Amhara Region Police

Amhara Region Police law enforcement organization

በሚሊዮን የሚቆጠር የህዝብና የሀገር ሀብት የዘረፉ ተጠርጣሪዎች  በቁጥጥር ስር ዋሉ።በደሴ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመሮችን እና የቴሌኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማት እቃዎች...
04/09/2026

በሚሊዮን የሚቆጠር የህዝብና የሀገር ሀብት የዘረፉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በደሴ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመሮችን እና የቴሌኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማት እቃዎችን ሲዘርፉ የነበሩ ግለሰቦች፣ ከተደበቁበትና ከቀበሩት ንብረት ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ከ4ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ጋር በመቀናጀት ባደረገው ጥብቅ የምርመራ ስራ፣ በአንድ ግቢ ውስጥ ተበታትነውና ተደብቀው ይገኙ የነበሩ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር የሚያወጡ የኃይል ማስተላለፊያ ትራንስፎርመሮች እና የቴሌ እቃዎች ሙሉ በሙሉ ተይዘዋል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጥላሁን ታደሰ እንደገለጹት፣ የተፈጸመው ድርጊት ሀገርን ከማጥፋት የማይተናነስና ህዝብን ከሰላም አስከባሪው ለመነጠል የታለመ እኩይ ተግባር መሆኑን አንስተዋል።

መምሪያው ልዩ የምርመራ ቡድን አዋቅሮ ወደ ስራ በመግባቱ የተሳካ ውጤት መገኘቱን ጠቁመው፣ በተጠርጣሪዎች ላይ የሚደረገው ህጋዊ ማጣራት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

አዛዡ አያይዘውም ምርመራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና መረጃ በመስጠት ለዚህ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ሚና ለተጫወተው ማህበረሰብና ድርጊት ፈፃሚዎችን አካላት ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ላዋለው የፀጥታ ኃይሎችን ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል ።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሠላም እና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ሠይድ አሊ በበኩላቸው፣ ሀገርንና ህዝብን ለማልማት የሚደረገውን ጥረት ለማደናቀፍ የተደራጀ የዘራፊዎች ቡድን በቁጥጥር ስር መዋሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለውም ድርጊቱ ማንም አካል ከህግ እጅ ማምለጥ እንደማይችል የሚያሳይ በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር የሚያደርገውን አጋርነት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደሴ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ሀብቱ አበበ፣ ከሐምሌ ወር ጀምሮ ተባብሶ የነበረውን የስርቆት ወንጀል በማስቆም የንብረት ውድመትን ለመታደግ ለተደረገው ከፍተኛ የትብብር ስራ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ሴኩሪቲ ማናጀር ኮሎኔል ገዛህኝ አለባቸው በበኩላቸው፣ ተቋሙ ጉዳዩን ከአጋር የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በልዩ ትኩረት እየተከታተለው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በባህር ዳር ከተማ ሰዎችን በማገት የተሳተፉ የወንጀል ቡድን አባላትና የመንግስት ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዋሉ።በባህር ዳር ከተማ በሰዎች ላይ እገታ በመፈፀም፣ ገንዘብ በመጠየቅና በመቀበል ወ...
04/09/2026

በባህር ዳር ከተማ ሰዎችን በማገት የተሳተፉ የወንጀል ቡድን አባላትና የመንግስት ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በባህር ዳር ከተማ በሰዎች ላይ እገታ በመፈፀም፣ ገንዘብ በመጠየቅና በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ የወንጀል ቡድን አባላትና ለወንጀሉ መፈፀሚያነት የዋለ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ።

ተጠርጣሪውቹ ታጋቾቹን አፍነው በመውሰድ ለ11 ቀናት አግተው ያቆዩዋቸው ሲሆን፤ በወቅቱ ታጋቾቹን ለመልቀቅ 3 ሚሊዮን 370 ሺህ ብር ከቤተሰቦቻቸው በመጠየቅና ገንዘቡ ከተከፈላቸው በኋላ እንዲለቀቁ ማድረጋቸውን የምርመራ መረጃው ያመላክታል።

