Amhara Industry and Investment Bureau

Amhara Industry and Investment Bureau The Amhara industry & Investment is found at Bahir Dar town which is the capital of Amhara Region

“ የዘርፉን የአሰራር መመሪያዎች በማዘጋጀት ለኢንቨስትመንቱ መስፋፋትና ውጤታማነት ጥረት እየተደረገ ነው”!!አቶ ዮሐንስ አማረየአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ****ባህ...
04/06/2026

“ የዘርፉን የአሰራር መመሪያዎች በማዘጋጀት ለኢንቨስትመንቱ መስፋፋትና ውጤታማነት ጥረት እየተደረገ ነው”!!
አቶ ዮሐንስ አማረ
የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ
****
ባህርዳር፣ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም (ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ)
የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ለዘርፎቹ መስፋፋት ብሎም ስኬታማነት ከምንጊዜውም በላይ ያለሰለሰ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡

ቢሮው “የግብርና፣ ሆርቲካልቸር እና አገልግሎት ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች መገምገሚያና የመሬት መጠን ወስኖ ለማስተላለፍ የወጣ ረቂቅ መመሪያ ” እንዲሁም “የግብርና፣ ሆርቲካልቸር እና አገልግሎት ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የልማት አፈጻጻም ለመገምገም የወጣ ረቂቅ መመሪያዎች” ዙሪያ የቫሊዴሽን ወርክሾፖ ከተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር ዛሬ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ አካሂዷል ።

በወርክሾፑ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ አማረ እንደገለፁት እንደ ተቋም የኢንቨስትመንት ዘርፉን ይበልጥ ለማስፋፋትና ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው፤ ለዚህ ማሳያም የዠርፉ የአሰራር መመሪያዎች በረቂቅ ደረጃ ተዘጋጅተው አስፈላጊው የግብዓት ማሰባሰብ ተጠናክረው መቀጠሉን ጠቁመዋል፡፡ ረቂቅ መመሪዎቹም በአብክመ ፍትህ ቢሮ አቃቢያን ህግ አቶ ሺድጋፍ ሀይሌና አቶ ዮናታን ጠብቀው አማካኝነት ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኃላ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል ።

በሌላ በኩል ቢሮው በቅርቡ ''በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለመሰማራት የሚቀርቡ የአዋጭነት ጥናት ሰነዶችን ገምግሞ የመስሪያ ቦታ(መሬት) ለመስጠት ተሻሽሎ የወጣ መመሪያ ቁጥር 138/2018'' እና ''ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የማስፋፊያ ቦታ(መሬት)ለመስጠት ተሻሽሎ የወጣ መመሪያ ቁጥር 140/2018'' አሻሽሎ ስራ ላይ ማዋሉ የሚታወስ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/investamhara?mibextid=ZbWKwL
Website- http://www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
WhatsApp- https://whatsapp.com/channel/0029Vb769KiHrDZb8EXzee0L
Twitter- https://x.com/amhara_and77292
See less

ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛዉ አመተ ሂጅራ የኢድአል አድሀ አረፋ በአል እንኳን አደረሳችሁ::የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚ...
26/05/2026

ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛዉ አመተ ሂጅራ የኢድአል አድሀ አረፋ በአል እንኳን አደረሳችሁ::
የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩ ታላላቅ በዓላት ዘንድ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው እና የአብሮነት እሴቶች በጉልህ የሚገለፅበት በዓል ነው፡፡

ህዝበ ሙስሊሙ በመተባበር፣ አብሮነትን በማጠናከር፣ እርስ በእርስ በመደጋገፍ እና በመቻቻል፣ በድምቀት የሚያከብረው በዓል ነው።

የኢድ አል-አድሃ በዓል የርህራሄ፣ ከራስ ይልቅ ለሌሎች የመስጠት; የመታዘዝ፣ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት በዓል ነው።

በዓሉ የማህበራዊ ትስስር እሴቶችም በህዝቡ ዘንድ በይበልጥ የሚጎለብቱበት ታላቅ በዓል ነው።

ይህንን በዓል ስናከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመደገፍ እና ሠላማችንን በመጠበቅ ሊሆን ይገባል።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆን ቢሮው ይመኛል።
ኢድ ሙባረክ!

26/05/2026
23/05/2026

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የለውጥ አመታት እመርታ ...

23/05/2026

#አሚኮ #አሚኮንጋት #አቦልዜና #እልፍኝ #አዲስጨዋታ #ግዕዝ #አሚኮዲጂታልሚዲያቀጣዮችን ማስፈንጠሪያዎች በመጫን የአሚኮ ቤተሰብ ይሁኑድረገጽ www.ameco.etዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCqረም.....

