Amhara Prosperity Party /APP/

Amhara Prosperity Party /APP/ "የጎርጎራ ቃልኪዳናችን፤ ለዘላቂ ሰላምና ለሁለንተናዊ ብልጽግናችን"
•~•~•
ቴሌግራም ▶https://t.me/amharaapp

06/06/2026
05/06/2026
"ሚሊሻው የሕዝባዊነትን ትርጉም በተግባር ያሳየ ኃይል ነው" ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ  የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ግንቦት 29/2018 ዓ.ም በክልል ደረጃ የሚካሄደውን የሚሊሻ 30ኛ ዓመት ...
05/06/2026

"ሚሊሻው የሕዝባዊነትን ትርጉም በተግባር ያሳየ ኃይል ነው" ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ

የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ግንቦት 29/2018 ዓ.ም በክልል ደረጃ የሚካሄደውን የሚሊሻ 30ኛ ዓመት የምሥርታ በዓል እና የእውቅና መርሐ ግብር አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ የሚሊሻ 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል የሚሊሻውን ታሪካዊ ተጋድሎ እና መስዋዕትነቱን ለመዘከር የታሰበ ነው ብለዋል።

በዓሉ ለሚሊሻ አባላት እና ለቤተሰቦቻቸው ክብር እና ምስጋና ለማቅረብ፤ ተቋማዊ ሪፎርም እና ዝግጁነቱን ለማረጋገጥ፤ የሕዝቡን እና የሚሊሻውን ትስስር ለማጥበቅ እና ሌሎች ዋና ዋና ዓላማዎች እንዳሉትም አንስተዋል።

ግንቦት 29/2018 ዓ.ም የአማራ ክልል ሚሊሻ የ30 ዓመታት የጀግንነት እና የሕዝባዊነት ጉዞ የሚከበርበት ልዩ ቀን እንደኾነም ገልጸዋል።

የሚሊሻ 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል ሲባል የሚሊሻ ምስረታ ዕድሜው 30 ዓመት ነው ለማለት ሳይኾን በክልል ደረጃ የተቋቋመበትን ለመግለጽ እንደኾነም ተናግረዋል። ሚሊሻ ከንጉሠ ነገሥቱ ዘመን ጀምሮ ዘመናዊ ወታዳር ባልነበረት ወቅትም ነበር ብለዋል።

ባለፉት ሦሥት አስርት ዓመታት የክልሉ ሚሊሻ በርካታ ታሪካዊ ምዕራፎችን ማለፉንም ገልጸዋል።

ሚሊሻው መደበኛ የሥራ ድርሻውን ሳያስተጓጉል በአንድ እጁ አምራች በሌላ እጁ ደግሞ የሰላም ዘብ በመኾን "የሕዝባዊነትን ትርጉም በተግባር ያሳየ ኃይል ነው" ብለዋል።

ሀገራዊ የሉዓላዊነት ፈተናዎች እና ክልላዊ የጸጥታ ስጋቶች ባጋጠሙ ጊዜያት ሚሊሻው ከመከላከያ ሠራዊት እና ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመሰለፍ በደም እና በአጥንቱ ደማቅ ታሪክ መጻፉን ገልጸዋል።

በክልሉ አንጻራዊ ሰላም እንዲመጣ የበኩሉን ሚና ተጫውቷልም ብለዋል፡፡

ኮሚሽኑ ይህንን 30ኛ ዓመት በዓል ሲያከብር ወደፊት የክልሉን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ማስከበር እና የሰላም ጥሪ ተግባራት ላይ በትኩረት ለመሥራት ታሳቢ አድርጓል ነው ያሉት ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

ወረታ ከተማን የማልማት ሥራ እየተሠራ ነው።የአማራ ክልል የሥራ ኀላፊዎች በደቡብ ጎንደር ዞን የወረታ ከተማ አሥተዳደር የልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።የወረታ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ጌትነ...
04/06/2026

ወረታ ከተማን የማልማት ሥራ እየተሠራ ነው።

የአማራ ክልል የሥራ ኀላፊዎች በደቡብ ጎንደር ዞን የወረታ ከተማ አሥተዳደር የልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።

የወረታ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ጌትነት ፈረደ ከተማዋ የብዙ አካባቢዎች ተሽከርካሪዎች መተላለፊያ እንደመኾኗ በየጊዜው የመንገድ ጥገና፣ የውኃ ማፋሰሻ ዲች እና መሰል ልማቶችን በመገንባት ከተማዋን ለነዋሪዎች እና ለተጓዦች ምቹ ለማድረግ እየተሠራ መኾኑን ገልጸዋል።

ከተማዋን በሚፈለገው ልክ ለማልማት የጸጥታ ችግሩ እንቅፋት ኾኖ መቆየቱን አንስተዋል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ጥላሁን ደጀኔ ወረታ ከተማ በዞኑ ከፍተኛ የንግድ እና የልማት እንቅስቃሴ ያለበት ከተማ መኾኗን ተናግረዋል።

ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ማኅበረሰባዊ እና አካባቢያዊ አቅሞችን በመጠቀም ከተማውን ለማልማት ጥረት ይደረጋል ብለዋል።

የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኀላፊ ኢብራሂም ሙሐመድ (ዶ.ር) ወረታ ከተማ የንግድ እንቅስቃሴ መተላለፊያ በመኾኗ ማልማት ያስፈልጋል ነው ያሉት።
ዋናውን የአስፋልት መንገድ በግራ እና በቀኝ መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ኀላፊ ሲሣይ ዳምጤ ወረታ ከተማ ለልማት ምቹ መኾኗን ጠቅሰዋል። በቁርጠኝነት ማልማት፣ ማስዋብ እና ጽዱ ማድረግ ከከተማ አሥተዳደሩ እና ከነዋሪዎች ይጠበቃል ብለዋል።

ለዚህም ማኅበረሰቡ በበጀት መደገፍ እና የአካባቢውን ሰላም ማረጋገጥ አለበት ነው ያሉት።

🌱 የአፈር ማዳበሪያ ችግር እንዳያጋጥም በትኩረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።በአማራ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በማረስ ...
04/06/2026

🌱 የአፈር ማዳበሪያ ችግር እንዳያጋጥም በትኩረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በአማራ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በማረስ ከ205 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ሰብል ለማምረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኀላፊ አጀበ ስንሻው ለአሚኮ ገልጸዋል።

ዕቅዱን ለማሳካት ደግሞ የአፈር ማዳበሪያ እና የምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ በትኩረት እየተሠራ እንደኾነ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

🌱🚜 ክልሉ በዚህ ዓመት፦

🚜 8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ ለማስገባት አቅዷል። ከዚህ ውስጥ 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የሚኾነው የክልሉ የአፈር ማዳበሪያ ዕቅድ ወደብ ላይ ደርሷል።

🚜 3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል የሚኾነው የአፈር ማዳበሪያ ደግሞ ወደ ክልሉ ተጓጉዞ ደርሷል። ከባለፈው ዓመት ተርፎ የነበረ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት ክልሉ ውስጥ መኖሩን አንስተዋል።

በጥቅል 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ለሥርጭት ቀርቧል። እስከ አሁን ባለው ጊዜም አርሶአደሮች ገዝተው የወሰዱት እና የተሠራጨው 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንደኾነ ተናግረዋል።

ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ነው የገለጹት። ለስርጭት የቀረበው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ቀድመው ከሚዘሩ ሰብሎች አኳያ በጥሩ የሚታይ እንደኾነም አንስተዋል።

🌱 በሌላ በኩል፦
220 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች ለማቅረብ ታቅዷል።
እስከ አሁን ባለው ጊዜ 208 ሺህ ኩንታል የሰብል ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ድልድል ተደርጓል።

72 ሺህ ኩንታል የሚኾነው የሰብል ምርጥ ዘርም ተሠራጭቷል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትየኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ ...
03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ የተሰማውን ደስታ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፀጥታ ኃይል አካላት እንዲሁም ሕዝቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተወጡት ሀገራዊ ኃላፊነት እና ላሳዩት ፅናትም ምክር ቤቱ ያለውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጿል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው፣ “ልዩነቶቻችንን እና ችግሮቻችንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመፈታት በምርጫው የታየውን ሰላም በማስቀጠል የበኩላችንን ሚና እንወጣ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ እንቁም” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

ሕዝቡ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነቱን በተግባር አረጋግጧል!ግንቦት 24/2018 ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከ ጫፍ በመውጣት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አዲስ ታሪክ ፅፈዋል። ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ...
03/06/2026

ሕዝቡ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነቱን በተግባር አረጋግጧል!

ግንቦት 24/2018 ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከ ጫፍ በመውጣት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አዲስ ታሪክ ፅፈዋል። ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ የሀገሪቱን የዲሞክራሲ ጉዞ ለማፅናትና ለማስቀጠል ያለውን ፅኑ ፍላጎት በግልፅ ያሳየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኖ ይመዘገባል። ሕዝቡ የምርጫ ካርዱን በጥንቃቄ አስቀምጦ በመያዝ በምርጫዉ እለት ድምፅ በመስጠት ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነቱን በተግባር አረጋግጧል።

