Bahirdar city prison Administration

Bahirdar city prison Administration Bahirdar City prison Administration

18/02/2022

✅ ሰው አፈር ነው አሉ - ታጥቦ የማይጠራ
እድፍ የሞላበት - ከጭቃ የተሰራ

✅ ሰው ሸክላ ነው አሉ - ድንገት ተሰባሪ
ወድቆ ለመነሳት - ምን ይሉኝን ፈሪ

✅ ሰው ህልም ነው አሉ - ታይቶ ማይጨበጥ
ኪዳኑን አፍርሶ - በሌላ ሚለውጥ

✅ ሰው ቅጠል ነው አሉ - ጠውላጊ ደራቂ
የሱን እልፍኝ ዘግቶ - የሰውን አድማቂ

✅ ሰው ዝንብ ነው አሉ - ከክፉም ከደጉ ከሁሉ አራፊ
መዘዝን ሰብሳቢ - በሽታን ጠላፊ

🌀 ሰው እሳት ነው አሉ -ለብልቦ ሚያቃጥል
በ አይን ተጋርፎ - በግልምጫ ሚጥል

🌀 ሰው ጊንጥ ነው አሉ - መርዛም ተናዳፊ
በምላሱ ልሶ - የሰውን ስም አጥፊ

🌀 ሰው ጅብ ነው አሉ - ሆዳም እራስ ወዳድ
አንዴ ካስቀመጡ - አላየንም ሲወርድ

🌀 ግና ሰው ብርቱ ነው አሉ - ስለ ሁሉ ታጋሽ
ተቀማጩ አይሰማው - ለ አምላኩ አልቃሽ


ሼርርርር

ለህልወና  ዘመቻው  የደም ልገሳ ፕሮግራም  በማረ/ቤት  ተካሔዷል።በባህር ዳር  ከተማ  አስተዳደር  ማረ/ቤት መምሪያ የሚገኙ  ሰራተኞች እና  የህግ  ታራሚዎች  አሽባሪውን  የህወሃት ወራሪ...
23/12/2021

ለህልወና ዘመቻው የደም ልገሳ ፕሮግራም በማረ/ቤት ተካሔዷል።

በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ የሚገኙ ሰራተኞች እና የህግ ታራሚዎች አሽባሪውን የህወሃት ወራሪ ሃይል በመደምሠስ ላይ ለሚገኘው ለወገን የፀጥታ ሃይል የደም ልገሳ አድርገዋል።

በደም ልገሳ ፕሮግራሙ ላይ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ውብሸት መኮነን ጨምሮ በእንግድነት የተገኙት የአማራ ክልል አቃቢያን ህግ እና የሲቪክ ማህበራት ጥምረት ሰብሳቢ አቶ አደራው አዲሱ በደም ልገሳ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ደማቸውን ለግሰዋል።
ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

ማረ/ቤቱ  ከህግ  ታራሚዎች  ጋር  ውይይት  አደረገ።የባህር  ዳር  ከተማ  አስተዳደር  ማረ/ቤት መምሪያ  በእርምት  ላይ  በማረ/ቤት ከሚገኙ  የህግ  ታራሚዎች  ጋር  በተለያዩ  ጉዳዮች...
07/12/2021

ማረ/ቤቱ ከህግ ታራሚዎች ጋር ውይይት አደረገ።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በእርምት ላይ በማረ/ቤት ከሚገኙ የህግ ታራሚዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ወይይት አድርጓል።

የስንቅ ዝግጅት   በባህር ዳር  ከተማ አስተዳደር  ማረ/ቤት  መምሪያ  እየተደረገ  ነው።በባህር  ዳር ከተማ አስተዳደር  ማረ/ቤት መምሪያ የሚገኙ መለዮ  ለባሽ  ፖሊስ አባላት  እና   ድ...
23/11/2021

የስንቅ ዝግጅት በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እየተደረገ ነው።

በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ የሚገኙ መለዮ ለባሽ ፖሊስ አባላት እና ድጋፍ ሰጪ ሲቪል ሠራተኛች ሃገርን ለማፍረስ የተነሳውን ሽብርተኛ ህወሃትን እየተፋለመ ለሚገኛው ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለልዩ ሃይሉና ለህዝባዊ ሠራዊት የድጋፍ ሥንቅ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት ።

በባህር  ዳር ከተማ  አስተዳደር  ማረ/ቤት  መምሪያ  የሚገኙ  የህግ  ታራሚዎች  በግብርና  የልማት ሥራ  ላይ  በተግባር  እየተሳተፉ  ይገኛሉ።
18/11/2021

በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ የሚገኙ የህግ ታራሚዎች በግብርና የልማት ሥራ ላይ በተግባር እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ማረ/ቤቱ  ከተቋሙ  መለዮ ለባሽ  ፖሊስ  አባላት  ጋር  ውይይት  አደረገ።የባህር  ዳር  ከተማ አስተዳደር  ማረ/ቤት  መምሪያ  ከተቋሙ  መለዮ  ለባሽ  ፖሊስ አባላት  ጋር  ውይይት  አ...
30/10/2021

ማረ/ቤቱ ከተቋሙ መለዮ ለባሽ ፖሊስ አባላት ጋር ውይይት አደረገ።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ ከተቋሙ መለዮ ለባሽ ፖሊስ አባላት ጋር ውይይት አድርጓል።

ከፖሊስ ሠራዊቱ ጋር ውይይት የተደረገውም :-

በመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አስጣጥ፣

የእርስ በርዕስ ግንኙነትና የፖሊስ አባላት ፖሊሳዊ ሥነ -ምግር ምን ይመስላል?

ህገ- ወጥ ድርጊትን መከላከልና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ሠፊ ውይይት ተደርጓል።

በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት አባላት በርካታ ሀሳቦችን አንስተዋል።ከተነሱ ሃሳቦች ህገ ወጥ ድርጊትን በምናድርገው መከላከል ለውጥ አለ ብለዋል።

አሁን ላይ እዚህ ግባ የሚባል የሚነሳ የመልካም አስተዳደር የለም ብለዋል የመድረኩ ተሳታፊዎች።

ያለን የእርስ በርዐስ ግንኙነትም በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል ነው ያሉት የፖሊስ አባላቱ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት።

አባላቱ በችግር ያነሱት ፣ በምን ሠራው ሥራ ላይ በሥምሪት ሠዓት የተሽከሪካሪ እጥረት እየገጠመን ሥለሆነ ቢታሰብበት ብለዋል።ከዚሁ ጋር አያይዘውም አባላቱ የሥራ ጫና እንዳለባቸው ገልፀዋል።

መድረኩን የመሩት የመምሪያው ሃላፊ ኮማንደር ውብሸት መኮነን ለአባላቱ እንደገለፁት፣ ሥራ ሥንሰራ በዲስፕሊን መመራትና መልካም ግንኙነትን መፍጠር ይገባናል ብለዋል።
መልካም የሆነ ፖሊሳዊ ሥነ ምግባር ሊኖር እንደሚገባ ኮ/ር ውብሸት ገልፀዋል።

አሁን ላይ ያለውን የተቋሙን ለውጥ ለማስቀጠል በመናበብና በመተሳሰብ መስራት ከተቻለ የተሻለ የተቋም ለውጥ እንደሚመጣ ኮ/ር ውብሸት ተናግረዋል።
በሠራ ነው ልክ፣ በአለን ውቀት ልክ ፣ በአልን የሥራ ልምድ ልክ ለምንሰጠው አገልግልትና ለምንሰራው ሥራ ውጤት ማስመዝገብ ከሁሉም ከተቋሙ ለመለዮ ለባሽ ፖሊስ አባላት ይጠበቃል ሲሉ ኮ/ር ውብሸት ገልፀዋል።
አልፎ አልፎ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችም በሂደት እየተቀረፉ እንደሚሔዱ ተገልጿል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት፣ 20/02/2014 ዓ/ም።

የአብክመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን  ኮሚሽነሮች  እና ከፍተኛ  የሥራ ሃላፊዎች በባህር ዳር  ከተማ አስተዳደር  ማረ/ቤት መምሪያ ተገኝተው  የሥራ ግምገማ አድርገዋል።የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ...
29/10/2021

የአብክመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነሮች እና ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ ተገኝተው የሥራ ግምገማ አድርገዋል።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ የማኔጅመንት አመራሮችም በመድረኩ ላይ አጠቃላይ የተቋሙን የሥራ እንቅስቃሴ በሪፖሪት መልክ አቅርበዋል።

በ18/02/2014 ዓ/ም ከአብክመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን ለሥራ ግምገማ የመጣው ቡድንም በዋነኛነት ትኩረት ያደረገባቸው አጀንዳዎችም:-