የመምሪያው የወንጀል ምርመራ ምክትል መምሪያ አዛዥ ኮማንደር መኳንንት አድማስ እንደገለጹት ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 (ኤፍራታ) አካባቢ ነዋሪና ነጋዴ የሆኑ ሶስት ግለሰቦች በራሳቸው ተሽከርካሪ ወደ ስራ ቦታቸው በመሄድ ላይ እያሉ በወቅቱ ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት እገታ ተፈፅሞባቸዋል ብለዋል።

ተጠርጣሪዎቹ ታጋቾቹን በመንግስት ተሽከርካሪ አፍነው በመውሰድ ለ11 ቀናት አግተው ማቆየታቸውን ያስረዱት ኮማንደር መኳንንት የወንጀሉ አደራጆች እና ተሳታፊዎች በቅንጅት የሰሩ መሆኑን አክለው አስታውቀዋል።

በተደረገው ጥብቅ ክትትልም 1ኛ. ወንጀሉን በዋናነት ያስተባበረው አብርሃም ጫኔ የተባለ በቀበሌ 06 የኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ባለቤት፤

2ኛ. ተሽከርካሪን ለወንጀል ያዋለ መለሰ ጌትነት የተባለ አሽከርካሪ ግለሰብ፤

3ኛ. ታጋቾቹን ደብቆ ያቆየውና ወንጀሉን የሸፈነው በቀበሌ 14 እንዘግድብ አካባቢ የሚገኝ ህንፃ አስተዳዳሪ (170 ሺህ ብር ክፍያ በመቀበል ወንጀሉን ያደባበሰ)፤

4ኛ. አበበ ጌቴ፣ ከአዲስ አበባ የተሳተፈ ተባባሪን ጨምሮ እስከ 870 ሺህ ብር በባንክ አካውንት ገቢ በማድረግ ረገድ የተሳተፉ አባላት፤ በአጠቃላይ አምስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ኮማንደር መኳንንት ያስታወቁት።

በተጨማሪም ለወንጀሉ ማስፈፀሚያነት የዋሉ አንድ ማካሮቭ እና አንድ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያዎች ከነተሽከርካሪው መያዛቸውን ገልጸዋል።

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንግስት ተቋማት ለስራ የተመደቡላቸውን ተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ሊያደርጉ እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለፍርድ ቤት ለማቅረብ የሚያስችል ጥብቅ የምርመራ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።

ሰርጎ ገብነትንና ልዩ ልዩ ወንጀሎችን በመቆጣጠር የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የመተማ ከተማ ፖሊስ ገለፀ።በምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የመተማ ከተማ አስተዳ...
04/09/2026

ሰርጎ ገብነትንና ልዩ ልዩ ወንጀሎችን በመቆጣጠር የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የመተማ ከተማ ፖሊስ ገለፀ።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የመተማ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ሚናን እየተወጣ እንደሚገኝ የፖሊስ አዛዡ ኢንስፔክተር ዳምጠው ሞላ ተናግረዋል።

ኢንስፔክተር ዳምጠው ሞላ እንዳሉት ከተማዋ ከሱዳን ጋር አዋሳኝ በመሆኗ የተለያዩ ህገወጥ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች እና የሰዎች ዝውውር፣ ህገወጥ የጦር መሳሪያ እና ተተኳሽ ዝውውር እንዲሁም የሰርጎ ገብነት ወንጀሎች በእጂጉ የሚስተዋልበት ነው ብለዋል።

እነዚህን የወንጀል ተግባራት በመከላከልና በመቆጣጠር ለከተማዋ ሰላም መስፈን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በጋራ በመሆን ውጤታማ ስራ መስራቱን ነው አዛዡ የተናገሩት።

አዛዡ አክለውም ከወንጀል ምርመራ ጋር በተያያዘ ባለፈው በጀት ዓመት ከ90 በላይ የክስ መዝገቦች ላይ አስፈላጊው የምርመራ ስራ ተሰርቶ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ተልኳል ሲሉ ጠቁመዋል።

በከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የወንጀል መከላከል ክፍል ኀላፊ ኢንስፔክተር አብዮት ጎሹ በበኩላቸው ወንጀሎችን በመከላከል የከተማዋን ሰላም ለማስፈን ማህበረሰቡን ያሳተፈ የወንጀል መከላከል ስራ እየተሰራ ነው።

በተሰሩ ጠንካራ የወንጀል መከላከል ስራም የእገታ፣ ስርቆት፣ ግድያ፣ ሰርጎ-ገብነት፣ የህገወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውር ወንጀሎች መቀነሳቸውንም ነው ኢንስፔክተሩ ያመላከቱት።

የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ የሰው ሀብት ልማትን በማጠናከ፣ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና አቅሙን ለመገንባት የሚያስችለውን ዕቅድ ማጽደቁን ገለፀ።የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ...
03/09/2026

የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ የሰው ሀብት ልማትን በማጠናከ፣ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና አቅሙን ለመገንባት የሚያስችለውን ዕቅድ ማጽደቁን ገለፀ።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ ከክልልና ከዞን የአስተዳደርና ልማት አመራሮች እና አባላት ጋር በበይነ-መረብ (ኦንላይን) የታገዘ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅና የስምምነት ሰነድ ፊርማ አካሄደ።

ዕቅዱን ያቀረቡት ምክትል ኮማንደር መላኩ ገድፈው የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ ረዳት መኮንን እንደገለጹት የተጀመሩ የፖሊስ ሪፎርም ስራዎችን ማስቀጠልና ማስፋፋት፣ የመለዮ ለባሽና የሲቪል የሰው ሀብት አስተዳደርን ማዘመን፣ የሰው ኃይል ምልመላ፣ ልማትና አቅም ግንባታን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

የፋይናንስ፣ ንብረት፣ ሎጂስቲክስና ጠቅላላ አገልግሎትን ማሳደግ፣ የጤናና ሕክምና አገልግሎትን ማሻሻል እና የቴክኖሎጂና ዲጂታል መረጃ አስተዳደርን ማስፋፋት የሚሉ በበጀት ዓመቱ ትኩረት የሚሰጣቸው ዋና ዋና ግቦች መሆናቸውን ምክትል ኮማንደር መላኩ አክለው አብራርተዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል እና የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሸነር አያልነህ ተስፋዬ ባደረጉት ንግግር የፖሊስ ተቋም የክልሉን ህዝብ ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ፣ ወንጀልን የመከላከልና የመመርመር እንዲሁም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ትልቅ ሀገራዊና ተቋማዊ ተልዕኮ አለበት ብለዋል።

ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራሉ አክለውም ይህንን ታላቅ ተልዕኮ በብቃትና በስኬት ለማሳካት የወቅቱን የጸጥታ ሁኔታ ያገናዘበ ህጋዊ ማዕቀፍ፣ ዘመናዊ አደረጃጀት፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሎጂስቲክስና በሙያ ብቃት የተገነባ የሰው ኃይል ወሳኝ ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ያጋጠሙ ክፍተቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ እና የተቋሙን የ2027 ስትራቴጂካዊ ራዕይ ለማሳካት ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል እና የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሸነር አያልነህ ተስፋዬ አብራርተዋል።

የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሸነር አብዮት ሽፈራው በበኩላቸው በተያዘው በጀት ዓመት ተቋሙ በሰው ሀብት ልማት ላይ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አስገንዝበዋል።

ረዳት ኮሚሸነር አብዮት በማብራሪያቸው “በተለይም የምልመላ ጥራትን ማሻሻልና አቅምን መገንባት ለፖሊስ ሰራዊቱ ውጤታማነት መሠረት በመሆኑ በልዩ ትኩረት እንሰራለን” ሲሉ ተናግረዋል።

