Bahirdar City Communications

Bahirdar City Communications This is Home Page for Bahir Dar City Communication Affairs Office. which is used as a Bridge between Peoples of Bahir dar city and Government.

ምሥራቅ ዕዝ እና የክልሉ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት የተቀናጀ ርምጃ ምርጫውን ለማደናቀፍ በሞከረው  የጽንፈኛው ቡድን ላይ  ኪሳራ ደርሷል።ሰሞኑን በደቡብ ጎንደር፣ በምዕራብ ጎጃም፣ በሰሜን ጎጃ...
04/06/2026

ምሥራቅ ዕዝ እና የክልሉ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት የተቀናጀ ርምጃ ምርጫውን ለማደናቀፍ በሞከረው የጽንፈኛው ቡድን ላይ ኪሳራ ደርሷል።

ሰሞኑን በደቡብ ጎንደር፣ በምዕራብ ጎጃም፣ በሰሜን ጎጃም እና በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ውስጥ ምሥራቅ ዕዝ ባደረገዉ ኦፕሬሽን 204 ተላላኪ ጽንፈኞችን በመደምሰስ 161 ማቁሰሉን ገልጿል።

በሰሜን ጎጃም ዞን የተሰማራዉ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል አዲሱ መሀመድ እንዳሉት ኢትዮጵያ ሊወራት የመጣውን ጠላት ባይደፈሬነት አሳፍራ የመለሰችና ለዘመናት ተከብራ የኖረች ናት ብለዋል። ይህችን ሀገር መንግሥት አልባ እና የተዳከመች ለማድረግ እንዲሁም በዴሞክራሲያዊ መንገድ ሳይኾን ባፈሙዝ ሥልጣን ለመያዝ ያለሙ የታሪካዊ ጠላቶቻችንን ተልዕኮ ያነገቡ ባዕዳን እና ባንዳዎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል። እነዚህ አካላት 7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ እዳይካሄድ ሕዝቡን ለመረበሽ እና ሁከት ለመፍጠር ያቀዱትን የተንኮል ሴራ ሠራዊቱ ከማኅበረሰቡ እና ከክልሉ የጸጥታ አካላት ጋር ጥምረት በመፍጠር ሕዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ያለ አንዳች የጸጥታ ስጋት እንዲፈጽም ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

በዚህ ቀጣና 29 የጽንፈኛ ቡድን አባላት ሲደመሰሱ 47ቱ ደግሞ ቁስለኛ ኾነዋል። ኅብረተሰቡ ለሰላም ያለውን ጽኑ ፍላጎት እና የዘራፊውን ጽንፍኛ ተልዕኮን አንግበው ለሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ያለውን የመረረ ጥላቻ አሳይቷል ነዉ ያሉት።

ሠራዊቱ በምዕራብ ጎጃም እና አዊ ብሔረሰብ ዞን በተሰማራንባቸዉ ቀጣናዎች በተለይም #በፍኖተሰላም እና በቲሊሊ ከተሞች ዙሪያና በተለያዩ አካባቢዎች የአካባቢዉን ሰላምና ጸጥታ ለማናጋት አቅዶ የመጣዉን የጠላት ኃይል በጀግናዉ የኮሩ ክፍለ ጦሮች እና ስታፍ ክፍሉ እንዲሁም በጥምር ጦሩ በደረሰበት ከፍተኛ ምት ህልሙ ቅዠት ሆኖበታል ነዉ ያሉት።

በዚህ ከፍተኛ ኦፕሬሽን በጽንፈኛው ላይ የሰዉ ሀይል እና የቁሳቁስ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን፤ የተደመሰሰ የጠላት ሃይል 85፣ የቆሰለ 40፣ የተማረከ 01፣ እጅ የሰጠ 01 መኾኑ ተጠቁሟል። አንድ ብሬን፣ ስድስት ክላሽ፣ ሁለት የቃታ መሳርያ፣ 4 የብሬን ዝናር ከነ ጥይቱ ፣ አንድ የእጅ ቦምብ፣ ሶስት የክላሽ ካዝና እና አንድ ትጥቅ መመማረኩንም ጠቅሰዋል።