፨ በህግ ታራሚዎች ሠብዓዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ፣

፨ የህግ ታራሚዎች መሠረታዊ ፍላጎትና ጤና አገልግሎተ፣
፨ የጥበቃ ፣መረጃና ደህንነት ሥራዎችንበተመለከተ፣
፨ ማዕከላዊነትን የጠበቀ አመራር ሰጪነት ምን ይመስላል፣

፨ በተቋሙ ያለውን የመልካም አስተዳደርን በተመለከተ፣
፨ የሰው ሃብት አያያዝና አጠቃቀም ፣
፨ የውስጥ ገቢ አሰባሰብና የበጀት አጠቃቀም በሚሉ አጀዳዎች ላይ ሠፊ ወይይት ተደርጓል።

ለሥራ ግምገማ በተቋማችን የተገኙት የአብክመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን የሥራ ሃላፊዎችም የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በብዙ የሥራ ዘርፎች ለውጥ እያሳየ ያለ ተቋም ነው ብለዋል።

የአብክመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን የህግ ታራሚዎች የፍትህ አስተዳደር ዳይሬክትሬቶት የሆኑት ረዳት ኮሚሽነር አማረ ወርቁ እንደገለፁት በማረም ማነፅ ሥራዎች፣ የሠብዓዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ ፣የጥበቃ፣መረጃና ደህንነት ሥራዎች በተሻለ መልካ እተሠሩ ያሉ ሥራዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

በአብክመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን ፣በምክትል ኮሚሽነር ረዳት ኮሚሽነር የሆኑት ውቤ ውንዴ እንደገለፁት ማረ/ቤቱ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ገምግመናል ከአሉ በኃላ ፣በተጨባጭ በአይን የሚታዩ ሥራዎች አይተናል ሲሉ ተናግረዋል።
ረዳት ኮሚሸነር ውቤ ውንዴ እንደተናገሩት በጥበቃና ደህንነት ሥራዎች ላይ ህገ ወጥ ድርጊትን ለማስወገድ፣ባለ ብዙ ባህሪይ ችግር ያለባቸውን ታራሚዎችን አቻችሎ የመምራት እና የማረም ማነፅ ሥራዎች ተሠርተዋል ሲሉ ገልፀዋል።

ማረ/ቤቱ ታራሚዎችን ከማስተማርና ከማስልጠን አንፃር ተቋሙ ብዙ እደሎች አሉት ብለዋል ረዳት ኮሚሽነር ውቤ ወንዴ እንደገለፁት።

የተሻለ እወቀትና ክህሎት ያላቸውን ታራሚዎች በሥራ አሳታፊ በማድረግ በኩል ያለው ተግባርም መልካም እንደሆነ ተገልጿል።

በሌላ በኩል የአብከመ ማረ/ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ወንድማገኝ ወዳጄ በውይይት ማጠቃላያው ላይ እንደተናገሩት በተቋሙ ላይ በብዘርፍ ያለው ለውጥና እንቅስቃሴ በቀላል የመጣ አይደለም ፣ቅንጅታዊ አሰራር መኖሩን ያሳያል ብለዋል።
ኮሚሽነር ወንድማገኝ እንደዓሉት ዘርፈ ብዙ ለውጦች አሉ ቀጣይነት እንዲኖራቸው ማድረግ ይገባል በለዋል።

የሥራ ጉብኝት ቡድኑ መስተካከል ያለባቸው ነጥቦችንም አስቀምጧል:-
፨አልፎ አልፎ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ፣

፨የሰው ሃይል ፍሰትን እንዳይኖር የአቅም ግንባታ ሥራን በሰፊው መሥራት እንደሚገባ፣
፨በጀትን በአግባቡ መጠቀምና ቅሬታን መቀሰ እንደሚገባ፣
፨ዘላቂነት ያለው ለሥራ የሚያመች መልካም ግንኙነትን መፍጠር፣

፨በአመራር ሰጪነት ላይ ግልፀኝነት እንዲኖር አድረጎ መሥራት፣

፨መለዮ ለባሽ የፖሊስ አባላቱ ፖሊሳዊ ሙያና መልካም ሥነ ምግባር እንዲኖራቸው ተከታታይ የሆነ የግንባታ ሥራዎች መሠራት እንዳለባቸው በሚሉ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

ማረ/ቤቱ  ከህግ  ታራሚ  ተወካይ ኮሚቴዎች  ጋር  ወይይት  አደረገ።የባህር  ዳር  ከተማ  አስተዳደር  ማረ/ቤት  መምሪያ  የህግ  ታራሚዎችን ወክለው  ከተመረጡ  የታራሚ  ኮሚቴዎች ጋር ...
27/10/2021

