04/06/2026
“ የዘርፉን የአሰራር መመሪያዎች በማዘጋጀት ለኢንቨስትመንቱ መስፋፋትና ውጤታማነት ጥረት እየተደረገ ነው”!!
አቶ ዮሐንስ አማረ
የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ
****
ባህርዳር፣ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም (ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ)
የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ለዘርፎቹ መስፋፋት ብሎም ስኬታማነት ከምንጊዜውም በላይ ያለሰለሰ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡
ቢሮው “የግብርና፣ ሆርቲካልቸር እና አገልግሎት ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች መገምገሚያና የመሬት መጠን ወስኖ ለማስተላለፍ የወጣ ረቂቅ መመሪያ ” እንዲሁም “የግብርና፣ ሆርቲካልቸር እና አገልግሎት ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የልማት አፈጻጻም ለመገምገም የወጣ ረቂቅ መመሪያዎች” ዙሪያ የቫሊዴሽን ወርክሾፖ ከተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር ዛሬ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ አካሂዷል ።
በወርክሾፑ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ አማረ እንደገለፁት እንደ ተቋም የኢንቨስትመንት ዘርፉን ይበልጥ ለማስፋፋትና ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው፤ ለዚህ ማሳያም የዠርፉ የአሰራር መመሪያዎች በረቂቅ ደረጃ ተዘጋጅተው አስፈላጊው የግብዓት ማሰባሰብ ተጠናክረው መቀጠሉን ጠቁመዋል፡፡ ረቂቅ መመሪዎቹም በአብክመ ፍትህ ቢሮ አቃቢያን ህግ አቶ ሺድጋፍ ሀይሌና አቶ ዮናታን ጠብቀው አማካኝነት ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኃላ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል ።
በሌላ በኩል ቢሮው በቅርቡ ''በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመሰማራት የሚቀርቡ የአዋጭነት ጥናት ሰነዶችን ገምግሞ የመስሪያ ቦታ(መሬት) ለመስጠት ተሻሽሎ የወጣ መመሪያ ቁጥር 138/2018'' እና ''ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የማስፋፊያ ቦታ(መሬት)ለመስጠት ተሻሽሎ የወጣ መመሪያ ቁጥር 140/2018'' አሻሽሎ ስራ ላይ ማዋሉ የሚታወስ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/investamhara?mibextid=ZbWKwL
Website- http://www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
WhatsApp- https://whatsapp.com/channel/0029Vb769KiHrDZb8EXzee0L
Twitter- https://x.com/amhara_and77292
See less