Amhara RoadTransport and Logistics Bureau

Amhara RoadTransport and Logistics Bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara RoadTransport and Logistics Bureau, Government Organization, Bahir Dar.

‎አንጎት የደገራ -የወረዳ -ወልማደግ 14 ነጥብ 5ኪሎ ሜትር መንገድ ከ17 ማሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት እየተጠገነ እንደሆነ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ መንገድ፣ትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ጽ/ቤት ...
28/05/2026

‎አንጎት የደገራ -የወረዳ -ወልማደግ 14 ነጥብ 5ኪሎ ሜትር መንገድ ከ17 ማሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት እየተጠገነ እንደሆነ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ መንገድ፣ትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ጽ/ቤት ገለፀ።

‎መንገዱ 5 ቀበሌዎችን የሚያገናኝ እና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መንገድ መሆኑን የገለፁት የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ ዳዊት መንበር እንደተናገሩት የመንገዱ መጠገን የማህበረሰቡን የልማት ጥያቄ የሚፈታ ነው ብለዋል።

‎የመንገድ ጥገናው በወረዳ በጀትና በህብረተሰብ ተሣትፎ የሚሰራ መንገድ እንደሆነ ሃላፊው አክለው ገልፀዋል።

‎በበጀት ዓመቱ በወረዳው ቀደም ብሎ ጥገና የጀመረውን ደምበጫ- የገሊላ -ዋዳን ቀበሌ አገናኝ መንገድ ጨምሮ አንጎት የደገራ-የወረዳ-ወልማደግ መንገድ ጥገና እየተካሄደ እንደሆነ አስረድተዋል።

‎አቶ ዳዊት አክለውም የመንገድ ጥገና ዘላቂነት እንዲኖረው ማህበረሰቡ በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቀውና ጥራቱን እንዲከታተል አሳስበዋል።

Dembecha zuria Communication

በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ የተገነባው የአጥዋ ወንዝ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል!*******በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ ጠንገጎ ቀበሌ የተገነባው የአጥዋ ወን...
27/05/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ የተገነባው የአጥዋ ወንዝ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል!
*******
በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ ጠንገጎ ቀበሌ የተገነባው የአጥዋ ወንዝ 22 ሜትር ኮንክሪት ድልድይ ሥራ ተጠናቆ በይፋ ተመርቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

ፕሮጀክቱ በክልሉ መንግስት በጀት ድጋፍ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎ የተገነባ ሲሆን፣ የአካባቢውን ቀበሌዎች ከማስተሳሰር ባሻገር ከሁለት በላይ አጎራባች ወረዳዎችን በማገናኘት ለህዝቡ የትራንስፖርት፣ የንግድ እና የማህበራዊ ትስስር አገልግሎት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል።

ድልድዩ በተለይ በክረምት ወቅት በወንዙ ምክንያት ይፈጠሩ የነበሩ የመንቀሳቀስ ችግሮችን በመቅረፍ የህዝቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዲቀላጠፍ ያግዛል ተብሏል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዞኑና የወረዳው አመራሮች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተው የድልድዩን ጠቀሜታ በማጉላት የርክክብ ሥነ-ሥርዓት አካሂደዋል። ድጋፍና ትብብር ላደረጉ የዞንና ወረዳ አስተዳደር አካላት፣ ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት ምስጋና ይገባል።

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ !በመጀመሪያ መላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆናችሁ የክልላችንና የሀገራችን ሕዝቦች፣ በተለይም በትራንስፖርትና ሎ...
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ !

በመጀመሪያ መላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆናችሁ የክልላችንና የሀገራችን ሕዝቦች፣ በተለይም በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ሌሊትና ቀኑን ሳትለዩ ሕዝባችሁንና ሀገራችሁን እያገለገላችሁ ለምትገኙ አሽከርካሪዎች፣ ረዳቶች፣ የዘርፉ ባለሀብቶችና ሠራተኞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል የእርስ በእርስ መተሳሰብን፣ መረዳዳትን፣ ፍቅርንና መስዋዕትነትን የምንማርበት ታላቅ መንፈሳዊ ዕለት ነው። ይህንን በዓል ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅና ካለን ላይ ለአቅመ ደካሞች በማካፈል ሊሆን ይገባል።
የማኅበረሰባችንን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴና የንግድ ፍሰት በላቀ ደረጃ ለማሳለጥ የትራንስፖርትና የሎጂስቲክስ ዘርፍ ሚና የማይተካ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ የበዓል ወቅትም ኅብረተሰቡ ወደ ፈለገበት ቦታ በሰላምና በደኅንነት እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ ዘርፉ ትልቅ ኃላፊነት አለበት፣ በመሆኑም፦
አሽከርካሪዎችና የዘርፉ ተዋናዮች፦ የበዓሉን ፍጹም ሰላማዊነት ለመጠበቅና የሰዎችን ሕይወት ለመታደግ በትራፊክ ሥርዓቱ ሕግና ደንብ መሠረት በጥንቃቄና በኃላፊነት ስሜት እንድታሽከረክሩ፤መላው የቢሮአችን ሠራተኞችና የዘርፉ ባለሙያዎች፦ ለተገልጋዩ ማኅበረሰብ የሚሰጡ አገልግሎቶች ሳይስተጓጎሉ በላቀ ዝግጁነትና ቅንነት እንድታገለግሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ይህ የደስታ፣ የበረከትና የሰላም በዓል ለክልላችንና ለሀገራችን ብልጽግና፣ ፍቅርና አንድነት ይበልጥ የሚጠናከርበት እንዲሆንልን ልባዊ ምኞቴን እገልጻለሁ።

ድጋሚ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ጋሻው አወቀ (ዶ/ር)
የአማራ ክልል መንገድ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊ

ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው  የመገናኛ ወንዝ ድልድይ ተመርቀ።******በሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው 60 ሜትር የመገናኛ...
26/05/2026

ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የመገናኛ ወንዝ ድልድይ ተመርቀ።
******
በሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው 60 ሜትር የመገናኛ ወንዝ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

ድልድዩ በአካባቢው ማህበረሰብ ለዘመናት ሲነሳ የቆየውን የመሠረተ ልማት ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የከተማዋን ትራንስፖርት፣ ንግድ፣ ማህበራዊ ትስስር፣ ኮሪደር ልማት እና የከተማውን ዋናጰመንገድ በእጅጉ የሚያሳልጥ ነው።

የድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቱ በክልሉ መንግስት እና በኢትዬጵያ መንገዶች አስተዳደር ትብብር የተከናወነ ሲሆን ግንባታውን የክልሉ የልማት ድርጅት ህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በፍጥነት እና ጥራት ተገንብቷል።

የአካባቢው አስተዳደርና ማህበረሰብ ለፕሮጀክቱ ያደረጉት ድጋፍ እና ትብብር የሚደነቅ ሲሆን ድልድዩ ለአገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት፣ መንገደኞች ደህንነትና ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።

ከ45 ሺህ ማህበረሰብ በላይ ተጠቃሚ የሚያደርገው የሽንፍ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ  ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገለጸ፤**********በገጠር ትስስር ለምግብ ዋሰትና ፕሮግራም በክልሉና...
25/05/2026

ከ45 ሺህ ማህበረሰብ በላይ ተጠቃሚ የሚያደርገው የሽንፍ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገለጸ፤
**********
በገጠር ትስስር ለምግብ ዋሰትና ፕሮግራም በክልሉና በወርልድ ባንክ በጀት ደጋፍ በመተማ ወረዳ የተገነባው የሸንፋ ውንዝ 120 ሜትር እግረኛ ተንጠልጣይ ድልድይ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ።

የምዕራብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አባይነህ ወረታ እንደገለፁት፤ 120 ሜትር ርዝመት ያለው ይህ ዘመናዊ ተንጠልጣይ ድልድይ በአብክመ መንገድ፣ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ እና በአለም ባንክ በተገኘ 23.8 ሚሊየን ብር ድጋፍ መገንባቱን ተናግረዋል።

ድልድዩ በቋራ ወረዳ የሚገኙትን በደላ፣ ኮዘራ፣ ወፍታ፣ ዳዛ እና ዛናአቦ ቀበሌዎች እና ከመተማ ወረዳ ጉባይ፣ ሌንጫ፣ ሻሽጌ፣ ሽንፍ እና ቱመተ ቀበሌዎች ጋር በቀጥታ የሚያስተሳስር ሲሆን፣ ከ45,000 በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።

