06/09/2026
በደባርቅ ወረዳ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀበሉ።
በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል።
በወረዳው ከሰሞኑ በርካታ ታጣቂዎች የሰላም እጦት በኅብረተሰቡ ላይ እያሳደረ የሚገኘውን ዘርፈ ብዙ ጫና በመገንዘብ የሰላም አማራጭን እየተቀበሉ ነው።
ጷግሜ 01/2018 ዓ.ም በወረዳው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 32 ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበላቸውን የደባርቅ ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።
አማራ ኮሙኒኬሽን