች ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃትን እና ደስታ እንደፈጠረላቸው የነገሩን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ማረሚያ ቤት መምሪያ የህዝብ ማግኘት ባለሞያ ኢንስፔክተር አድና መለሰ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው የእርስ በርስ ግንኙነታቸውን ከማጠናከር ባለፈ ጤናማ ስነ _ልቦና እንዲኖራቸው ያግዛል ብለዋል።
ያነጋገርናቸው የህግ ታራሚዎች ስፖርታዊ ጨዋታዎች በመመቻቸታቸው ምስጋና አቅርበዋል።
ለመረጃው :- ከህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ዘገባው :- የአሚኮ ነው ።
የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
👉ፌስቡክANRS Prison Commission
👉ቴሌግራም-https://t.me/ AmharaPrisonOffice_12
👉ቲክቶክ- https://t.me/Getish_23
👉ዩቲዩብ-https:youtube.com/?si=5Qd6SdhCRmvgYkJ1