Amhara Finance Bureau

Amhara Finance Bureau Bureau of Finance (BoF) is one of the Bureaus under Amhara National Regi

The Amhara National Regional State Bureau of Finance & Economic Cooperation (BoFEC) has established to enhance maximum development of the Amhara Region.

27/05/2026
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በመከታተል እና በመደገፍ ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸየማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ...
23/05/2026

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በመከታተል እና በመደገፍ ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ የመንግስትንና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል።

በዕለቱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ፥ የልማት ድርጅቶች በዞኑ ዘርፈብዙ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የህብረተቡን ችግሮች ለመፍታት የሚያከናውኗቸውን የልማት ተግባራት በሚገባ መከታተል እና መደገፍ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

በዞኑ የተያዙ የልማት እቅዶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የጋራ ርብርብ ይጠይቃል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ባለድርሻ አካላት በእነዚሁ ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በመከታተል እና በመደገፍ ውጤታማ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል፡፡

የመንግስት እና የሲቪል ማህበራት ጥምረት የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መመለስና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማስፈን እንደሚያስችል ጠቁመው፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍ ሊጠናከር እንደሚገባም አክለዋል፡፡

የዞኑ ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ነጋ በበኩላቸው በተቋቋመው አዋጅ መሠረት ተግባራዊ ተደርጎ በየጊዜው የጋራ ግምገማ መደረጉን አንስተዋል።

በዞኑ በዘንድሮው በጀት ዓመት 26 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሁለት ነጥብ አንድ ቢሊዮን በሚጠጋ ብር 28 የልማት ፕሮጀክቶች እያከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

ጤና፣ ትምህርት፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ማስፋፋት እና የሴቶች እና ህጻናት ተጠቃሚነት ማጎልበት ድርጅቶቹ የዞኑን መንግስት ጥረት እየደገፉ ከሚገኙባቸው ዘርፎች መካከል እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡

በዞኑ ስምምነት ወስደው እየተቀሳቀሱ ከሚገኙ 26 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ 15ቱ አገር አቀፍ እና 11ዱ ደግሞ አለምአቀፍ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንደሆኑም ታውቋል።

በዚሁ የምክክር መድረክ የተለያዩ የዞኑ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመራር አባሎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሚዩኒኬሽን

21/05/2026

⚠️📢የተቋማችንን ስምና መለያ በመጠቀም ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስለ ስራ ግብር ቅናሽ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው፡፡

📌ስለተቋሙ ስራ ትክክለኛ መረጃዎችን የገንዘብ ሚኒስቴር የማህበራዊ ሚዲያ ገፆችን በመከተል ማግኘት ትችላለችሁ፡፡

 # የ1.2 ቢሊዮን ብር የፕሮጀክት ስምምነት ይፋ ሆነ ፡፡********************************የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ እና ወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢ...
18/05/2026

