Amhara Finance Bureau

Amhara Finance Bureau Bureau of Finance (BoF) is one of the Bureaus under Amhara National Regi

The Amhara National Regional State Bureau of Finance & Economic Cooperation (BoFEC) has established to enhance maximum development of the Amhara Region.

የህፃናት ማቆያ ማዕከል ለሠራተኞች ውጤታማነትና ለተቋማት አፈጻጸም የላቀ አስተዋጽዖ እንደሚኖረው ተገለፀ።የህፃናት ማቆያ ማዕከል መኖሩ የሠራተኞችን የሥራ ተሳትፎና ውጤታማነት በማሳደግ ለተቋማ...
18/08/2026

የህፃናት ማቆያ ማዕከል ለሠራተኞች ውጤታማነትና ለተቋማት አፈጻጸም የላቀ አስተዋጽዖ እንደሚኖረው ተገለፀ።

የህፃናት ማቆያ ማዕከል መኖሩ የሠራተኞችን የሥራ ተሳትፎና ውጤታማነት በማሳደግ ለተቋማት የሥራ አፈጻጸም የላቀ አስተዋጽዖ እንዳለው ተገለፀ።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ የህፃናት ማቆያ ማዕከልን ተግባራዊ በማድረግ፣ ሠራተኞች ልጆቻቸውን በሚሰሩበት አካባቢ በምቾት እንዲያቆዩና ጡት የሚያጠቡበት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቋል።

የመምሪያው ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ነጋ እንደገለፁት፣ የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ መኖሩ በተለይም ሠራተኛ እናቶች ስለልጆቻቸው ያላቸውን ጭንቀት በመቀነስ በሥራቸው ላይ የተሻለ ትኩረት እንዲያደርጉ ያግዛል።

ይህም ሠራተኞች የሥራ ተሳትፎአቸውን እንዲያጠናክሩ፣ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡና የተቋሙን የሥራ አፈጻጸም እንዲያሻሽሉ የሚያስችል መሆኑን ኃላፊዋ ገልፀዋል።

እናቶች ልጆቻቸው በአጠገባቸው በደህና መቆየታቸውን ሲያውቁ ከልጆቻቸው ጋር በቀላሉ ለመገናኘትና በሥራቸው ላይ በተረጋጋ መንፈስ ለመስራት የተሻለ እድል እንደሚያገኙም ገልጸዋል።

የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ለሠራተኞች ደህንነትና እርካታ፣ ለተቋሙ ውጤታማነት እና ለአገልግሎት ጥራት የራሱ የሆነ አስተዋጽዖ እንዳለውም ኃላፊዋ አስረድተዋል።

ማዕከሉ ለህፃናት ይበልጥ ምቹና ማራኪ እንዲሆን ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተለያዩ የማሻሻያ ሥራዎች ማከናወኑን ወ/ሮ ሰላማዊት ነጋ ገልጸዋል።

በተቋሙ የህፃናት ማቆያ አገልግሎት መጀመሩ ልጆቻቸውን በአቅራቢያቸው በማግኘታቸው ሥራቸውን በተረጋጋ መልኩ ለማከናወን እንደሚያስችላቸው የመምሪያው ሠራተኞች ተናግረዋል።

በአጠቃላይ የህፃናት ማቆያ ማዕከል ለሠራተኛ እናቶች ምቹ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ፣ የሠራተኞችን ተሳትፎና ውጤታማነት በማሳደግ የተቋማትን አገልግሎት ጥራትና የሥራ አፈጻጸም ለማሻሻል አስፈላጊ ማህበራዊ ድጋፍ መሆኑ ተገልጿል።

ማእከላዊ ጎንደር ዞን ኮሚዩኒኬሽን

ከአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/191YyDU2YK/
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofFinance
ዋትስአፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vb8BHKA4SpkAKHBs6M0H
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/amhara415?igsh=MTh1Nzd3dnNpaWRxMg==
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/.finance.bureau?_r=1&_t=ZS-98Pv19CAtHA
ዌብሳይት http://www.amharabofec.gov.com/
ኤክስ (ትዊተር) https://twitter.com/

 #በአዲሱ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ስልጠና  ********************************የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳ...
17/08/2026