ከተደመሰሱት የጽንፈኛው አባላት መካከልም ሙሉጌታ የተባለ የፅፈኛዉ ሻለቃ አዛዥ፣ ዋሴ ወርቁ ጎድ አዛዥ፣ ጤናዉ አቻም ክፍለ ጦር አዛዥ እና የቡድን መሳርያ ተኳሾች ይገኙበታል።

በደቡብ ጎንደር ዞንም በደብረ ታቦር፣ በእስቴ፣ በአንዳቤት፣ በስማዳ፣ በሳሊ፣ በንፋስ መውጫ፣ በታች ጋይንት፣ በላይ ጋይንት እና ክምር ድንጋይ ላይ ጽንፈኛዉ ያለ የሌለውን ኃይል ከተደበቀበት ጉድጓድ አሰባስቦ የኅብረተሰቡን ሰላም ለማወክ ቢመጣም በሠራዊቱ እና በክልሉ የጸጥታ ኃይል የተቀናጀ ኦፕሬሽን ጠላት ሙትና ቁስለኛ መሆኑን የቀጠናዉ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ልጃለም ምትኩ አብራርተዋል።

በዚህ ቀጣናም በጠላት ላይ የደረሰው ቁሳዊ እና ሰብዓዊ ኪሳራ ሲታይ የተደመሰሰ ጠላት 90፣ የቆሰለ 74፣ የተማረከ ክላሽ 09፣ የቃታ መሳሪያ 11 እና አንድ ጂም 3 መሳሪያ ተማርኳል።

በቀጣናው ግዳጃቸውን በአመርቂ ውጤት እየፈፀሙ ያሉት የክፍለ ጦር አመራሮች እንደተናገሩት ሠራዊቱ ጠላትን ጠንቅቆ የሚያውቅ እና ለሚሰጠው ግዳጅ አስፈላጊውን ሥነ ልቦናዊ እና ወታደራዊ ዝግጅት በማድረግ ከፍተኛ ጥቃት በመፈጸም ተስፋ እንዲቆርጥ አድርጓል ነው ያሉት። ዛሬም ነገም የሀገራችን ሰላም እና ፀጥታ ለመጠበቅ ዝግጁ ነው ብለዋል።



Finote Selam City Communications

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ ------------------(ዜና ፓርላማ)  ግንቦት 27፣ 2018 ዓ.ም፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ጉ...
04/06/2026

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ
------------------
(ዜና ፓርላማ) ግንቦት 27፣ 2018 ዓ.ም፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አፀደቀ።

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አፅድቋል።

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ፈትሂ ማህዲ( ዶ/ር ) የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ በኢትዮጵያና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ ባዮሎጂካል ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል የጋራ ሳይንሳዊ እና ጥናታዊ የምርምር ስራዎችን ለማጠናከርና ለማሳደግ እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር መሰረተ ልማት ግንባታ እንዲሁም የምርምር ውጤትን ወደ ገበያ የማቅረብ ተቋማዊ ቅርጽ በማስያዝ የሁለቱ ሀገራት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ምክትል ሰብሳቢው አያይዘው ገልጸዋል፡፡

የሀገር በቀል የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን የዓሳ ሀብት ልማት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው እንደመሆኑ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ወደ ውጭ ኤክስፓርት ለማድረግ ሩሲያ በዘርፉ ካላት ከፍተኛ ልምድ ለማካበት እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡

በመሆኑም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅ ፣አዋጅ ቁጥር 1421/2018 ሆኖ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።

በተመሳሳይ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመ ስምምነት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፅድቋል።

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ፈትሂ ማህዲ( ዶ/ር ) የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

ምክትል ሰብሳቢው በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመው ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን የሁለትዮሽ ትብብርንና የዲፕሎማሲ ግንኙነት መስመርን ለማጠናከር የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል።