# የ1.2 ቢሊዮን ብር የፕሮጀክት ስምምነት ይፋ ሆነ ፡፡
********************************
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ እና ወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ተግባራዊ ለሚደረጉ 4 አዳዲስ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚሆን የ1.2 ቢሊዮን ብር የፕሮጀክት ስምምነት ፊርማ እና የማስጀመሪያ ስነ ስርዓት በባህርዳር ከተማ በብሉናይል አቫንቲ ሪዞርት ሆቴል ተፈጽሟል፡፡
በፕሮጀክት ፊርማ ስምምነቱ የተገኙት የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ አታላይ ጥላሁን ወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የአማራ ክልል በገጠመው ወቅታዊ ችግር የክልሉን ህዝብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቅረፍ ለክልሉ አጋርነትን ያሳዬ ትልቅ ድርጅት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የአማራ ክልል ሰፊ የቆዳ ስፋት ያለው፣ታታሪ እና ስራ ወዳድ ህዝብ መኖሩን የገለጹት ቢሮ ኃላፊው አቶ አታላይ ለዚህ የህብረተሰብ ክፍል የልማት ስራዎችን ለመተግበርና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም በእለት ደራሽ አደጋ ምላሽ ስራዎችን ለመተግበር ወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከክልሉ ጋር ላደረገው የ1.2 ቢሊዮን ብር የፕሮጀክት ስምምነት በቢሮውና በክልሉ ስም ምስጋቸውን አቅርበዋል፡፡
ወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የክልሉ አሻጋሪ የመንግስት የልማት አቅድ ውስጥ የራሱን ድርሻ ለመወጣት በ6 ዞኖችና በ16 ወረዳዎች ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግ የክልላችንን ህብረተሰብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመፍታት እየሰራ እንደሆነ የገለጹት አቶ አታላይ ጥላሁን የክልሉ ገንዘብ ቢሮ በወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ እና በአጋር አካላት መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ በማገልገል ይሰራል ብለዋል፡፡
ቢሮ ኃላፊው አክለውም ወርልድ ቪዥንም ሆነ ሌሎች የፕሮጀክቱ ፈጻሚ ተቋማት በተቀናጀ ድጋፍና አጋርነት የህብረተሰቡን ዘላቂ የልማት ውጤት በሚያረጋግጥ ሁኔታ በጋራ ልንሰራ ይገባል ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
የወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ምእራብ አማራ እና ምስራቅ አማራ አስተባባሪ አቶ ቴወድሮስ አባተ በበኩላቸው ወርልድ ቪዥን ላለፉት 40 ዓመታተት በላይ ከመንግስት እና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር ከድንገተኛ አደጋ ምላሽ ስራዎች ጀምሮ በርካታ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን ሲፈጽም ቆይቷል፤ እአሁንም እየፈጸመ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ወርልድ ቪዥን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ለቀጣይ 5 ዓመታት ስትራቴጅካዊ እቅድ አውጥቶ 15 ሚሊዮን የሚደርሱ ህጻናትን ተደራሽ ለማድረግ ከክልሉ መንግስት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ የፕሮጀክት ስምምነት ከክልሉ መንግስት ጋር ወስዶ እየሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ቴወድሮስ በዛሬው እለትም ለ4 ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚሆን 1.2 ቢሊዮን ብር ወይንም 7.6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ፕሮጀክት ስምምነት መደረጉን ገልጸዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በ3 ፕሮግራሞች የእለት ደራሽ አደጋ ምላሽ ስራዎች እና በ1 መደበኛ የልማት ፕሮግራም በ6 ዞኖችና በ16 ወረዳዎች ተግባራዊ የሚሆንና 860 ሽህ የህበረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የገለጹት አቶ ቴወድሮስ ከዚህ ውስጥ 121 ሽህ ያህሉ ህጻናት እንደሆኑ እና ሁሉም የወርልድቪዥን ፕሮጀክቶች ህጻናት ላይ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩ አያይዘው ገልጸዋል፡፤
የፕሮጀክት ስምምነቱ ሃብት የተገነው በአሜሪካ መንግስት እና በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ የተገኘ እንደሆነም አቶ ቴወድሮስ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

 #የፕሮግራሙን ሃብት እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም አጠናቆ ወደ ሚቀጥለው ዙር ለመግባት የጋራ መግባባት ተደርሷል//ገንዘብ ቢሮ   ********************************** የአ...
16/05/2026