#በአዲሱ የግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ስልጠና
********************************
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአዲሱ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር አፈፃፀም መመሪያ ዙሪያ ለክልል ተቋማት የግዥ ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

በስልጠና መድረኩ የተገኙት የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አደራጀው ካሴ ለክልላችን የኢኮኖሚ እድገትና የልማት ግቦች መሳካት ትልቅ ሃላፊነት ወስዳችሁ ለምትሰሩ የግዥ ዘርፍ አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች አዲሱ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ስልጠና መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀው በአለፉት 15 አመታት በክልላችን ሲሰራበት የቆየው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 179/2003 በመተካት በአዋጅ ቁጥር 306/2018 ዓ.ም የፀደቀ ሲሆን ይህንኑ አዋጅ ተከትሎ የወጣውን የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ከ2019 በጀት አመት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ አዲሱ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ በርካታ ማሻሻያዎች ተደርገውበት እንደፀደቀ የገለፁት ም/ቢሮ ሃላፊው አቶ አደራጀው ከአገሪቱ የኢኮኖሚ አድገት፣ የመግዛት አቅም ለውጥ እንዲሁም አለምአቀፋዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ እና ከቴክኖሎጅ እድገት ጋር የተጣጣመ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ እንዲያስች ተደርጐ የተዘጋጀ መመሪያ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ስልጠና ሁላችንም ራሳችንን በማብቃትና ለሌሎች ባለሙያዎች ግንዛቤ በመስጠት እንደተቋም ከወዲሁ የተደራጀ እቅድ በማቀድ የግዥና ንብረት አስተዳደር ስራዎችን በማዘመንና ዲጂታላይዝ በማድረግ በኤሌክትሮኒክስ የግዥ ስርዓት መተግበር፣ አዋጁ ሲሻሻል የተጠያቂነት ስርአትንም አብሮ እንዲተገበር ተደርጐ ስለተዘጋጀ ተጠያቂነትን ማስፈንና የህግ ማስከበር ስራን በመስራት፣ ግዥዎችን ስንፈጽም የህይወት ዘመን ወጭ ትንተናና የአካባቢ ጥበቃን ታሳቢ ያደረገ ግዥ በመፈፀም መስራት እንደሚገባና በመጨረሻም የአገር ውስጥ አምራቾችን እና የስራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታ የግዥ ስርዓት በመከተል እንዲሁም የሰነዶች አያያዝና ውል አስተዳደር ስራን በማጠናከር የግዥ ስራዎቻችንን በዚህ ልክ አስበን ለመተግበር ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባም ም/ቢሮ ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡

እያንዳንዱ ግዥ ፈፃሚ ተቋም ግዥዎችን ሲፈጽም መረጃዎችን በሃርድና በሶፍት ኮፒ/ዲጂታላይዝ/ መረጃ በማደራጀት መያዝ አለበት ያሉት አቶ አደራጀው የፍትህ ዘርፉም በውል አስተዳደር ስርዓት ዙሪያ የግዥ ስራዎችን እንዴት መደገፍ እንዳለበት በዚህ መድረክ ውይይት የሚደረግበት ይሆናል ብለዋል፡፡

በቀጣይም 4030 ለሚሆኑ ዞን፣ ታች ወረዳና ከተሞች ድረስ ለሚገኙ የግዥና ንብረት አስተዳደር ፈፃሚ ባለሙያዎች ተመሳሳይ ስልጠናዎች እንደሚሰጡም በመድረኩ ተገልጿል፡፡
ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/191YyDU2YK/
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofFinance
ዋትስአፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vb8BHKA4SpkAKHBs6M0H
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/amhara415?igsh=MTh1Nzd3dnNpaWRxMg==
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/.finance.bureau?_r=1...
ዌብሳይት http://www.amharabofec.gov.com/
ኤክስ (ትዊተር) https://twitter.com/

 #ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 እቅድን  ገመገመ ****************************************የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ከዳይሬክ...
13/08/2026

#ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 እቅድን ገመገመ
****************************************
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ከዳይሬክቶሬቶች ጋር የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2019 እቅድ ዝግጅትን በተናጠል በጥልቀት በመገምገም የማስተካከያ ሀሳብ እና አቅጣጫ አስቀምጦል፡፡

የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን ቢሮው በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት በእቅድ ይዞ ሲፈጽም የቆየውን በጥንካሬና በድክመት በመለየት እያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት አቅርቦ ማስገምገሙ ለቀጣይ አፈፃፀማችን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልፀው በያዝነው 2019 በጀት ዓመት የሚተገበሩ ተግባራት ከክልሉ የአሻጋሪ እድገትና ዘለቂ ልማት እቅድ በመነሳት በቢሮ ደረጃ የታቀደውን በማውረድ እያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት የራሱን ተግባራትን በአግባቡ ለይቶ በመያዝ እና የመፈፀሚያ ጊዜ አስቀምጦ በማቀድ የሚጨበጥ ውጤት ለማምጣት እንደተቋም አስበን እንድንሠራ ያግዘናል ብለዋል፡፡

እያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት የ2018 በጀት አፈፃፀሙን በተናጠል በዳይሬክቶሬት ደረጃ አቅርቦ በማስገምገም አቅጣጫ የተሰጠበት ሲሆን በተመሳሳይ የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ከተቋሙ እቅድ ከመካተቱ በፊት እያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት አቅርቦ በማስገምገሙ የማስተካከያና የወደፊት የስራ አቅጣጫ ጭምር ተሰጥቷል፡፡

በቀጣይም በተቋም ደረጃ የተዘጋጀው የተጠቃለለ እቅድ አፈፃፀም እና ተቋማዊ እቅድ በቢሮው ሰራተኞች እና እንዲሁም በዞን እና ሪጂዮፖሊታን ከተሞች ገንዘብ መምሪያዎች ቀርቦ በቅርቡ የሚገመገም ይሆናል፡፡

ከአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/191YyDU2YK/
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofFinance
ዋትስአፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vb8BHKA4SpkAKHBs6M0H
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/amhara415?igsh=MTh1Nzd3dnNpaWRxMg==
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/.finance.bureau?_r=1&_t=ZS-98Pv19CAtHA
ዌብሳይት http://www.amharabofec.gov.com/
ኤክስ (ትዊተር) https://twitter.com/

 # በተሻሻለው የቴምብር ቀረጥ አዋጅ ዙሪያ የግንዛቤ መስጫ ውይይት********************************የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የፊሲካል ፖሊሲ በአዲሱ በተ...
12/08/2026

# በተሻሻለው የቴምብር ቀረጥ አዋጅ ዙሪያ የግንዛቤ መስጫ ውይይት
********************************
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የፊሲካል ፖሊሲ በአዲሱ በተሻሻለው የቴምብር ቀረጥ አዋጅ ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ መስጫ ውይይት አካሂዷል፡፡
የቴምብር ቀረጥን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር 307/2018 እስካሁን በስራ ላይ የነበረው የበፊቱ የቴምብር ቀረጥ አዋጅ የተቀመጠው የቴምብር ቀረጥ ማስከፈያ አዋጁ ከወጣ ረጅም ጊዜ ያስቆጠር በመሆኑ እና የቴምብር ቀረጥ ማስከፈያ ምጣኔው ዝቅተኛ ስለሆነ ከተገልጋዮች የመክፈል አቅም ጋር የተመጣጠነ ማሻሻያ በማስፈለጉ እና ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት የቴምብር ቀረጥ አዋጁን አስመልክቶ ማሻሻያ የተደረገባቸውን አዋጆች ለአፈጻጸም ያመች ዘንድ በዚህ ማሻሻያ አዋጅ አጠቃሎ ማውጣት ማስፈለጉ እንደሆነ በውይይቱ ተገልጿል፡፡
እስከአሁን ስራ ላይ ያሉ የቴምብር ቀረጥ አዋጅ ቁጥር 31/1991፣1992/2003፣249/2009 እና 275/2013 ክልላችን ከደረሰበት የኢኮኖሚ እድገትና ዓለማቀፋዊ ሁኔታዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ ከዚህ በፊት የነበረውን የቴምብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር ሙሉ በሙሉ በመቀየር የቴምብር ቀረጥ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 307/2018 በመተካት ከታህሳስ 17/2018 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን በአዋጁ ተገልጿል፡፡
ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/191YyDU2YK/
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofFinance
ዋትስአፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vb8BHKA4SpkAKHBs6M0H
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/amhara415?igsh=MTh1Nzd3dnNpaWRxMg==
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/.finance.bureau?_r=1...
ዌብሳይት http://www.amharabofec.gov.com/
ኤክስ (ትዊተር) https://twitter.com/