ለዓመታት በክረምት ወቅት የሽንፍ ወንዝ የሰው ሕይወት ሲቀጥፍ፣ ንብረት ሲያወድም እና ማህበረሰቡን ከኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ሲያርቅ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን የተገነባው ዘመናዊ ድልድይ ይህን ችግር በመቅረፍ የህዝቡን የጉዞ፣ የንግድ፣ የጤናና የትምህርት ተደራሽነት በእጅጉ እንደሚያሻሽል አቶ አባይነህ አስረድተዋል።

አቶ አባይነህ አክለውም፣ ተንጠልጣይ ድልድዩ በርካታ ቀበሌዎችን በልማት፣ ንግድና ማህበራዊ ትስስር ለማገናኘት አዲስ ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል።

ድልድዩ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ያደረጉ የስራ ተቋራጮችና የቴክኒክ ባለሙያዎችን ጨምሮ ለጋሻው አየነውና ቡድናቸው አቶ አባይነህ ልዩ ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ (E-Mobility) ስትራቴጂና የትግበራ ማዕቀፍ በይፋ ተጀመረ***ኢትዮጵያ ወደ ዘላቂና አረንጓዴ የትራንስፖርት ሥርዓት ለመሸጋገር ያላትን ቁርጠኝነ...
25/05/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ (E-Mobility) ስትራቴጂና የትግበራ ማዕቀፍ በይፋ ተጀመረ
***
ኢትዮጵያ ወደ ዘላቂና አረንጓዴ የትራንስፖርት ሥርዓት ለመሸጋገር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ (E-Mobility) ስትራቴጂና የትግበራ ማዕቀፍ በይፋ ተጀምሯል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ፣ መንግሥት ዘመናዊ፣ አረንጓዴና የኢኮኖሚ እድገትን የሚደግፍ የትራንስፖርት ሥርዓት ለመገንባት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ልማት የካርቦን ልቀትን እና በነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል።

ሚኒስትሩ በተጨማሪም የኤሌክትሪፊኬሽን ሥራዎች በመላው የትራንስፖርት ሰንሰለት ውስጥ የተቀናጀ አሰራር እንዲኖራቸው አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም የተሽከርካሪ እና የአገልግሎት ዕቅድ፣ ሎጂስቲክስ፣ የቻርጅ መሠረተ ልማት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፣ የደህንነትና የመመዘኛ ሥርዓቶች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን እንደሚያካትት አስረድተዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ክቡር መላኩ አለበል በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሥርዓትን እንደሚደግፍ ገልጸዋል።

ስትራቴጂው የማምረቻ አካባቢ ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ ኢንቨስትመንት እና የስራ ዕድል ፍጠራን እንደሚያበረታታ ተናግረዋል።

የተጀመረው ስትራቴጂ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ለማስፋፋትና የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመን የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውስጡም፦
📌የቻርጅ መሠረተ ልማት ማስፋፋት፣
የተቀናጀ የሎጂስቲክስና የትራንስፖርት ሥርዓት ማበረታታት፣
📌የኤሌክትሪክ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ማስፋፋት፣
📌የደህንነትና የመመዘኛ ሥርዓቶችን ማጠናከር፣
📌የኃይል አቅርቦትና የታዳሽ ኃይል ቅንጅት፣
📌የአቅም ግንባታና የተቋማት ቅንጅት፣
📌በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ማምረትና አሰባሰብ ላይ ኢንቨስትመንት ማበረታታት፣
ንጹህ፣ ቀልጣፋና ለአካባቢ ተስማሚ የከተማ እንቅስቃሴን ማጎልበት ያካትታል።
ስትራቴጂው የኢትዮጵያን አረንጓዴ ኢኮኖሚ እድገትና የአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ልማት ራዕይ ለማሳካት የሚያግዝ ሲሆን፣ ኢትዮጵያንም በአፍሪካ የኤሌክትሪክ መኪኖች ትግበራ ቀዳሚ ሀገር እንድትሆን ያግዛል።
በስትራቴጂው ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ፣ ትስስር እና መሠረተ ልማት ልማት ዲቪዥን ዳይሬክተር ዶ/ር ሮበርት ሊሲንጌ፣ ክቡራን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታዎች አቶ በርኦ ሀሰን እና አቶ ደንጌ ቦሩ፣ እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት፣ ተባባሪ ድርጅቶች፣ ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