#የፕሮግራሙን ሃብት እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም አጠናቆ ወደ ሚቀጥለው ዙር ለመግባት የጋራ መግባባት ተደርሷል//ገንዘብ ቢሮ
**********************************
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከኢፌድሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ከተውጣጡ የካልም ፕሮግራም ማስተባበሪያ ኃላፊዎችና የክልላችን የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ሴክተሮችና ዞኖች ጋር የመጀመሪያውን ዙር ማጠናቀቂያ ምክክር መድረክ / work shop/ፕሮግራም አካሄደ፡፡
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን የዘላቂ መሬት አያያዝና አጠቃቀም (ካልም) ፕሮግራም የልማት ክፍተቶቻችንን በመሙላትና በአጠቃላይ በክልሉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻችንን ለመፍታት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለ ሃብት መሆኑን በመግለጽ ይህንን ሃብት በወቅቱና ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል በማድረግ መስራት ይጠበቀብናል ያሉ ሲሆን የመጀመሪያውን ዙር ፕሮግራም በማጠናቀቅ ለቀጣይ 2ኛው ዙር ፕሮግራም ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከወዲሁ አስቦ በትጋትና በኃላፊነት መስራት ይገባል ብለዋል፡፡
ክልሉ የመጀመሪያውን ዙር የፕሮግራሙን መዝጊያ መድረክ / work shop/ፕሮግራም በሚያካሂድበት ወቅት የኢፌድሪ ገንዘብ ሚኒስቴር የቻናል አንድ ፕሮግራም የዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በመገኘት ላደረጋችሁልን ድጋፍና አጋርነት ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ ያሉት ቢሮ ኃላፊው አቶ አታላይ ቀጣይም የዚህን ፕሮግራም ጨምሮ ሌሎች ፕሮግራሞችንም ተገቢ ድጋፍና አጋርነታችሁን የበለጠ በማጠናከር በጋራ ለክልሉ ልማት ስራ ላይ የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ ዘንድ የተለመደ ትብብራችሁ እንዳይለየን ሲሉ አሳስበዋል፡፡
የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ መሰረት አዱኛ በበኩላቸው እኛ እንደ አማራ ክልል ማነኛውንም ሃብት በአግባቡ እና በወቅተ በመጠቀም እየሰራን እንገኛለን በማለት የካልም ፕሮግራምን ጨምሮ በሁሉም የቻናል 1 ፕሮግራሞች የመጣን ሃብት በውቅቱና ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በአግባቡ በመፈጸምና በማስፈጸም እየሰራን ነው፤ምናልባትም የፌደራል መንግስት የሚተርፍ ሃብት ካለው ለክልላችን ቢልክልን በቀጠይ ቀሪ ወራት ለክልላችን ህዝብ ተጨማሪ ልማት በመስራት ውጤት አምጠተን እናሳያለን ብለዋል፡፡
ይህ የካልም ፕሮግራም የበጀት እጥረቶቻችንን በመሸፈን የክልላችንን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻችንን እየፈታ መሆኑን የግለጹት ምክትል ቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ መሰረት የተመደበውን ሃብት ለታለመለት አላማ በማዋል ከሰኔ 30/2018 ዓ.ም መሻገር የለበትም ሲሉ አስታውቀዋል፡፤
በሌላ በኩል የካልም ፕሮግራም የመንግስትን ቁልፍ የልማት ፕሮግራሞች የሚተገበሩበት እንደሆነ የገለጹት በገንዘብ ቢሮ የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ ያየህ ፕሮግራሙ በ158 ወረዳዎች በአርሶ አደር የመሬት ካርታ ባለቤትነት፣በተፋሰስ ስራ፣ በእንስሳት እና ንብ እርባታና በመሳሰሉት ወደ 2 ሚሊዮን በላይ የክልሉን ህብረተሰብ ተጠቃሚ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
ፕሮግራሙ የ 7 ዓመት ቆይታ ጊዜውን ሰኔ 30/2018 በማጠናቀቅ በ2019 በጀት ዓመት ካልም 2 ፕሮግራም በአዲስ እንደሚጀምርም የምክክር መድረኩን ሲከፍቱ ተናግረዋል፡፡

የአማራ ክልል የካልም ፕሮግራም በዚህ መድረክ ባየነው አግባብ ውጤታማ የሚያደርግ አሰራርን በመከተል ሰኔ 30/2018 ዓ.ም አጠናቆ ለቀጣይ ዙር ዝግጅት በዚህ ሁኔታ መግባባት የተደረሰበትን ያደነቁት ደግሞ በኢፌድሪ ገንዘብ ሚኒስቴር የቻናል 1 ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ኃላፊ አቶ ሮቤል ሽፈራው ሲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ቀሪ ስራዎችን በመናበብና በጋራ ቅንጅት መስራት ይገባል ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

 #የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት የፊርማ ስምምነት ተደረገ****************************በአብክመ ገንዘብ ቢሮ እና በኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ዲስትሪክት መካከል የኢን...
14/05/2026

#የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት የፊርማ ስምምነት ተደረገ
****************************
በአብክመ ገንዘብ ቢሮ እና በኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ዲስትሪክት መካከል የኢንተርኔት ባንኪክግ አገልግሎት የፊርማ ስምምነት ሥነ ስርዓት ተካሄዷል፡፡