እንዲሁም ቪዛ ለማግኘት የሚያስፈልጉትን ቅድመ -ሁኔታዎችና የሚወስደውን ጊዜ በማስቀረት የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል እና አገልግሎት ፓስፖርት የያዙ የሁለቱ አገራት ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናትና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ዜጎች በየጊዜው የሚያደርጉት እንቅስቃሴና ጉዞ በቀላሉ እንዲመቻች የሚያደርግ መሆኑን አያይዘው ተናግረዋል ።
በመሆኑም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 1422/2018 ሆኖ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።

(በ ፀሀይ ነጋሽ)

04/06/2026

ባሕርዳር ከተማን ለነዋሪዎቿ ውብ፣ምቹ፣ አረንጓዴ፣ የማድረግ ጉዞው ተጠናክሮ ይቀጥላል።

🌊 ባህርዳር፡ የጣና ዕንቁና የከተሞች የውበት አምባባህርዳር ዛሬ የለውጥ ነፋስ እየነፈሰባት ነው። ጥንታዊው የጣና እና የዓባይ ቃልኪዳን በዘመናዊ የከተማ ልማት ታጅቦ ከተማዋን ወደ አዲስ ምዕ...
04/06/2026

🌊 ባህርዳር፡ የጣና ዕንቁና የከተሞች የውበት አምባ

ባህርዳር ዛሬ የለውጥ ነፋስ እየነፈሰባት ነው። ጥንታዊው የጣና እና የዓባይ ቃልኪዳን በዘመናዊ የከተማ ልማት ታጅቦ ከተማዋን ወደ አዲስ ምዕራፍ እያሸጋገራት ይገኛል። በተለይም በሁለት ዋና ዋና ግዙፍ ፕሮጀክቶች አማካኝነት የባህርዳር ገጽታ በአይን በሚታይ ፍጥነት እየተቀየረ ነው።

🏙️ የኮሪደር ልማት፡ የከተማዋ አዲስ መተንፈሻ
የከተማዋን ዋና ዋና መንገዶችና አደባባዮች ደረጃቸውን በጠበቁ የእግረኛ መንገዶች፣ በብስክሌት መስመሮችና በአረንጓዴ ስፍራዎች የማስዋቡ ስራ ባህርዳርን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለቱሪስቶች ደግሞ ሳቢ እያደረጋት ነው።

መንገዶች ከትራፊክ መጨናነቅ ወጥተው ለሰዎች እንቅስቃሴ ቅድሚያ እንዲሰጡ ተደርገው እየተሰሩ ነው።

የሌሊት ድምቀት፡ ዘመናዊ የጎዳና ላይ መብራቶችና የጌጣጌጥ ስራዎች ባህርዳርን በሌሊትም እንደ ቀን ውብ አድርገዋታል።

🌿 የጣና ዳር (Tana Dar) ልማት፡ ከተማዋ ወደ ውሃዋ ስትመለስ
ለዘመናት የቆየው የባህርዳርና የጣና ግንኙነት አሁን በይፋዊ የልማት ፕሮጀክት እየታጀበ ነው። የጣና ዳር ልማት ከተማዋን ከሀይቁ ጋር የሚያስተሳስር ድልድይ ሆኗል።

የመዝናኛ ማዕከላት፡ በሀይቁ ዳርቻ የሚገነቡት መናፈሻዎች ነዋሪው ከሀይቁ ንጹህ አየር እየተነፈሰ ዘና እንዲል ዕድል እየፈጠሩ ነው።

የኢኮኖሚ መነቃቃት፡ ይህ ልማት የቱሪስት ፍሰቱን ከመጨመሩም በላይ ለአካባቢው ወጣቶችና ስራ ፈጣሪዎች አዳዲስ የንግድ እድሎችን ይዞ መጥቷል።

ባህርዳር የውሃና የለምለም ተፈጥሮ ባለቤት ብቻ ሳትሆን፣ አሁን ደግሞ የጽዱና የዘመናዊ ከተማ ተምሳሌት ለመሆን እየገሰገሰች ነው። የኮሪደር ልማቱ ቅልጥፍናን፣ የጣና ዳር ልማቱ ደግሞ ውበትንና ሰላምን ሰጥቷታል። ባህርዳር ዛሬም፣ነገም የኢትዮጵያ የቱሪዝም ልብ ሆና እንደምትቀጥል ጥርጥር የለውም!