በውይይቱ ወቅት የተሳተፉ አመራሮችና አባላት በበኩላቸው በዕቅዱ ላይ ያላቸውን አስተያየት የሰጡ ሲሆን፤ በተለይም የፖሊስ አባላትን ጥቅማ ጥቅም ከመጠበቅ፣ የሥራ አካባቢን ምቹ ከማድረግ እና ከአቅም ግንባታ አኳያ በበጀት ዓመቱ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየቶችና ማብራሪያ ለሚፈልጉ ጥያቄዎች በየደረጃው በሚገኙ የበላይ አመራሮች በኩል ተገቢ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ የተያዙትን ግቦች ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የጋራ ቁርጠኝነት በመያዝ እና የዕቅድ ርክክብና የስምምነት ሰነድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት በመፈጸም ውይይቱ ተጠናቋል።

ሶስት ሚሊዮን ብር የተጠየቀበት የህፃን ልጂ እገታ ወንጀል በፖሊስ ብርቱ ጥረት ከሸፈ።የአሰሪዎቿን ህፃን ልጅ በማገት ገንዘብ የጠየቀችው የቤት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር መዋሏን የጎንደር ከተማ ፖ...
03/09/2026

ሶስት ሚሊዮን ብር የተጠየቀበት የህፃን ልጂ እገታ ወንጀል በፖሊስ ብርቱ ጥረት ከሸፈ።

የአሰሪዎቿን ህፃን ልጅ በማገት ገንዘብ የጠየቀችው የቤት ሰራተኛ በቁጥጥር ስር መዋሏን የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ወጣት መቅደስ ሞገስ የተባለች የቤት ሰራተኛ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤት ሰራተኝነት ተቀጥር ከምትሰራበት ቤት ህፃን ፊዮና ሰለሞን የተባለች የሰባት ዓመት ህፃንን በማገት ወደ አማራ ክልል ጎንደር ከተማ አግታ በመውሰድ ከቤተሰቦቿ ገንዘብ ለመቀበል ስትሞክር በቁጥጥር ስር መዋሏን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አንተነህ ቴዎድሮስ ተናግረዋል።

እንደ ኮማንደር አንተነህ ገለፃ ግለሰቧ ህፃኗን ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር ከተማ በማምጣት በከተማዋ ማራኪ ክፍለ ከተማ ዩኒቨርሲቲ ጫካ ውስጥ በተደረገ ክትትል እና ጥቆማ መያዟን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዋ ለጊዜው በቁጥጥር ስር ካልዋለው ግርማ ወንድአሁን ከተባለ የአክስቷ ልጅ ጋር በመሆን ወንጀሉን በመፈፀም ለህፃኗ ቤተሰቦች ስልክ በመደወል 3 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ሲሆን ከ3 መቶ ሰባ ሺህ ብር በላይ መቀበላቸውንም ኮማንደሩ ተናግረዋል።

ፖሊስ ወንጀለኛውንና ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ብርቱ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝም አዛዡ ጠቁመዋል።

የሀገር ኩራት፣ የወገን መከታ፣ የጠላት ማርከሻ፣ የህዝብ ጋሻ!!ከሀገር ፍቅር ከመነጨ ስሜት፣ ከወገን ሰላም መሻት ከተቀዳ ወኔ ከችግር ፊት እንደ ተራራ፣ ከህዝብ ፊት እንደ ጋሻ የቆመ ሰራዊት...
03/09/2026

የሀገር ኩራት፣ የወገን መከታ፣ የጠላት ማርከሻ፣ የህዝብ ጋሻ!!

ከሀገር ፍቅር ከመነጨ ስሜት፣ ከወገን ሰላም መሻት ከተቀዳ ወኔ ከችግር ፊት እንደ ተራራ፣ ከህዝብ ፊት እንደ ጋሻ የቆመ ሰራዊት! የክልሉ የደጀን ኃይል።

ጀግንነት በአፍ በሚነገር ትረካ ሳይሆን በተግባር በሚገለፅ በክቡር ዋጋ ይተመናል። ለሀገር ክብር፣ ለወገን ሰላም በሚሰጥ ታማኝ አገልግሎት ይገለፃል።

በየትኛውም የግዳጅ ቀጠና የተሰጠውን ኃላፊነት ከገባው ቃለ-መሀላ ጋር አጣጥሞ መፈፀም ደግሞ የዚህ ጀግና ወታደር ዋነኛ መገለጫ ነው። ለህዝብ ሲል ምቾቱን፣ ለሀገር ሲል ህይወቱን በመገበር በወርቃማ ብዕር ወርቃማ የልብ ብራና ላይ ወርቃማ ታሪክን ይከትባል።