በፊርማ ስነ ስርዓቱ የተገኙት የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን ዲጂታል 2025 አጠናቀን ወደ 2030 እየገባን እንደሆነና በአገር አቀፍ ደረጃ በፋይናንስ አካታችነት በደጂታል ሲስተም እየተሰራና የፋይናንስን ተደራሽነት ከማረጋገጥ አንፃር ከፍተኛ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፤ ዜጐች አገልግሎት በቅርበትና በቀላሉ እንዲያገኙ ከማድረግና የመንግስትን አሰራር ውጤታማ እንዲሆን ዲጂታላይዝ የሆነ አሰራር መከተል አማራጭ የሌለው ወቅታዊ አሰራር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቢሮ ኃላፊው አቶ አታላይ አያይዘውም በክልላችንም ይህ አሰራር የተጀመረና በዛሬው እለት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ዲስትሪክት ጋር ያደረግነው ስምምነት ይፋ እንዲሆን ከማሳወቅ አንፃር መሆኑን ገልፀው የክልል ተቋማትም ለስራው አስፈላጊ የሰው ሃይልና ቁሳቁሶችን በማሟላት ወደስራ መግባት እንደሚገባቸው የገለፁ ሲሆን ገንዘብ ቢሮም የማስተባበሩንና የድጋፍ ስራም እንደሚያደርግ አሳውቀዋል፡፡

የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ባህር ዳር ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ደሞዜ ባልቢ ይህ ኢንተርኔት ባንኪንግ ሲስተም ገንዘብንና ጊዜን በአግባቡ እንድንጠቀምበት የሚያደርግና በየትኛውም ባንክ ሂሳብ ያለን ገንዘብ በፈለግነው ጊዜና ቦታ እንድንጠቀም የሚያግዝ መሆኑን በመግለጽ ኢንተርኔት ባንኪንግ መጠቀም ከፍጥነቱ አንፃር በጀትን በእጥፍ እንደመጠቀም ይቆጠራል ሲሉ ምን ያህል ስራዎቻችንን ሊያቀል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ኢንተርኔት ባንኪንግ ከነበረው የወረቀት አሰራር በበለጠ ጥብቅ የሆነ የቁጥጥር ስርአት ያለው አሰራር መሆኑን ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

በፊርማ ስነስርዓቱ የሚመለከታቸው የባንክ ኃላፊዎች፣ዳይሬክተሮች፣ የክልል ሴክተር መ/ቤት ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

12/05/2026

የቻናል አንድ ፕሮግራም

 #የገንዘብ ቢሮ እና ፍትህ ቢሮ ቅንጂታዊ አሰራር*********የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ እና ፍትህ ቢሮ በጋራ ቅንጂታዊ አሰራር እየሰሩ እንደነበርና ቀጣይም በጋራና በትብብር እንደሚሰሩ አስ...
10/05/2026

