25/08/2026
በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረብርሃን ዞናል መናኸሪያ ውስጥ በሚገለገሉ ተጠቃሚዎች መካከል የሚፈጠረው የታሪፍ ልዩነት እንደ ተሽከርካሪዎች ደረጃና የተጠቃሚው ብዛት እንደሆነ ተገልጿል።
የመነሀሪያዉ የኢቲኬቲን ባለሙያዎች ሽፍት ማናጀር የሆኑት አቶ ያሬድ ወንድሙ እንደገለፁት በመነሀሪያ ዉስጥ ኢቲኬቲንግ ከተጀመረ ሁለት አመት እያስቆጠረ ነዉ።
የመነሀሪያዉ አገልግሎት አንዳንዴ ከፍተኛ የህዝብ እንቅስቃሴ ባለበት ወቅት እና አንደ ተሽከርካሪዉ ደረጃ የተወሰነ የመደበኛ ታሪፍ ክፍያ ልዩነት እንደሚኖር በመመሪያ የተፈቀደ አሰራር ስላለ ተጠቃሚ ሊረዳ ይገባል ብለዋል።
ነገር ግን አንዳንድ ተጠቃሚዎች ያለአግባብ ጭማሪ እንደተደረገባቸዉ ሲገልፁ ይታያሉ ፤ ይህን ለመረዳት ደግሞ ባግባቡ የሚጠይቁም መኖራቸዉን ገልፀዉ ኢቲኬቲንግ እያንዳንዱ ተሳፋሪ ባለሙያዎችን ጠይቆ በታሪፍ የተቀመጠውን ክፍያ ባግባቡ ከፍሎ ያለ ቅሬታ ወደ ሚፈለገው ቦታ እንዲንቀሳቀስ ከማድረጉ ባሻገር ለበርካታ ወጣቶችም የስራ እድል በመፍጠርም አስተዋፅዖ አድርጓል ሲሉ ገልፀዋል ።