ሀገራችን በየዘመኑ ከሚገጥሟት ውስጣዊ እና ውጫዊ የፀጥታ ችግሮች የተፈጠሩ እና በትውልድ ቅብብሎሽ የፀናች ሀገርን የሚያስቀጥሉ፣ በፈተናዎች ፀንተው እና በችግሮች ተፈትነው ያለፉ አያሌ ጀግኖች ዛሬም ድረስ ይገኛሉ።

ባለፉት ዓመታት በአማራ ክልል የተፈጠረው የፀጥታ ችግር በብዙ ዘርፎች ማህበረሰቡን ፋታ የለሽ መከራዎችን እንዲያስተናግድ አድርገውታል። ይሁን እንጂ ይህን የህዝብ መከራ ለመቀልበስ የክልሉ የፀጥታ መዋቅ በርካታ መስዕዋትነት እየከፈለ ቆይቷል፤ እየከፈለም ይገኛል።

የክልሉን ሰላም የበለጠ ለማስፈንንና የፀረ-ሰላም ሀይሎችን የጥፋት ተልዕኮ በማክሸፍ ሀገርንና ህዝብን ለማገልገል ከተለያዩ የፀጥታ አካላትና መደቦች ተውጣጥተው ዋጋ እየከፈሉ ከሚገኙ የደጀን ሀይል የፀጥታ መዋቅርን ሚና ከሰራዊቱ አመራርና አባላት ጋር ቆይታ አድርገን እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል።

በቆይታችን በምዕራብ ጎንደር ዞን ኮኪት ከተማ ዙሪያ ከሚገኘውና የተሰጠውን ህዝብና ሀገር የመጠበቅ ግዳጁን እየተወጣ የሚገኘውን የ2ኛ ሻለቃ 2ኛ ሻምበል የደጀን ሀይል የግዳጅ አፈፃፀምን ተመልክተናል።

የሻለቃው ምክትል አዛዥ ኢንስፔክተር ሙላት ላቅያለው እንደሚሉት የደጀን ሀይሉ ከዞኑ ፖሊስ፣ ሰላም አስከባሪና ሚሊሻ አመራሮችና አባላት የተውጣጣ ሀይል መሆኑን በመጠቆም የተሰጠውን ህዝብን የመጠበቅ ግዳጅ በብቃት እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

እንደ ኢንስፔክተር ሙላት ገለፃ የደጀን ሀይሉ በብዙ መንገድ የውጊያ ብቃትን፣ ወታደራዊ ስነ-ስርዓትን ጠንቅቆ የሚያውቅና በሀገር ፍቅር ስሜት የተገነባ ስነ-ልቦናን የተላበሰ በመሆኑ ግዳጁን በስኬት ለመወጣት ዝግጁ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የክልላችን ብሎም የሀገራችን ሰላም እስኪሰፍን ድረስ የምንከፍለውን መስዕዋትነት አጠናክረን እናስቀጥላለን ሲሉም ምክትል አዛዡ ጠቁመዋል።

የሰራዊቱ አባላት በበኩላቸው ለሀገር ሰላምና ለህዝባችን ደህንነት ስንል ቤት ንብረቴ ሳንል፣ ቤተሰብ ሳያሳስበን፣ ጫካው መኖሪያዬ ምሽጉ መጠለያዬ ብለን ተግባራችን በቆራጥነት እየተወጣን ነው ብለዋል።

አባላቱ እንደሚሉት ላኪ እና ተላላኪ ፀረ-ሰላም ሀይሎች የሀገራችንን ክብርና የህዝባችንን ሰላም ለማወክ እያደረጉት ያለውን ከንቱ ምኞት ለማክሸፍ ቁርጠኛ ነን ሲሉ አረጋግጠዋል።

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የ2018 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ አካሄደ።የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻ...
02/09/2026

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የ2018 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ አካሄደ።

