ANRS Planning Institute

ANRS Planning Institute Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ANRS Planning Institute, Government Organization, Bahir Dar.

12/08/2026
12/08/2026
04/08/2026

የአማራ ክልል ፕላን ኢንስቲትዩት ከ130 በላይ ፕላኖችን አዘጋጅቶ ለከተሞች ማስረከብ ችሏል።

የአማራ ክልል ፕላን ኢንስቲትዩት በ2018 ዓ.ም የነበረውን የተቋም አፈጻጸም አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ምትኩ ዓለማየሁ (ዶ.ር) በሰጡት መግለጫ በበጀት ዓመቱ የፕላን ለውጦች ሲኖሩ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ መመሪያዎችን ማዘጋጀት መቻሉን ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ በክልሉ በአጠቃላይ 137 ፕላኖችን አዘጋጅቶ ለከተሞች ማስረከቡን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ ከተዘጋጁት መካከል ሦሥት መዋቅራዊ፣ ሰባት የስትራቴጂክ፣ 44 መሠረታዊ፣ 39 የገጠር ቀበሌ ማዕከላት፣ 41 የሰፈር ልማት ፕላኖች እና ሦሥት የከተማ ዲዛይኖች እንደሚገኙበት ገልጸዋል።

በፕላን ዝግጅት እና ዳታ ሥብሠባ ሂደት ከ14 ሺህ 900 በላይ የማኅበረሰብ አባላትን ማሳተፍ የተቻለ ሲሆኾን ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የመሬት ላይ መቆጣጠሪያ ነጥቦችም
ተሠርተዋል ነው ያሉት።

እስካሁንም 69 ከተሞች ፕላኑን በምክር ቤት አጽድቀው ወደ ሥራ የገቡ ሲኾን 131 ሺህ 697 የፕላን ስምምነቶች ተደርገዋልም ነው ያሉት።

በተጨማሪም የፕላን አተገባበርን ለመከታተል በ11 ከተሞች የኦዲት ክንውን የተካሄደ ሲኾን ፕላኑ በአግባቡ እንዲተገበር ለ50 ከተሞች የቁጥጥር እና የልምድ ድጋፍ ስለመደረጉም አስገንዝበዋል።

ተቋሙ በቀጣይ 130 የገጠር ቀበሌ ማዕከላት ስኬች ፕላንን ጨምሮ በአጠቃላይ 187 ፕላኖችን ለመሥራት ማቀዱን ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

🇪🇹



ዘጋቢ: ኪሩቤል ተሾመ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

ምትኩ አለማየሁ (ዶ/ር)በአብክመ የፕላን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርየፕላን ኢንስቲትዩት ለጠቅላላ ሠራተኞች በፕላን ዝግጅት፣ በሶሽዮ ኢኮኖሚና በመሠረታዊ ካርታ ዝግጅት ዙሪያ የአቅም ግንባታ ...
29/07/2026


ምትኩ አለማየሁ (ዶ/ር)
በአብክመ የፕላን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር

የፕላን ኢንስቲትዩት ለጠቅላላ ሠራተኞች በፕላን ዝግጅት፣ በሶሽዮ ኢኮኖሚና በመሠረታዊ ካርታ ዝግጅት ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና በባህር ዳር ከተማ እየሰጠ ይገኛል።

የፕላን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ምትኩ አለማየሁ እንደገለጹት በኢንስቲትዩቱ የሚዘጋጀው ፕላን ዓለምአቀፋዊ ስታንዳርዱን ጠብቆ በክልል ብቻ ሳይሆን በአገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ በመሆን የከተሞችንና የገጠር ቀበሌ ማዕከላት የዕድገት ደረጃቸዉን ከፍ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል::

የፕላንና የካርታ ዝግጅት ስራዎች የፕላን አዋጁን መሰረት በማድረግ የተዘጋጁ የሕግ ማዕቀፎችን ሙያተኞች በቂ ግንዛቤ በመያዝ በሁለም ዘርፍ ዉጤታማ ስራ በመስራት የከተሞችንና የገጠር ቀበሌ ማዕከላትን እንዲሁም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አለባቸው ያሉት ዶ/ር ምትኩ ለአሰራር ክፍተት የሚፈጥሩ ጉዳዮችን ከሙያተኞቹ ግብዓት በመዉሰድ ወጥ የሆነ አሰራር ለመፍጠር ያግዛል ብለዋል።