"የትራንስፖርት ቁጥጥሩ ለተጓዦች እፎይታን እያመጣ ነው" ተገልጋዮችባሕር ዳር: ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተው የነዳጅ ቀውስ በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ ባሳ...
25/05/2026

"የትራንስፖርት ቁጥጥሩ ለተጓዦች እፎይታን እያመጣ ነው" ተገልጋዮች

ባሕር ዳር: ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተው የነዳጅ ቀውስ በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ ባሳደረው ተጽዕኖ ማኅበረሰቡን ለእንግልት ሲዳርግ ተስተውሏል። ይህንን ችግር ለመቅረፍም የተለያዩ የመፍትሔ አማራጮች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ።

በባሕር ዳር ከተማ ጎጃም በር መናኸሪያ በነዳጅ እጥረት ሰበብ የነበረው የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች እጥረት እና ሕገ ወጥ የታሪፍ ጭማሪ በአሁኑ ሰዓት እየተቀረፈ መኾኑን ተገልጋዮች ነግረውናል ።

ተጓዦች ቀደም ሲል ከሦስት ቀን በላይ በመጉላላት ለአላስፈላጊ ተጨማሪ ወጭዎች ይዳረጉ እንደነበር ነው የገለጹት። አሁን ላይ በአንጻራዊነት መሻሻሉንም ተናግረዋል። ይህ አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ጠቁመዋል።

የአማራ ክልል መንገድ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ቢሮ የትራንስፖርት ኢንስፔክሽን ዳይሬክተር አበባው ታደሰ የነዳጅ አቅርቦቱ በመሻሻሉ የጉዞ ስምሪት የሚያገኙ ተሽከርካሪዎች ቁጥር ጨምሯል ብለዋል።

በዚህም ከፍተኛ የትራንስፖርት ክፍተት የነበረባቸው መስመሮች በአሁኑ ወቅት በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ነው ያሉት።

​የነዳጅ እጥረቱን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እና ትርፍ የሚጭኑ ሕገ ወጥ አሽከርካሪዎችን ለመቆጣጠር ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት ሕጋዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

የተጀመረው የተቀናጀ የቁጥጥር ተግባር በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

​ኅብረተሰቡም በጉዞ ወቅት ያልተገባ ሕገ ወጥ አሠራር በተመለከተ ጊዜ ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ
ጥሪ አቅርበዋል ።

አሚኮ

በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ከ180 ሚሊዬን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት የ24 ኪ .ሜ የመንገድ ግንባታ ተመረቀ!!******በክልሉ መንግስት በጀት በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ባ...
22/05/2026

በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ከ180 ሚሊዬን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት የ24 ኪ .ሜ የመንገድ ግንባታ ተመረቀ!!
******
በክልሉ መንግስት በጀት በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ባቲ ወረዳ የባቲ - ጋሪሮ - ኤላ መንገድ ፕሮጀክት 24 ኪ.ሜ መንገድ የ55 ሜትር የድልድይ ግንባታ ተጠናቆና ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉ ተገለፀ።

የመንገዱ ሙሉ ስራ በወረዳው የሚገኙ 8 ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ሲሆን ባቲ ከተማን፣ ባቲ ወረዳን እና፣ ኤላ ንኡስ ከተማን ያገናኛል፡፡

በአጠቃላይ የመንገድ ግንባታው በአብክመ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አማካኝነት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ መቻሉ የሚደነቅ ነው። የአካባቢው አስተዳደርና ህዝቡ በንቅናቄና በድምቀት አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉ የሚደነቅ ነው

#ኢትዮጵያንወደተምሳሌትሀገር
#የምርጫምልክትየስንዴነዶነው

#ብልፅግናፓርቲንይምረጡ

የጨዋ ወንዝ 111 ሜትር ርዝምት ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ ። *****በዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዝቋላ ወረዳ በክልሉ መንግስትና አለም ባንክ መቀናጆ በጀት አማካ...
20/05/2026

የጨዋ ወንዝ 111 ሜትር ርዝምት ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ ።
*****
በዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዝቋላ ወረዳ በክልሉ መንግስትና አለም ባንክ መቀናጆ በጀት አማካኝነት 11 ሚሊየን ብር በጀት በላይ የተሠራው ጨዋ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ ተመረቀ።

በዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በዝቋላ ወረዳ ደብረ ፀሀይ፣ ሀገረ ሰላም እና ሰሜን በር ከዝቋላ ወረዳ እንዲሁም ጽጽቃ ከተማ ጋር የሚያገናኝው ጨዋ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ በድምቀት ተመርቋል። ለአገልግሎትም ክፍት ተደርጓል።

የድልድዩ እርዝመት 110 ሜትር ሲሆን በዚህ ተንጠልጣይ ድልድይ የሚገለገሉ ቀበሌዎች 6 ሲሆኑ 04፣ 05፣ 06፣ 07፣ 08፣ 09 ቀበሌዎች መሆናቸውን አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

ግንቦት 12/1018 ዓ.ም

በጋዝጊብላ ወረዳ በ22 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመንገድ ድልድይ ተመረቀ።****** በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በጋዝጊብላ ወረዳ መንገድና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት በ021 መስቀሎ ቀበሌ ጉልሆ...
20/05/2026

በጋዝጊብላ ወረዳ በ22 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመንገድ ድልድይ ተመረቀ።
******
በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በጋዝጊብላ ወረዳ መንገድና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት በ021 መስቀሎ ቀበሌ ጉልሆ ወንዝ በ22 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመንገድ ድልድይ ተጠናቆ ተመርቋል።

የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጸጋው እሸቴ እንደገለጹት ፣መንገዱን የ3 ወር ውል ወስዶ የሰራው ኖህ ገጠር መንገድ ህብረት ስራ ማህበር ሲሆን መንገዱን በተሰጠው ጊዜና የስራ ጥራት ፈጽሞ አጠናቋል ብለዋል፡፡

መንግስት ለህዝብ የሚሰራቸውን መሰረተ ልማቶች ህብረተሰቡ ተረክቦ መንከባከብና መጠበቅ አለበት ብለው ይህ ድልድይ እንዲሰራ ድጋፍ ላደረጉ በጀቱን መድቦ እንዲገነባ ላደረገው የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ፣ ስራው በተቀመጠለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ላደረጉ ለብሄረሰብ አስተዳደር መንገድ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ መምሪያ; ለወረዳ አስተዳደር ምክር ቤትና መንገድና ሎጅስቲክስ ጽ/ቤት እና ለቀበሌው አመራርና ህዝብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል አቶ ጸጋዉ።

የጋዝጊብላ ወረዳ መንገድና ትራንስፖርት ኃላፊ እና ም/አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ አየለበበኩላቸዉ የኖህ ገጠር መንገድ ህ/ስራ ማህበር በተሰጠው ጊዜ አጠናቆ በማስረከብ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉን ምስጋና አቅርበዉ በቀጣይ የተገነባውን ድልድይ ህብረተሰቡ ተረክቦ እየጠገነ ደህንነቱን እየጠበቀ እንዲገለገል መልክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የኖህ ገጠር መንገድ ህ/ስራ ማህበር በተሰጠው ጊዜ አጠናቆ በማስረከብ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉን እና ከክልል እስከ ቀበሌ በበጀትም፣ በሀሳብም፣ በጉልበትም ላስተባበሩ ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ የተገነባውን ድልድይ ህብረተሰቡ ተረክቦ እየጠገነ ደህንነቱን እየጠበቀ እንዲገለገል መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

የኖህ ገጠር መንገድ ህ/ስ/ማህበር ሊቀመንበር አቶ እያሱ አማረ ይህን መንገድ በወሰድነው ውል መሰረት በጥራትና በጊዜ እንድንፈጽም ላደረጉ ከዞን እስከ ቀበሌ ላሉ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አበርክተዋል።

የ020 መስቀሎ ቀበሌ የልማቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብም የተገነባላቸውን የመንገድ ድልድይ አመስግነው በቀጣይም ሌሎች ወንዞችም በእቅድ ተይዞ እንዲሰራላቸውና የመንገድ ርክክቡንም በተሰጠን ተልእኮ መሰረት የምንጠብቅ፣ የምንከባከብና የምንጠብቅ ይሆናል ብለዋል።

በመጨረሻም በጎ አስተዋጾ ለነበራቸው ባለ ድርሻ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል ።

ጋዝጊብላ ወረዳ ኮሙኒኬሺን

Address

Bahir Dar

Opening Hours

Monday 02:30 - 23:30

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara RoadTransport and Logistics Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share