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሄደ።

በምክክር መድረኩ ላይ የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም፣ የአማራ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው፣ የፍትሕ ቢሮ አመራሮች፣ የዞን ፍትሕ መምሪያ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ቢሮው በአዋጅ ቁጥር 300/2017 አንቀጽ 36 በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን የማስከበር፣ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የመጠበቅ እንዲሁም የመንግሥትንና የሕዝብን ጥቅም የማስጠበቅ ተግባራትን በስፋት ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል።

በመድረኩ የውይይት መነሻ ሪፖርት በፍትሕ ቢሮ የዕቅድና በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አብራራው ምሕረት የቀረበ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ስኬቶች ተዳስሰዋል።

በፍትሕ ቢሮ፣ ፍርድ ቤት፣ ፖሊስ እና ማረሚያ ቤት መካከል ወጥ የሆነ የመረጃ ቅብብሎሽ እንዲኖር መረጃን ወደ አንድ ቋት የመሰብሰብ ሥራ መከናወኑ፤ ለበርካታ ዜጎች የንቃተ-ሕግ ትምህርት መሰጠቱ፤ የሥነ-ምግባር ጉድለት የታየባቸውን ፈጻሚዎች ተጠያቂ የማድረግ ሥራ መሠራቱ ተገልጿል።

በጦርነት የተጎዱ የፍትሕ ተቋማትን መልሶ የማቋቋም ሥራ የተከናወነ መሆኑ በተጨማሪም የቢሮውን ሕንፃ የማደስ ሥራ እየተሠራ መሆኑ በ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መሆናቸውም በሪፖርቱ ተመላክቷል።

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም በመድረኩ ባደረጉት ንግግር በ2018 በጀት ዓመት የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና የተቋሙን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ የተከናወኑት ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።

አቶ ብርሃኑ አክለውም ፍትሕ የመስጠት ሒደት የአንድ ተቋም ብቻ ሥራ ባለመሆኑ በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የውስጥና የውጭ ቅንጅታዊ አሠራር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና በተለይም የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥና የተገልጋዩን ማኅበረሰብ እርካታ ማሳደግ ዋነኛ ትኩረት እንደሚሆን አስረድተዋል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የአማራ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል ታደሰ አያሌው በበኩላቸው ከፍትሕ ቢሮ ጋር በወንጀል ጉዳዮች ዙሪያ የተፈረመው የጋራ መግባቢያ ሰነድ በወንጀል ምርመራ ሒደት ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመፍታት በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል ታደሰ አክለውም የወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱን ውጤታማነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ የፍትሕ ባለሙያዎችንና የፖሊስ መርማሪዎችን ሙያዊ አቅም በጥናት ላይ ተመስርቶ በጋራ የመገንባት ሥራ በቀጣይነት መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የስብሰባው ተሳታፊዎች በ2018 ዓ.ም የነበረው ቅንጅታዊ አሠራር መልካም እንደነበር ጠቁመው በቀጣይም የፍትሕ ባለሙያዎችና የምርመራ አካላት የጋራ አቅም ግንባታ ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የጠራ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ማከናወን፤ በበጀት ዓመቱ የታዩ ችግሮች ለይቶ መፍትሔ መውሰድ፤ የውስጥና የውጭ ቅንጅታዊ አሠራርን ይበልጥ ማጠናከር፤ ዐበይት ጉዳዮችን በጥናትና በሰነድ ለይቶ ውጤታማ ሥራዎችን መሥራት፤ የተጠናከረ የዘርፍ ድጋፍና ክትትል ማድረግ፤ የአቅም ግንባታና የሥነ-ምግባር ማነፅ ሥራዎችን ማጠናከር፤ የተጠያቂነት ሥርዓትን ማረጋገጥ የሚሉ በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸው ተመላክተዋል።