የፕላን ዝግጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብርሃም አለማየሁ በበኩላቸው እንደገለጹት የፕላን ዝግጅት ዋና ዓላማ ጤናማና ዘላቂ የከተማና የገጠር ማዕከላት ዕድገት እንዲኖር ማድረግ፣ የተረጋጋና የተመጣጠነ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት መፍጠር እና ሕዝብን ያሳተፈ የመሬት አጠቃቀም ሥርዓት ለመዘርጋት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የመሠረታዊ ካርታ ዝግጅት ባለሙያ አቶ አዲሱ አወቀ የካርታና የፕላን ዝግጅት ተግባራት መሠረታዊ ካርታዎችን በሳተላይት ኢሜጅና በመሬት ላይ ቅየሳ ማዘጋጀት፣ የከተማ መዋቅራዊ ፕላንና የስትራቴጂክ ፕላን ማዕቀፎችን መቅረጽ እንዲሁም ሕንፃዎችና የልማት ሥራዎች ከዕቅዱ ውጭ እንዳይከናወኑ መቆጣጠር ነው ብለዋል፡፡
የፕላንና የካርታ ዝግጅት እንዲሁም የሶሽዮ ኢኮኖሚ ሥራዎች በመሬት አጠቃቀም፣ በዕድገት አቅጣጫና በሕዝብ ተሳትፎ ላይ ተመስርቶ የከተሞችንና የገጠር ቀበሌ ማዕከላትን ልማት ለመምራት የሚያስችል ነው፡፡
በስልጠናው በቀረቡ ማንዋሎች በዝርዝር ቀርበዉ ሙያተኞችም በርካታ ሃሳቦችን አንስተዉ ዶ/ር ምትኩ ምላሽ የሰጡና የተነሱ ጉዳዮችን በማደራጀት ለግብዓትነት በመጠቀም ለአሰራር ምቹ ሁኔታ የሚፈጠር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ምትኩ አለማየሁ(ዶ/ር)በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተርየ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የማናበብ ስራ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር የፊርማ ሥነ ሥርዓት በባህር ዳር ከተማ በማከናወን ተጠና...
12/07/2026


ምትኩ አለማየሁ(ዶ/ር)
በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር

የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የማናበብ ስራ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር የፊርማ ሥነ ሥርዓት በባህር ዳር ከተማ በማከናወን ተጠናቀቀ፡፡
በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ምትኩ አለማየሁ በፊርማ ሥነ - ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት የፕላን ዝግጅትና ትግበራ ለተቋሙ ቁልፍ ተግባር በመሆኑ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሁሉም ተግባራት በተቀመጠላቸው ጊዜና በጥራት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አጽንኦት በመስጠት ገልጸዋል፡፡
የፕላን ኢንስቲቲዩትና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ በማጠናከር ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ የገለጹት ዶ/ር ምትኩ በቀጣይም ዋና ዋና ተግባራትን በማከናወን የደንበኞች እርካታ በተለይም ከተሞች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን እንዴት እንደሚመለከቱት የሚያሳይና እንደ ተቋም ያለንበትን ሁኔታ ሊያሳይ ስለሚችል ጠንክረው መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የኢንስቲቲዩቱ ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋሁን ተናኘ በበኩላቸው እንደገለጹት የድጋፍና ክትትል ስራውን የበለጠ በማጠናከር የተያዙ ስትራቴጅክ ዕቅዶችን በምን ሁኔታ እየተፈጸሙ መሆኑንና አሰራሮችን በማዘመን ጥራት ያለው ስራ በሁሉም ዘርፍ ማከናወን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የተቋሙ የአቅም ግንባታ ስራ በዝግጅት ምዕራፉ በመስጠት ሁሉንም ሙያተኛ ማብቃት ለተሻለ አፈጻጸም አወንታዊ ሚና አለው ያሉት ዶ/ር ተስፋሁን ከመቸውም ጊዜ በተሻለ ሁኔታ ወቅቱን የጠበቀ የዕቅድ ማናበብ ስራ መሰራቱ ተግባራትን በጥራትና በጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል ብለዋል፡፡

አንዳንድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃለፊዎች እንደገለጹት ተቋሙ በሁለት እግሩ እንዲቆም የኢንስቲቲዩቱ አመራሮች ቁርጠኝነት ላቅ ያለ መሆኑን የገለጹ ሲሆን የዕቅድ ማናበብ ሥራው በወቅቱ መሰጠቱ በፍጥነት ወደ ተግባር ለመግባት እንደሚያስችላቸው፣ የማናበብ ስራው የአቅም ግንባታና የልምድ ልውውጥ መድረክ ጭምር መሆኑ፣ ከዩንቨርስቲዎችና ከተቋማት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ያመላከተና ተቆጥሮ የተሰጠን ተግባር ቆጥሮ ለማስረከብ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡

   ምትኩ አለማየሁ(ዶ/ር)በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተርበአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የማናበብ ሥራ ከሐምሌ 03 ቀን 20...
10/07/2026


ምትኩ አለማየሁ(ዶ/ር)
በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር

በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የማናበብ ሥራ ከሐምሌ 03 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በባህር ዳር ከተማ ማካሄድ ጀመረ፡፡

በአማራ ክልል የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ምትኩ አለማየሁ(ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የ5 ዓመቱን ስትራቴጅክ ዕቅድ ታሳቢ ያደረግ ዕቅድ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር የማናበብ ስራና የፊርማ ሥነ ስርዓት የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በፕላን ዝግጅቱና ትግበራው የህብረተሰቡ ተሳትፎና የመረጃ አያያዝ ወሳኝ ነው ያሉት ዶ/ር ምትኩ ለዘላቂ ልማት ህብረተሰቡን ከገጠር ወደ ገጠር ማዕከላት ደረጃ በደረጃ ማስፈር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡
በ2019 በጀት ዓመት ኢንስቲቲዩቱ ስድስት ግቦች ላይ የትኩረት ማዕከል በማድረግ ይሰራል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ተቋማዊ የማስፈጸም አቅም መገንባት፣ ዘላቂ ልማትንና መዋቅራዊ ሽግግር ማከናወን፣ ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን ያሟሉ መሰረታዊ ካርታ ማዘጋጀት፣ ከፕላን ጋር የተያያዙ ሁለንተናዊ ምርምር ማካሄድ፣ በከተማ ፕላን ትግበራ የተቀመጡ የሕግ ማዕቀፎች መፈጸምና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ምትኩ አክለው እንደገለጹት የክረምትና የኢንሸቲቭ ስራዎችን በማስተሳሰር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማከናወን፣ ውዝፍ ተግባራትን ፈጥኖ ማጠናቀቅ፣ የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማካሄድ፣ ተሞክሮ ከተለያዩ አካባቢዎች መውሰድና መጠቀም፣ የበጎ አድራጎት ስራዎችን ማከናወን፣ በገጠር ኮሪደር ልማት ላይ የተቋሙን ሚና መወጣት እንዲሁም የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናና የዲጅታል መታወቂያ ስራዎችን ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡

ምትኩ አለማየሁ (ዶ/ር)በአማራ ክልል የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተርበአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ አረንቴሽን...
08/07/2026


