03/06/2026
በኤፍራታ ግድም ወረዳ በ14.8 ሚሊዮን ብር የሚገነባው የመስኖ ካናል ፕሮጀክት አፈጻጸም 65 በመቶ ደረሰ
ባህር ዳር፦ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም (አስስአኮ)
በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ ግድም ወረዳ ፈረዶ ቀበሌ በአብክመ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን "ያልተማከለ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ስራ አመራርን ማጠናከር ፕሮጀክት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ የሚገኘው የመስኖ ካናል ግንባታ አፈጻጸም 65 በመቶ መድረሱ ተገልጿል። ከክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር እየተከናወነ ለሚገኘው ለዚሁ ፕሮጀክት 14.8 ሚሊዮን ብር በጀት መመደቡ ታውቋል።
የአካባቢውን አምራች ኃይል ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የሚጠበቀው ይህ የመስኖ ልማት ስራ በአሁኑ ወቅት በጥሩ አፈጻጸም ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ እስካሁን ባለው ሂደት 1.5 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገድ ጠረጋ ስራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። በተጨማሪም 183 ሜትር ኩብ የድንጋይ ግድብ ስራ እና 190 ሜትር ኩብ የድንጋይ ማቅረብ ተግባር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል።
ለግንባታው የሚያስፈልገው 250 ኩንታል ሲሚንቶ ቀድሞ በቦታው እንዲደርስ የተደረገ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት የ100 ሜትር የካናል ቁፋሮ እና የስትራክቸር ግንባታ ስራዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህ የመስኖ ካናል ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ በአካባቢው የሚገኘውን ማህበረሰብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የአደጋ ስጋትን ለመቀነስ የጎላ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል።
#ተግባራችን #የመስኖልማት #ኤፍራታግድም #የአደጋስጋትስራአመራር
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት
Like,Shares & Comment ያድርጉ
📌 ድረ-ገጽ፦ Web:-https://anrsdpfsc.org.et
***
📌 ፌስቡክ:-www.facebook.com/profile.php?id=100067131507069
***
📌 ዩቲዩብ፦https://youtube.com/
***
📌 ቲክቶክ፦ tiktok.com/
***
📌 ቴሌግራም፦ https://t.me/ADRMC_1
***
📌 ቲዊተር /x አካውንት፦ https://x.com/disaster_food_1
***
📌 ኢንስታግራም፡- https://www.instagram.com/drmc_1
***
📌 ዋትስአፕ፦https://whatsapp.com/channel/0029VbCXynhJuyAF8GRYmW1N
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!