በመጨረሻም መድረኩ በቀጣይ በጀት ዓመት ለሚከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች፣ ለጥናትና ምርምር፣ ለሙያዊ ሥነ-ምግባር ግንባታና ለተጠያቂነት ሥርዓት መረጋገጥ የጋራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹም የቢሮውን የእድሳት ሒደት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የሠላም  አማራጭን  የተቀበሉ ህገ-ወጥ ታጣቂዎች እጅ ሰጡ። በሰሜን ጎንደር ዞን አዲአርቃይ ወረዳ አንጓ አከባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የህገ-ወጥ ታጣቂው ቡድን አባላት እጅ መሥጠታቸው ተገለጸ።በ...
02/09/2026

የሠላም አማራጭን የተቀበሉ ህገ-ወጥ ታጣቂዎች እጅ ሰጡ።

በሰሜን ጎንደር ዞን አዲአርቃይ ወረዳ አንጓ አከባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የህገ-ወጥ ታጣቂው ቡድን አባላት
እጅ መሥጠታቸው ተገለጸ።

በ10ኛ ዕዝ የመብረቅ ክፍለጦር አዛዥ ኮሎኔል ስንታየሁ ሰይድ እንዳሉት በሰሜን ጎንደር ዞን አዳርቃይ ወረዳ አንጓ አካባቢ ሰላምን በማወክ የአካባቢው ስጋት የነበሩ የህገ-ወጥ ቡድኑ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለው ለሠራዊቱ እጅ መስጠታቸውን ተናግረዋል።

በአካባቢው ሠላምን ለማሥፈን እና አላሥፈላጊ አካሄዶች መቆም አለባቸው ብሎ በማሠብ ታጣቂዎች ወደ ሰላም እንዲገቡ በተደረገው ጥረት ቁጥራቸው 12 የሆኑ ታጣቂዎች ከነሙሉ ትጥቃቸው ሠላምን መርጠው ገብተዋል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ አመራሮችና አባላት ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ አዲስ የትምህርት ዘመን መጀመርን አስመልክቶ ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የሚደረገውን...
01/09/2026

የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ አመራሮችና አባላት ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ

አዲስ የትምህርት ዘመን መጀመርን አስመልክቶ ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የሚደረገውን ድጋፍ ለማጠናከር፣ የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ አመራሮች፣ የወረዳ ፖሊስ አዛዦች እና አባላት በራሳቸው ፈቃድ ገንዘብ በማዋጣት የደብተር እና እስክሪፕቶ ቁሳቁስ ድጋፍ አከናውነዋል።

ድጋፉ ትናንት በተከናወነው ዓመታዊ የዕቅድ ትውውቅ መድረክ ላይ የተሰበሰበ ሲሆን፣ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አመራሮች፣ የወረዳ ፖሊስ አዛዦችና አባላት ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ባላቸው ቁርጠኝነት የተከናወነ የበጎ አድራጎት ተግባር ነው።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ተሾመ ብዙ እንደገለጹት፣ የፖሊስ ሰራዊቱ የህዝብን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ዋና ተግባሩ ቢሆንም ለአቅመ ደካማ ወገኖችና ለወደፊት ሀገር ተረካቢ ተማሪዎች አጋርነት ማሳየት የዘወትር ባህሉ መሆኑን ጠቁመዋል።

አዛዡ አክለውም ድጋፉ ተማሪዎች ያለምንም የስነ-ልቦና እና የቁሳቁስ ጫና ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ ለማስቻል የተደረገ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የተዘጋጀውን የትምህርት ቁሳቁስ ከዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ከኮማንደር ተሾመ ብዙ እጅ የተረከቡት የምዕራብ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ የስጋት ደሴ፣ ለተደረገው መልካም እና አርአያነት ያለው ተግባር የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

አቶ የስጋት ደሴ እንደተናገሩት፣ የፖሊስ መምሪያው አመራሮችና አባላት ያደረጉት ይህ በጎ አድራጎት ለሌሎች ተቋማት ትልቅ አርአያ የሚሆንና የተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ የሚያጎለብት ነው ብለዋል።

ወንጀልን አምርሮ የሚጠላ ማህበረሰብ የተፈጠረባት፤ የአብሮነትና የሰላም ማሳያ፣ የነጭ ወርቅ ምድር ውብ ከተማ!የምዕራብ ጎንደር ዞን መቀመጫ የሆነችው ገንዳውሃ ከተማ ሰላሟን አጠናክራ በማስቀጠ...
01/09/2026

ወንጀልን አምርሮ የሚጠላ ማህበረሰብ የተፈጠረባት፤ የአብሮነትና የሰላም ማሳያ፣ የነጭ ወርቅ ምድር ውብ ከተማ!