ደብረ ማርቆስ፦ የዕድገት ማማ እና የኢንቨስትመንት ተመራጭ መዳረሻ !​በአማራ ክልል እምብርት ላይ የምትገኘውና የታሪካዊው የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና መቀመጫ የሆነችው ደብረ ማርቆስ ከተማ፣ በአ...
23/05/2026

ደብረ ማርቆስ፦ የዕድገት ማማ እና የኢንቨስትመንት ተመራጭ መዳረሻ !

​በአማራ ክልል እምብርት ላይ የምትገኘውና የታሪካዊው የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና መቀመጫ የሆነችው ደብረ ማርቆስ ከተማ፣ በአሁኑ ወቅት የሪጂዮፖሊታን ከተማነት ደረጃን ተጎናጽፋ ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ከፍታ እየተመመች ያለች ተምሳሌት ናት። ከአማራ ክልል መዲና ባሕር ዳር በ265 ኪሎ ሜትር፣ ከሀገሪቱ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ደግሞ በ299 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ይህች ከተማ፣ ስትራቴጂካዊ መገኛዋን ተጠቅማ የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል እየሆነች ትገኛለች።

​ከተማዋ ከ17,000 ሄክታር በላይ ስፋት ባለው መሬት ላይ የተዘረጋች ሲሆን፣ በአስተዳደራዊ መዋቅርም በ4 ክፍለ ከተሞች እና በ20 ቀበሌዎች ተደራጅታ ከ323,105 በላይ ለሚሆን ንቁና አምራች ህዝብ መኖሪያ መሆን ችላለች።
​ደብረ ማርቆስ ከተማ ከባሕር ወለል በላይ በ2,420 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝ በመሆኗ፣ ዓመቱን ሙሉ እጅግ ማራኪና ለኑሮም ሆነ ለሥራ ምቹ የሆነ የወይና ደጋ አየር ንብረት አላት። ዓመታዊ የዝናብ መጠኗ 1,380 ሚሊ ሜትር ሲሆን፣ ማራኪ ገጽታን የተላበሰው የመሬት አቀማመጧ ደግሞ 75 በመቶ ኮረብታማ፣ 20 በመቶ ተዳፋት እና 5 በመቶ ሜዳማ ቅርጽ አለው።
​ይህ የተፈጥሮ ስጦታ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከማድረጉም በላይ፣ ለከተማ ግብርና እና ለቱሪዝም ልማት ልዩ ምህዳር ይፈጥራል።
​ከተማዋን ለየትኛውም የኢንቨስትመንት ዘርፍ ተመራጭ ከሚያደርጓት ቀዳሚ ምክንያቶች አንዱ በዙሪያዋ ያሉ ከ20 በላይ ትርፍ አምራች ወረዳዎች መኖራቸው ነው። እነዚህ ወረዳዎች ለኢንዱስትሪዎች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ዘርፈ-ብዙ የጥራጥሬ፣ የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በስፋት የሚያቀርቡ የከተማዋ የጀርባ አጥንቶች ናቸው።
​በዚህ እምቅ አቅም ሳቢያ በአሁኑ ወቅት ከ169 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች መሬት ተረክበው በግንባታ እና በምርት ሂደት ላይ ይገኛሉ።
ከተማዋ ለባለሀብቶች የምታቀርበው ሰፊ የመሬት አቅርቦት እና በየደረጃው የሰለጠነና የተማረ የሰው ኃይል መኖሩ፣ ለኢንዱስትሪዎች መፋጠን ትልቅ ጉልበት ሆኗል።

​ደብረ ማርቆስ የረጅም ዘመን ታሪክ፣ የባህል እና የቱሪዝም መዳረሻ የወለደች ከተማ ናት። የከተማዋ ማህበረሰብ ሰው አክባሪ፣ እንግዳ ተቀባይ እና እሴቱን ጠባቂ በመሆኑ ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ትልቅ መሰረት ጥሏል። ይህንን እምቅ አቅም ተከትሎ በከተማዋ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ እንዲሁም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ፈጣንና አስደናቂ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል። ዘመናዊ ህንጻዎች፣ የመዝናኛ ስፍራዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች የከተማዋን ገጽታ በየዕለቱ እየቀየሩት ነው።
​​ደብረ ማርቆስ ከተማ ምቹ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥን፣ የተፈጥሮ ሀብትን፣ ሰፊ የገበያ ዕድልን እና አስተማማኝ የመንግስት ድጋፍን አስተባብራ የያዘች የወደፊት የኢንቨስትመንት ምድር ናት።
በኢንዱስትሪ ዘርፍ ማለትም በአግሮፕርሰሲንግ፣ በኬሚካልና ኮንስትራክሽን፣በማዕድን፣ በጨርቃጨርቅና ቆዳ፣ በእንጨትና ብረታብረት ፣በሪል-እስቴት፣ በቱሪዝም እና በሌሎች በርካታ አማራጮች ለመሰማራት ፍላጎት ላላችሁ ባለሀብቶች በሙሉ፣ ደብረ ማርቆስ የላቀ ስኬት የሚረጋገጥባት ተመራጭ ከተማ በመሆን እጆቿን ዘርግታ ትጠብቃችኋለች።