ማረ/ቤቱ ከህግ ታራሚ ተወካይ ኮሚቴዎች ጋር ወይይት አደረገ።
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ የህግ ታራሚዎችን ወክለው ከተመረጡ የታራሚ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት አድርጓል።

የውይይቱ ዋናው ዓላማ የህግ ታራሚዎችን ወክለው የተመረጡ የኮሚቴ ታራሚዎች የሚሠሩትን የሥራ ተግባር መሠረት አድርጎ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል።

የወይይቱ አጀንዳዎችም:-

#የህግ ታራሚዎች ጠቅላይ ኮሚቴ አደረጃጀትና አሰራር፣
#የህግ ታራሚዎች የዞን አደራጃጀት ና አሰራር፣
# የህግ ታራሚዎች የሥነ-ሥርዓት ኮሚቴ አደራጃጀትና አሰራር፣
# አጠቃላይ የህግ ታራሚዎች የእርምት ሁኔታ እና የዲስፕሊን ምን ይመስላል በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ሠፊ ወይይት ተደርጓል።

የህግ ታራሚዎችን ወክለው የተገኙ የታራሚ ኮሚቴዎች የባህር ዳር ከተማ ማረ/ቤት በለውጥ ላይ ያለ ማረ/ ቤት ነው ሲሉ አስተያየታቸውን አስቀምጠዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ ኮሚቴዎች እንደተናገሩት በማረ/ቤቱ ውስጥ በህግ ታራሚዎች የሚቀርቡ መሠረታዊ ሸቀጣሸቀቶች ላይ የታራሚ ነጋዴዎች ዋጋን ያለ አግባብ እየጨመሩ ሥለሆነ ቁጥጥር ቢደረግ መልካም ነው ብለዋል።

ጠንክረው የሚሰሩ የታራሚ ኮሚቴዎች በተለያየ መልኩ መበረታታት እንደዓለባቸው በመድረኩ ላይ በኮሚቴዎች ተገልጿል።

የታራሚዎች ኮሚቴ በእቅድ መመራት እንዳለባቸውም በመድረኩ ተፀባርቋል።

በህግ ታራሚ ኮሚቴዎች የሚሠሩ ሥራዎች በየጊዜው በአጭር በአጭሩ መገምገም እንደሚገባም በመድረኩ ላይ በኮሚቴዎች ተነግሯል።

የህግ ታራሚዎች የማረምና ማነፅ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ግርማ ጥሩነህ እንደተናገሩት ከህግ ታራሚዎች ተወካይ ኮሚቴዎች ያለንን የውይይት ክፍተት እናርማለን ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ግርማ ጥሩነህ እንደተናገሩት ኮሚቴው ውጤታማ ሥራ እንዲሠራ የተሻለ የመሥሪያ ቢሮ እንዲኖር እናደርጋለን ሲሉ ተናግረዋል።

አጠቃላይ ከተቋም አንፃር የተነሱ ክፍተቶችን እየታረሙ እንደሚሔዱ መድረኩን በመሩ አመራሮች በኩል በማጠቃላያ መልስ ለታራሚ ክሚቴዎች ተገልጿል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት፣ 17/02/2014 ዓ/ም።

ማረ/ቤቱ  ከማረ/ቤት  ፖሊስ  አባላት  አመራሮች  ጋር  ውይይት  አደረገ።የባህር  ዳር  ከተማ  አስተዳደር  ማረ/ቤት  መምሪያ  የተቋሙ የማኔጅመንት  አመራሮች  ከጥበቃ ኦፊሠሮች  እስከ...
13/10/2021

ማረ/ቤቱ ከማረ/ቤት ፖሊስ አባላት አመራሮች ጋር ውይይት አደረገ።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ የተቋሙ የማኔጅመንት አመራሮች ከጥበቃ ኦፊሠሮች እስከ ቲም ድረስ ያሉ አመራሮችን በሥራ ተግበራ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ ላይ አመራሮቹ ከሚመሩዓቸው የፖሊስ አባላት ጋር መልካም ግንኙነትን በመፍጠር መሥራት እንደሚያስፈል ተገልጿል።

አመራሩ መለካት ያለበትም በሚሠራው የሥራ ልክ እንደሆነ ተነግሯል።

እያንዳንዱ ከጥበቃ ኦፊሠር እስከ ቲም መሪ ድረስ ያለው አመራር መልካም ግንኙነትን በመፍጠር ተቆራርጦ መሥራት እንደዓለባቸው በውይይት መድረኩ ላይ ተገልጿል።