የምዕራብ ጎንደር ዞን መቀመጫ የሆነችው ገንዳውሃ ከተማ ሰላሟን አጠናክራ በማስቀጠልና ልማቷን በማሳለጥ ላይ ትገኛለች።

አሁን ላለችበት አንፃራዊ ሰላም የከተማዋ ማህበረሰብ፣ ፖሊስ እና ሌሎች የፀጥታ አካላት በማህበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከል አሰራር ላይ ትኩረት ያደረገ የጋራ ጥረት መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች እና የፖሊስ አካላት ይመሰክራሉ።

የገንዳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር ኃይሌ ብርሃኑ እንደሚሉት በከተማዋ የሚፈጠሩ ልዩ ልዩ ወንጀሎችን በመከላከል ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ከሚሊሻ፣ ሰላም አስከባሪ እና ሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የከተማዋን ሰላም የማስጠበቅ ስራ የዕለት ከዕለት ተግባራቸው መሆኑንም ነው ኀላፊው የጠቆሙት።

እንደ ኢንስፔክተር ሃይሌ ገለፃ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት በተደረገ የወንጀል መከላከል ስራ የእገታ፣ የህገወጥ ጦር መሳሪያ ዝውው፣ የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀሎች መቀነስ ተችሏል ነው ያሉት።

ባለፈው በጀት ዓመት በወንጀል ምርመራ፣ በትራፊክ ቁጥጥር ስራና በህግ ማስከበር ተግባር የከተማዋ ፖሊስ ከፍተኛ ስራ መስራቱንም ኃላፊው ጠቁመዋል።

በከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ክፍል ኀላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ባበይ ጨቅሉ እንደተናገሩት የከተማዋን ማህበረሰብ ተሳታፊ እና ባለቤት ያደረገ የወንጀል መከላከል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ማህበረሰቡ ለፖሊስ መረጃ ከመስጠትና ተባባሪ ከመሆን ባለፈ አካባቢውን በንቃት በመጠበቅ ወንጀልን አምርሮ የሚጠላ ሆኗል ነው ያሉት ክፍል ኃላፊው።

በበጀት ዓመቱም በርካታ ህገወጥ ተተኳሾች፣ መሳሪያዎች እና የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውንም ረዳት ኢንስፔክተር ባበይ ጨቅሉ ጠቁመዋል።

አቶ ነጋ ሀይሌ የከተማዋ ነዋሪ በበኩላቸው ሰላም በጋራ ጥረት የሚረጋገጥ የጋራ ሀብት በመሆኑ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመሆን እና የተለያዩ አደረጃጀቶን በማዋቀር የከተማችንን ሰላም እየጠበቅን እንገኛለን ብለዋል።

በምሽት አካባቢያቸውን ሲጠብቁ ከነበሩት የማህበረሰብ ክፍሎች መካከል ወይዘሮ ዘዋል ባዬ እና ወጣት ሲሳይ ጌታነህ እንደተናገሩት ከራስ ተነሳሽነት በመነጨ እና በከተማዋ ፖሊስ አደራጅነት እና አስተባባሪነት የወንጀል መከላከል ስራን እየሰራን ነው ብለዋል።

ከከተማዋ ፖሊስ ጋር በጋራ በተሰሩ የሰፈር ጥበቃ፣ የወንጀል መከላከል ስራም ከዚህ በፊት ይከሰቱ የነበሩ የእገታ፣ የዝርፊያ፣ የንጥቂያና የህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ወንጀሎች መቀነሳቸውን በመጠቆም ተግባሩን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉም አመላክተዋል።

Address

Police Commission
Bahir Dar
244

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Region Police posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Region Police:

Shortcuts

Share