ምትኩ አለማየሁ (ዶ/ር)
በአማራ ክልል የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር
በአብክመ የፕላን ኢንስቲቲዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ አረንቴሽን የውይይት መድረክ ከጠቅላላ ሠራተኞች ጋር በባህር ዳር ከተማ አካሄዷል፡፡
የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ምትኩ አለማየሁ እንደገለጹት የኘላን ሥራ የገጠርና ከተማ እንዲሁም የከተማና ከተማ ትስስርን በማጠናከር ዘላቂ ልማት በማረጋገጥ ወሳኝና መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ፕላን የአንድን አካባቢ የወደፊት ዕድገት የህዝብን ጥቅም መሰረት አድርጎ የሚዘጋጅ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ምትኩ በ2018 በጀት ዓመት ስልጣንና ተግባሩን ለማስፈጸም ሁለት መመሪያዎች የተዘጋጁ ሲሆን የፕላን ምደባ ለውጥና የፕላን ማስተካከያ መመሪያ የጸደቀና የፕላን ዝግጅት ወጪ መሸፈኛ መመሪያ ተጠናቆ ለክልል መስተዳደር ካቢኔ ለማስጸደቅ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር ሶስት ማኑዋሎች ማለትም የፊዚካል ፕላን ዝግጀት ስታንዳርድ ማኑዋል፣ የመሠረታዊ ካርታ ዝግጅት ስታንዳርድ ማኑዋልና የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መረጃ አሰባሰብና የመረጃ ትንተና ማኑዋል የተዘጋጁ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ በየደረጀው ለሚገኙ የኢንስቲትዩት 124 አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሶስት ክላስተሮች ኮምቦልቻ፣ ባህር ዳር እና ጐንደር ከተሞች ከ3 - 5 ቀን የቆየ ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል፡፡
ኢንስቲቲዩቱ ከከተሞች ጋር በተላይም ከትላልቅ ከተሞች ጋር የነበረው ግንኙነት በጣም ችግር ነበረበት ያሉት ዶ/ር ምትኩ ከደሴ፣ ከባህር ዳር፣ ከኮምቦልቻና ከደብረ ብርሃን ከተማ አመራሩ ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ችግሩን በመፍታት ተቀራርቦ መሰራት መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አክለው እንደገለጹት ተቋሙ በጥንካሬ በዕቅድ እንዲመራ መደረጉ፣ የሕግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት በህግና በአሰራር እንዲመራ መደረጉ፣ ከከተሞች ጋር መልካም ግንኙነት መፈጠሩና በሰው ሃይልና በግብዓት ለማሟላት ጥረት መደረጉ የሚገለጹ ናቸው ብለዋል፡፡
ባሳለፍነው በጀት ዓመት በክፍተት የታዩ የሙያተኞች አቅምና ልምድ ውንስንነት፣ በተወሰኑ አካላት ላይ የትጋትና የታታሪነት መጓደል፣ የሚሰሩ ፕላኖች በጥራትና በፍጥነት አልፎ አልፎ ያለመፈጸም ሁኔታ መታየቱን የገለጹት ዶ/ር ምትኩ የቀጣይ የትኩረት መስኮች ምቹ የሥራ አካባቢ መፈጠር፣ የሠራተኛውን የዕውቀት፣ የክህሎትና ልምድ ውስንነትን ለመፍታት የአቅም ግንባታ ስልጠና በስፋት መስራት፣ ፕላንን በሚመለከት የጥናትና ምርምር ሥራን ማካሄድና የገጠር ቀበሌ ማዕከላት ስኬች ፕላን በልዩ ሁኔታ በመፈጸም የገጠር ትራንስፎርሜሽን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመወጣት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

የውይይት መድረክ"የአብክመ ፕላን ኢንስቲትዩት የ4ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ"የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕላን ኢንስቲትዩት የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ ...
07/07/2026

የውይይት መድረክ
"የአብክመ ፕላን ኢንስቲትዩት የ4ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ"
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕላን ኢንስቲትዩት የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ እና መጪውን የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ለማስተዋወቅና ለመወያየት ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በዚህ የልማትና የዕቅድ መድረክ ላይ፦
✅ ባለፈው በጀት ዓመት የተከናወኑ ዋና ዋና የፕላን ዝግጅት፣ የጥናትና ምርምር እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች አፈፃፀም በጥልቀት ውይይት ተደርጎበታል።
✅ በጥንካሬ የታዩ አሰራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል እና ያጋጠሙ ማነቆዎችን በመለየት፣ በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት ይበልጥ ውጤታማና ክልላዊ ዕድገትን የሚያረጋግጡ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ላይ ሰፊ ውይይት ይደረጋል።
✅ የኢንስቲትዩቱ አመራሮችና መላው ባለሙያ የተጣለበትን ታላቅ ኃላፊነት በላቀ ደረጃ ለመወጣት የሚያስችላቸው የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።
ኢንስቲትዩቱ የክልላችንን ከተሞችና ገጠር ቀበሌ ማዕከላትን ሁለንተናዊ ልማት በሳይንሳዊ ጥናት፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በፕላን ለመምራት የሚያደርገውን ተቋማዊ ጉዞ አጠናክሮ ይቀጥላል!