አመራር ማለት እራሱ ሠርቶ የሚያሰራ እና ታግሎ የሚያታግል አመራር መሆን እንዳለበት ተነግሯል።

ህግና ሥርዓትን ተከትሎ የሚሠራ አመራር መፈጠር እንደአለበት በውይይት መድረኩ ላይ ተገልጿል።

መጥፎ ፖሊሳዊ ሥነ- ምግባርን መታገልና ማስተካከል እንደሚገባ የሰው ሃብት ልማት ሥራ አመራር የሆኑት ኮማንድር ፍርድ አወቅ እንዳለው በመድረኩ ላይ ለአመራሮቹ ገልፀዋል።

ኮማንድር ፍርደአወቅ እንደተናገሩት ከታች ያለውን አባል በአግባቡ ለመምራት አመራሩ በሁለመና ምሳሌ ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል ብለዋል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት፣ 03/02/2014 ዓ/ም

ማረ/ቤቱ  ከህግ ታራሚዎች  ጋር  ውይይት አደረገ።የባህር  ዳር  ከተማ  አስተዳደር  ማረ/ቤት   መምሪያ  በማረ/ቤት  በእርምት  ላይ  ከሚገኙ የህግ  ታራሚዎች  ጋር  በተለያዩ  ጉዳዮች...
13/10/2021

ማረ/ቤቱ ከህግ ታራሚዎች ጋር ውይይት አደረገ።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በማረ/ቤት በእርምት ላይ ከሚገኙ የህግ ታራሚዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል።

ከህግ ታራሚዎች ጋር ውይይት የተደረገባቸው አጀንዳዎችም:-

# በማረ/ቤቱ እየተሠጠ ሥለአለው የፍትህ አስተዳደር አገልግሎት በተመለከተ:፣
# በመሠረታዊ ፍላጎትና ጤና አገልግሎት ተደራሽነት፣

# በማረም ማነፅ ሥራዎች ዙሪያ፣
# በሠብዓዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ እና በአጠቃላይ በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከህግ ታራሚዎች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በውይይት መድረኩ ላይ ከተራሚዎች በተነሱ የተለያዩ ሃሳቦች ላይ በሚመለከታቸው በተቋሙ አመራሮች ምላሽ ተሠጥቷል።

በመድረኩ ላይ ታራሚዎች በእርምት ቆይታ ጊዚዓቸው ህግና ሥርዓትን አክብረው በመንቀሳቀስ መታረም እንደሚያስፈልግ በአወያዮች በኩል ተገልጿል።

መድረኩን የመሩት የመምሪያው ሃላፊ ኮማንድር ውብሸት መኮነን እንደተናገሩት የታራመ፣ የባህሪ ለወጥ ያሳየ እና ደንብና መምሪያ የሚፈቅደውን ያሟላ የህግ ታራሚ በአመክሮ፣ በይቅርታ የእንዲፈታ ተግተን እንሰራለን ሲሉ ለተራሚዎች ተናግረዋል።

የመምሪያው ኮማንደር ውብሽት በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት በማረ/ቤት በእርምት ላይ የሚገኝ ሰው ሁሉ በእኩል ይስተናገዳል ነው ያሉት በንግግራቸው እንደገለፁት።
የህግ ታራሚዎችን ወክለው የሚሠሩ የህግ ታራሚ ኮሚቴዎችም በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸው በመድረኩ ላይ ተገልጿል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት፣ 03/02/2014 ዓ/ም

እንኳን  ለብርሃነ  መስቀሉ  አደረሳችሁ።ለባህር  ዳር  ከተማ  አስተዳደር   ማረ/ቤት  መምሪያ   መለዮ  ለባሽ  ፖሊስ  አባላት እና  ድጋፍ  ሰጪ  ሲቪል  ሠራተኞች፣  እንዲሁም ለመላው...
26/09/2021

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ።

ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ መለዮ ለባሽ ፖሊስ አባላት እና ድጋፍ ሰጪ ሲቪል ሠራተኞች፣ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2014 ዓ/ም የመስቀል በዓል በሠላም አደረሳቸሁ ።

በዓሉ:- የሠላም ፣ የጤና፣ የአብሮነት ፣የመተሳሰብ በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል።

ሠላምና አንድነት ለአገራችን፣
አሸባሪው ህውሃት ይደመሠሳል; ኢትዮጵያ ታሸነፋለች።

መልካም በዓል

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ ።

Address

West
Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahirdar city prison Administration posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share