ሀበሻ ጋቢዮን ማምረቻ ድርጅት አቋርጦ የነበረውን የማምረት ስራ  ጀመረ።******************************************************ባህርዳር: ግንቦት 15/2018 ዓ...
23/05/2026

ሀበሻ ጋቢዮን ማምረቻ ድርጅት አቋርጦ የነበረውን የማምረት ስራ ጀመረ።
******************************************************
ባህርዳር: ግንቦት 15/2018 ዓ.ም (ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ)
የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ በተከታታይ ባደረገው ድጋፍናክትትል ለረጅም ወራት ስራ አቋርጦ የቆየውን ኢንዱስትሪ በድጋሜ ስራ አስጀመረ። ይህ ፕሮጀክት አጋጥሞት የነበረውን የጥሬ ዕቃ ግብዓትና የገበያ ትስስር ችግር በተከታታይ በተደረገው ድጋፍ ሁሉም ችግሮች ተፈትተውለት በአሁኑ ሰዓት በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ገብቷል።
ጋብዮን ማምረቻው በአሁኑ ወቅት ለ180 ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠረና በቀን 1500 ሜትር ኪዬብ የጋቢዮን ምርት እያመረተ ይገኛል። ይህንንም ፕሮጀክት የመምሪው ሀላፊው አቶ አስራት መሠለ ፣ የፓርኮች ሀላፊ አቶ ፀጋው አለሙና ሌሎች ባለሙያወች በቦታው ተገኝተው ጉብኝት አድርገዋል።
ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/investamhara?mibextid=ZbWKwL
Website- http://www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
WhatsApp- https://whatsapp.com/channel/0029Vb769KiHrDZb8EXzee0L
Twitter- https://x.com/amhara_and77292

የስርዓተ ፆታና ማህበራዊ ጉዳዮች አካታችነት ስኬታማነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች  የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ማደግ ሚናው የጎላ መሆኑ ተገለፀ!************ባህርዳር፣  ግንቦት 1...
20/05/2026

የስርዓተ ፆታና ማህበራዊ ጉዳዮች አካታችነት ስኬታማነት ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ማደግ ሚናው የጎላ መሆኑ ተገለፀ!
************
ባህርዳር፣ ግንቦት 12/2018 ዓ.ም. (ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ)
የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሰራተኞች በወቅታዊ ኤች.አይ. ቪ/ኤድስ ስርጭትና የስርዓተ-ፆታና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ዙሪያ የፓናል ውይይት አካሂደዋል።

የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ ታረቀኝ በፓናል ውይይቱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት እንደ መንግስትም ሆነ እንደ ተቋም ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር የስርዓተ ጾታና አካቶ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም በጣም አስከፊ የነበረውን የኤች. አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭት በመቀነስ ረገድ አመርቂ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ እንደሚታወቀው ይህ በሽታ የሚያጠቃው አምራች ሀይሉን ነውና በየደረጃው ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን መስራት ይጠበቅብናል ሲሉም ገልጸዋል፡፡ ዘርፋችን በተለይም አምራች ኢንዱስትሪዎች ወጣቱን የሰው ሀይል የያዙ በመሆኑ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን መስራት አይነተኛ መንገድ እንደሆን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡

በቢሮው የስርዓተ ፆታና አካቶ ትግበራ ባለሙያ አቶ አብርሀም ምትኬ ለፓናል ውይይቱመነሻ ፅሁፍ አቅርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎ የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ አማረ ለተነሱ ሀሳቦች ማብራሪያና ማጠቃለያ ሰጥተው መድረኩ ተጠናቋል።

18/05/2026

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ በቀሪ ሁለት ወራት እቅድ ዙሪያ ሲወያዩ በፎቶኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ ...
18/05/2026

የአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ በቀሪ ሁለት ወራት እቅድ ዙሪያ ሲወያዩ በፎቶ
ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/invpestamhara?mibextid=ZbWKwL
- http:/www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
ፈኀWhatsApp- https://chat.whatsapp.com/C7sUyLeKQ5D9C4kLK4Uizo
Twitter- https://x.com/amhara_and77292
TikTok- https://www.tiktok.com/.regi?_t=8rw4bEMf3hg...
See less

Address

Ethiopia, Amhara Provision
Bahir Dar

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251582201454

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Industry and Investment Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share