#የገንዘብ ቢሮ እና ፍትህ ቢሮ ቅንጂታዊ አሰራር
*********
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ እና ፍትህ ቢሮ በጋራ ቅንጂታዊ አሰራር እየሰሩ እንደነበርና ቀጣይም በጋራና በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ አታላይ ጥላሁን የገንዘብ ቢሮ አጠቃላይ ክልሉን ወከሎ የህግ ሂደቶችን ፍትህ ቢሮን ጨምሮ ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በጋራ በማርቀቅ እየሰራ እንደሆነ ገልፀው ፤ለአብነትም የመንግስት ግዥ ረቂቅ አዋጅ ፣የህብረተሰብ ተሳተፎ ማስተባበሪያ አዋጅ ፣የግዥ ረቂቅ መመሪያ እና የመሳሰሉትን ተግባራትን በጋራ ሰርተናል እየሰራንም እንገኛለን ብለዋል።
የአብክመ ገንዘብ ቢሮ በማክሮ ደረጃ የክልሉን ሀብት ያስተዳድራል በማይክሮ ደረጃ ደግሞ እንደማንኛውም ተቋም ተግባሩን ያከናውናል ያሉት ቢሮ ኃላፊው የተከበሩ አቶ አታላይ በህግ የሚመለሱ ተግባራትን በጋራ ቅንጅት ለመስራት ከፋትህ ቢሮ ጋር አብረን እንሰራለን ብለዋል ።
ፍትህ ቢሮ ለቢሮአችን በዚህ ልክ በጥንካሬ በድክመት ተግባራትን በመለየት የተደገፍንበትን አግባብ ያደነቁት ኃላፊው አንዳንዶቹ ተግባራት በተግባር ስንፈጽም ከህግ አንጻር በቀጣይ በጋራ የምናየው ይሆናል ብለዋል።
ውል አስተዳደርን አስመልክቶ ውልን የመመርመር ጉዳይ ገንዘብ ቢሮ እና ፍትህ ቢሮ በጋራ በመወያየት አቅጣጫ ማስቀመጥ አንደሚገባም ቢሮ ኃላፊው ጨምረው ተናግረዋል ።
የአብክመ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ብርሀኑ ጎሽዬ በበኩላቸው ፍትህ ቢሮ ከገንዘብ ቢሮ ጋር ያደረገውን የድጋፍ ውጤት በዚህ ልክ መግባባት የተደረሰበትን ሁኔታ መልካም እንደሆነ በመግለጽ የተለያዩ የግዥ ውሎችን ስናራዝም ከህግ አንጻር ክፍተት እንዳይኖራቸው ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ከግዥ ዘዴዎች አኳያ አንደኛውን ጥለን ሌላኛውን ስንመርጥ ከህግ እና ከመንግስት ሃብት አጠቃቀም አንጻር በአግባቡ እየታየ መሆን አለበት ሲሉ ቢሮ ኃላፊው አቶ ብርሃኑ አሳስበዋል ።ከኦዲት ጉድለት ማስመለስ አንጻር ከባለበጀት ተቋማት ጋር በመነጋገር እና በመግባባት የኦዲት ግኝቶችን ለማስመለስ በጋራ እንደሚሰሩም አቶ ብርሀኑ ጠቁመው ሃብት የሚያስተዳድሩ ተቋማት ፣ መሬት የሚያስተዳድሩ ተቋማት አና የመሳሰሉትን ተቋማት ትኩረት ሰጥቶ ማየት እንደሚገባም ቢሮ ኃላፊው አስታውቀዋል ።

 # የ2019 በጀት ዓመት በጀት ስሚ ኦረንቴሽን ፡፡********************************የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ለቀጣይ 2019 በጀት ዓመት በጀት ስሚ ኦ...
09/05/2026

# የ2019 በጀት ዓመት በጀት ስሚ ኦረንቴሽን ፡፡
********************************
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ለቀጣይ 2019 በጀት ዓመት በጀት ስሚ ኦረንቴሽን ከክልል ባለበጀት መስሪያቤቶች ጋር አካሄደ፡፡
በዚሁ ኦረንቴሽን የክልላችን ቢሮዎች የበጀት አስተዳደር ዳይሬክተሮች እና የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በቀጣይ ክልሉ በሚያድርገው የበጀት ስሚ መርሃ ግብር መሰረት በክልሉ የሚገኙ ሁሉም ቢሮዎች የበጀት ስሚ መርሃ ግብር እንደሚያካሂዱ ቢሮው አስታውቋል፡፡

 #በፕሮግራሙ የሚመጣ ሃብት የህዝብን ልማት ማስፈፀሚያ እንደሆነ ታውቆ ሊሰራበት ይገባል// ገንዘብ ቢሮ  *****************************************የአማራ ክልል ገንዘ...
08/05/2026

#በፕሮግራሙ የሚመጣ ሃብት የህዝብን ልማት ማስፈፀሚያ እንደሆነ ታውቆ ሊሰራበት ይገባል// ገንዘብ ቢሮ
*****************************************
የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ የቻናል አንድ ፕሮግራሞች የዘላቂ መሬት አያያዝና አጠቃቀም (ካልም) ፕሮግራም በዚህ አመት መጨረሻ በሚጠናቀቀው ካልም አንድ ፕሮግራም አፈፃፀም ላይ ከፈፃሚ ክልል ሴክተር መ/ቤቶች፣ ከዞንና ወረዳዎች ጋር ገምግሟል፡፡