ባህርዳር—በለውጥ ጎዳና ላይ ያለች የውበት ተምሳሌት!

የባሕርዳር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም የውይይት መድረክ ተካሄደ። ግንቦት 27/2018 ዓ/ም (ባሕርዳር ከተማ ኮሙዩኒኬሽን) የባሕ...
04/06/2026

የባሕርዳር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም የውይይት መድረክ ተካሄደ።

ግንቦት 27/2018 ዓ/ም (ባሕርዳር ከተማ ኮሙዩኒኬሽን) የባሕርዳር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን በማስመልከት የማጠቃለያ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄደ።

የአማራ ክልል ማዕድን ልማት ቢሮ ኅላፊ አቶ ሀይሌ አበበ እንደገለፁት ምርጫው ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ እና በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው እንዲሆን የማህበረሰቡ ተሳትፎ እና የአመራሩ ቁርጠኝነት የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

በባሕርዳር ከተማ የታየው ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፣ ማህበረሰቡ ከቅድመ ምርጫ እስከ ድህረ ምርጫ ለሰላም ላሳየው ቁርጠኝነት እንዲሁም በባሕርዳር ከተማ የነበረው የምርጫ ንቅናቄ ለሌሎች አካባቢዎች ተሞክሮ እንደነበር ጠቁመው ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን ላደረጉ አካላት ምስጋና ሰጠዋል።

የባሕርዳር ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት ድልንና የድልን ፍሬ ጨብጠው ለተገኙት ታዳሚዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ በምርጫው ችግሮችን ገምግሞ መፍትሄ የሚሰጥ አመራር የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።

የምርጫው ሂደትም አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ተከፍቶ የታየበት መሆኑን አብራርተዋል።

ክቡር ከንቲባው አክለው "እኛም ትናንት የመጣንበትን መንገድ እያነሳን የምንቆም ሳይሆን ከፊታችን የሚመጣውን መልካም ጊዜ እያሰብን የምንሻገር" መሆን ይገባል ብለዋል።

ቀጣይ ባሕርዳርን ፤በአዲስ ገጽታ የጣናና የዓባይ ዳርቻዎችን በማልማት "ስማርት ባሕር ዳር!” ይበልጥ ለመገንባት ትኩረት ሰጠን እንሰራለን ብለዋል።

የባሕርዳር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኅላፊ አቶ ሞላ ሁሴን እንደገለጹት ምርጫው ሰላማዊ፣ዴሞክራሲያዊ፣ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ምርጫ ሆኖ መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው ገልጸው ከምርጫ በኋላ የተቀመጡ ስራዎችን ትኩረት ሰጦ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የህዝብ ጥያቄዎችን ፈጥኖ ምላሽ በመስጠት የዜጎችን ህይወት የሚያሻሽሉ ሰው ተኮር ተግባራትን አጠናክሮ መፈፀም እንደሚገባ ተናግረዋል።

ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች፣የከተማዋ ኗሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች መላው የጸጥታ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

በመድረኩ የክልል፣ የከተማ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች ተገኝተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የባሕርዳር ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ገጽ ይወዳጁ:-
Facebook
https://www.facebook.com/BahirdarcityGovenmentalCommunicationAffairsoffice
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCNoAcvzPiExah4lyaAb6_BQ
Telegram
https://t.me/Bahirdarcitycommunication
Twitter
https://x.com/BahirdarO8493?s=35
Tiktok
https://www.tiktok.com/

04/06/2026
03/06/2026

#ባሕርዳር

03/06/2026

የኮሪደር ልማት የቀየረዉ የባህርዳር አዲስ ገጽታ በከፊል

03/06/2026

ኢትዮጵያውያን ሊኮሩ ይገባል - የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን

"Today is a day the people of Ethiopia should be proud" - AU Mission Commends Ethiopia's Electoral Process

03/06/2026

Address

Bahir Dar
6000

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 12:00

Telephone

+251582262889

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahirdar City Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Bahirdar City Communications:

Share