የፖለቲካ ሥልጣን ምንጭ ሕዝብ ብቻ መሆኑንም ዳግም ለመላው ዓለም በማሳየት፣ ኢትዮጵያን ከፍ ማድረግ ተችሏል። በዚህ ታሪካዊ ሂደት ውስጥ ዋነኛውና ብቸኛው አሸናፊ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ናቸው። መራጩ ሕዝብ ሳይሰለች ከነጋት 10:00 ሰአት ጀምሮ ረጅም ሰልፎችን በመያዝ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ድምፁን የሰጠው የፓርቲዎችን ድል ለመወሰን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ክብር ከፍ ለማድረግ ነው። እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እድሜ ጠገብ አዛዉንቶች፣ ሙሽሮች ሳይቀሩ በነቂስ ወጥተው ዲሞክራሲን ለማፅናት ያሳዩት ትዕግስት የኢትዮጵያን ብሔራዊ አንድነትና ጥንካሬ ለዓለም ያሳየ ታላቅ የድል ምዕራፍ ነው።

የዘንድሮው የምርጫ ሂደት ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ፣ ስልጡን እና ፍፁም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ ለሀገራችን ትልቅ የሞራል ድል ሲሆን ሕዝቡ ያሳየው የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል፣ መቻቻልና እርስ በርስ የመከባበር እሴት ኢትዮጵያን ሊከፋፍሉና ሊያዳክሙ ለሚፈልጉ ሀይሎች ሁሉ ግልጽ ምላሽ የሰጠ ታሪካዊ ድል ነው። ይህ ስልጡን የዲሞክራሲ ልምምድ አካሄድ ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ረገድ የደረሰችበትን ጀረጃ በተግባር ያሳየና የሀገሪቱን ገጽታ በዓለም መድረክ ከፍ ያደረገ ልዩ ክስተት ነው።

ይህ ምርጫ ለአዲሲቷና ለበለፀገችው ኢትዮጵያ ጠንካራ መሰረት በመጣል ለነገዋ የበለፀገችና የተረጋጋች ሀገር ጠንካራ መሰረት የጣለ ታላቅ የስኬት ምዕራፍ ነው። 7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የልዩነት ሳይሆን የኅብረት፣ የብጥብጥ ሳይሆን የሰላም መገለጫ በመሆኑ የሀገሪቱን የነገ ተስፋ ብሩህ አድርጎታል።

በመጨረሻም በተለያዩ ጫናዎች እና ፈተናዎች ሳይበገሩ ድምፄ ዋጋ አለዉ በማለት በታላቅ ሀገራዊ ክብር ፀንተዉ በመቆም በትዕግስት እስከ ሌሊት ተሰልፈው ድምፃቸውን ለሰጡ እና የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ታላቅነት በተግባር ላገዘፉ ዜጎች ሁሉ ታላቅ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል።

ኢትዮጵያ መርጣለች!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ታሸንፋለች!



#ኢትዮጵያንወደተምሳሌትሀገር

🌴 የባሕር ዳር የኮሪደር እና የጣና ዳር ልማት የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ነው 🌴 በባሕር ዳር ከተማ በከፍተኛ ፍጥነት እና ጥራት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር እና የጣና ዳር ልማት ፕሮጀክት...
03/06/2026

🌴 የባሕር ዳር የኮሪደር እና የጣና ዳር ልማት የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ነው 🌴

በባሕር ዳር ከተማ በከፍተኛ ፍጥነት እና ጥራት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር እና የጣና ዳር ልማት ፕሮጀክት፤ ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለቱሪስቶች ደግሞ ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል።

የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ዋና ዋና ስኬቶች እና ፋይዳዎች፦

🔹የቱሪዝም መነቃቃት፦ የዐይን ማረፊያ የኾኑ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የጣና ዳርቻ ዘመናዊ መንገዶች፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መስመሮች የጎብኚዎችን ቆይታ ያራዝማሉ።
የዘንባባ ፓርክም ሙሉ በሙሉ ሳቢ ኾኖ ተጠናቅቋል።

🔹ውበት እና ደኅንነት፦ ለአረንጓዴ ልማት የተሰጠው ትኩረት ከተማዋን ውብ እና ንጹሕ ከማድረጉ ባለፈ፣ የዘመናዊ መንገድ መብራቶች መገጠማቸው የምሽት እንቅስቃሴን እና ደኅንነትን አሳድጓል።

🔹የኢኮኖሚ ዕድገት፦ የቱሪስት ፍሰቱ መጨመር ለሆቴሎች፣ ለትራንስፖርት እና ለአካባቢው ነጋዴዎች ሰፊ የሥራ ዕድል እና ከፍተኛ ገቢ እየፈጠረ ይገኛል።

🔹"የባሕር ዳር ኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ ለትውልድ የሚተርፍ አሻራም ነው።

አሚኮ


#ኢትዮጵያንወደተምሳሌትሀገር

03/06/2026

ኢትዮጵያውያን ሊኮሩ ይገባል - የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን

"Today is a day the people of Ethiopia should be proud" - AU Mission Commends Ethiopia's Electoral Process

03/06/2026

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Prosperity Party /APP/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share