በገንዘብ ቢሮ የቻናል አንድ ፕሮግራሞች ተወካይ አስተባባሪ አቶ ማስተዋል ሙሉአለም በግምገማ መድረኩ ተገኝተው የዘላቂ መሬት አያያዝና አጠቃቀም (ካልም) ፕሮግራም ላለፉት ሰባት ዓመታት የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች ሲፈታ የቆየ መሆኑን ገልጸው፤ በአሁነ ወቅት ፕሮግራሙ 156 ወረዳዎች ላይ ተፈፃሚ እየሆነ እንደሚገኝና ከሌሎች ፕሮግራሞች በተሻለ ትልቅ ሃብት በማምጣት በክልሉ ከፍተኛ የሆነ ለውጥ ያሳየ ፕሮግራም እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

ፕሮግራሙ በያዝነው 2018 በጀት አመት መጨረሻ እንደሚጠናቀቅ የገለፁት አስተባባሪው አቶ ማስተዋል በአዲስ ካልም ሁለት ለሚጀምረው ፕሮግራም አጀማመር እንዲረዳ ከዚህ አፈፃፀም የተሻለ ተሞክሮዎችን በመውሰድና ክፍተቶችን በመለየት በቀሪ ወራቶች የመጣውን ሃብት ለታለመለት አላማ በአግባቡ አሟጦ በመጠቀም አጠናቆ ለቀጣይ የተሻለ ሃብት እንዲመጣና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

የዘላቂ መሬት አያያዝና አጠቃቀም (ካልም) ፕሮግራም ሃብት የህዝቡ ልማት ማስፈፀሚያ በመደበኛ በጀት መሸፈን ያልተቻለውን ሸፍኖ የሚሰራ በብድር የሚገኝ ሃብት መሆኑ ታውቆ ይህ ሃብት የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮችን እንዲፈታ የአመራሩ፣ የባለሙያው እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ሃብቱን ለታለመለት አላማ በማዋል አፈፃፀሙን ከፍ ማድረግና የተሰሩ ስራዎች የሚያሳይ ወቅቱንና ጥራቱን የጠበቀ ሪፖርት እንዲልኩ አስተባባሪው አቶ ማስተዋል አስገንዝበዋል፡፡

በግምገማው የተገኙት በመሬት ቢሮ የካልም ፕሮግራም ም/አስተባባሪ አቶ ደርበው አያሌው ለፕሮግራሙ የሚመደበውን በጀት በአግባቡና ከተመደበለት አላማ ጋር በማጣጣም በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መጠቀም እንደሚገባ ገልፀው፤ በፕሮግራሙ በጀት የሚገዙ ንብረቶችን በመመዝገብ በአግባቡ ማስተዳደርም ጭምር እንደሚገባና ሃብቱን ውጤት በሚያመጣና ለውጥን በማያሳይ መንገድ መጠቀም ይገባል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ማስተዋል እንደፋይናንስ ማህበረሰቡ የፕሮግራሙ በጀት ባለቤት መሆኑን ከማሳወቅ ጀምሮ ሂሳቡ በአግባቡ ስራ ላይ እንዲውል እየተደረገ ያለው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ ሁሉም የዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ በፕሮግራሙ የተመዘገቡ ተሰብሳቢ ሂሳቦችን በወቅቱ ማመራረድ፣ ጠንከር ያለ የኦዲት ስራ መስራት፣ የወጭ አፈፃፀሞችን በየጊዜው መገምገም፣ ሂሳቡን በአይቤክስ መመዝገብ፣ ጥራትና ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት በመላክ እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራሮችን አጠናክሮ በመቀጠልና በጋራ በመገምገምና ለመጣለት አላማ ብቻ በማዋልና አሟጦ በመጠቀም ሂሳቡን መዝጋትና ለቀጣይ ካልም ሁለት ራስን በዚህ ልክ ዝግጁ ማድረግ ይገባል ሲሉ ግምገማውን አጠቃለዋል፡፡

Address

Bahir Dar
217

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Finance Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share