05/07/2026

I got over 150 reactions on my posts last week! Thanks everyone for your support! 🎉

The Next Generation of Urban Planning​Tomorrow’s cities will not be built by concrete alone. They will be shaped by peop...
03/07/2026

The Next Generation of Urban Planning
​Tomorrow’s cities will not be built by concrete alone. They will be shaped by people who understand data, mobility, sustainability, policy, and human needs together.
​Urban planning is no longer just about roads and buildings. It is about creating cities that are smarter, greener, healthier, and more resilient.
​Every step matters:
​📊 Surveys reveal how communities live.
​🌱 Land use shapes environmental balance.
​👥 Demographics guide inclusive development.
​🚶 Mobility analysis improves accessibility and reduces emissions.
​🏙️ Development plans turn ideas into action.
​📜 Policy frameworks create long-term direction.
​💡 Smart city visions connect technology with sustainability.
​The future of green buildings and sustainable cities depends on a new generation of urban planners who can think beyond infrastructure and focus on people, climate, and resilience at the same time.
​Because a truly sustainable city is not measured by how tall its buildings are, but by how well it supports the lives within them.
​Cities are evolving.
The question is: are we designing them for the future, or simply expanding the past?

​ቀጣዩ የከተማ ፕላን ትውልድ
​የነገ ከተሞች በኮንክሪት ብቻ አይገነቡም። እነሱ የሚቀረጹት መረጃን፣ ተንቀሳቃሽነትን፣ ዘላቂነትን፣ ፖሊሲን እና የሰውን ፍላጎት በአንድ ላይ በሚረዱ ሰዎች ነው።
የዘመኑ ​የከተማ ፕላን እሳቤ ስለ መንገዶች እና ህንፃዎች ብቻ አይደለም። ይልቁንም ይበልጥ ስሉጥ፣ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ይበልጥ አይበገሬ የሆኑ ከተሞችን ስለመፍጠር ነው።
​እያንዳንዱ እርምጃ ዋጋ አለው፡
​📊 የዳሰሳ ጥናቶች ስለማህበረሰብ ሁለንተናዊ የአኗኗር ዘይቤ ያሳያሉ።
​🌱 የመሬት አጠቃቀም የአካባቢን ሚዛን ይቀርጻል።
​👥 የስነ-ህዝብ መረጃ ሁሉን አቀፍ ልማትን ይመራል።
​🚶 የተንቀሳቃሽነት ትንተና ተደራሽነትን ያሻሽላል፣የካርበን ልቀትንም ይቀንሳል።
​🏙️ የልማት እቅዶች ሃሳቦችን ወደ ተግባር ይቀይራሉ።
​📜 የፖሊሲ ማዕቀፎች የረጅም ጊዜ አቅጣጫ ይፈጥራሉ።
​💡 የስሉጥ ከተማ ራዕዮች ቴክኖሎጂን ከዘላቂነት ጋር ያገናኛሉ።
​የአረንጓዴ ህንፃዎች እና ዘላቂ ከተሞች መፃኢ እድል ከመሠረተ-ልማት ባሻገር ማሰብ በሚችሉ እና በተመሳሳይ ጊዜ በሰዎች፣ በአየር ንብረት እና በተቋቋሚነት ላይ ማተኮር በሚችሉ አዲስ የከተማ ፕላነሮች ትውልድ ላይ የተመሰረተ ነው።
​ምክንያቱም ዘላቂ የሆኑ ከተሞች የሚለኩት በህንፃዎች ቁመት ሳይሆን በውስጣቸው ያሉትን ህይወቶች ምን ያህል በጥሩ ሁኔታ እንደሚደግፋ ነው።

ጥያቄ፡-ከተሞቻችንን ፕላን እየሰራንላቸው እና እየተገበርን ያለነው ስለወደፊቱ ነው ወይስ በተለመደው እሳቤ ነው?

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Planning Institute posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share