10/08/2026
"በ2019 ዓ.ም በክልሉ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው" አቶ አታላይ ጥላሁንየአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፌዴራል የመንግሥት ግዥ እና ንብ...
10/08/2026

"በ2019 ዓ.ም በክልሉ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው" አቶ አታላይ ጥላሁን

የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ከፌዴራል የመንግሥት ግዥ እና ንብረት ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን በክልሉ ለመተግበር ለተመረጡ አስር ተቋማት የግዥ ባለሙያዎች እና የሥራ ኀላፊዎች ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።

የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኀላፊ አታላይ ጥላሁን እንደገለጹት አሠራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የማዘመን እና የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ውጤታማ የማድረግ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።

የሕዝብ ሃብትን በቁጠባ እና በተቀላጠፈ መልኩ ለማሥተዳደር የሚያስችለውን አዲሱን አሠራር በ2019 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ የሕግ ማዕቀፍ፣ የመመሪያ እና የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።

አክለውም የአስሩ ተቋማት የሙከራ ትግበራ ስኬታማነት ሥርዓቱን እስከ ታችኛው የመንግሥት እርከን ለማስፋት መሠረት እንደሚኾንም ጠቁመዋል።

በፌዴራል የመንግሥት ግዥ እና ንብረት ባለሥልጣን የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓት ፕሮጀክት የአቅም ግንባታ አሥተባባሪ ደበበ ማሞ በበኩላቸው ሥርዓቱ በ2014 ዓ.ም በዘጠኝ የፌዴራል ተቋማት ተጀምሮ በ2017 ዓ.ም በሁሉም የፌዴራል ተቋማት ቅርንጫፎች እና ዩኒቨርሲቲዎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል።

አሠራሩ ከወረቀት እና ከሰው ንኪኪ ነፃ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና አስተማማኝ በመኾኑ ወጥ የኾነ ሀገራዊ ሥርዓት ለመዘርጋት ወደ ክልሎች የማውረድ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

በሥልጠናው እየተሳተፉ የሚገኙ የግዥ ባለሙያዎች እስካሁን የነበረው ወረቀትን መሠረት ያደረገ አሠራር የተንዛዛ እና አሰልች እንደነበር ገልጸው የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓቱ መተግበሩ ጊዜን፣ ጉልበትን እና ወጭን ከመቆጠቡ ባሻገር ሙስናን በመከላከል እና እንግልትን በማስቀረት አገልግሎቱን በከፍተኛ ሁኔታ ያቀላጥፋል ሲሉ ተናግረዋል።



አሚኮ

 # የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ማስተግበሪያ ፕሮግራም ማስጀመሪያ ስልጠና  ********************************የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ከኢፌዲሪ የመንግስት ግዥ ...
10/08/2026

# የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ማስተግበሪያ ፕሮግራም ማስጀመሪያ ስልጠና
********************************
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ ከኢፌዲሪ የመንግስት ግዥ ባለስልጣን ጋር በጋራ በመተባበር በክልሉ በተመረጡ 10 ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ ስርዓት (Electronic Government Procurment System) e-GP ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ትግበራ ማስጀመሪያ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡

በስልጠና መድረኩ የተገኙት የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን የኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ ስርዓት ቀደም ብሎ በፌደራል ደረጃ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው፤በክልላችን በተመረጡ 10 ተቋማት የፕሮግራሙን ማስጀመሪያ ስልጠና በመስጠት የመንግስት ግዥ ሂደቱ ቀልጣፋ፣ወጤታማ ለማድረግ በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ መደረጉ ልዩ እንደሚያደርገው ተናግረዋል፡፡

የመንግስትን ሃብት በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋል የኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ ስርዓት ትልቅ ሚና አለው ያሉት ቢሮ ኃላፊው አቶ አታላይ ይህንን በውጤታማነት ተግባራዊ ለማድረግ እንደክልል የመጀመሪያው የህግ ማዕቀፍ በክልል ምክር ቤት በማጸደቅ ለመንግስት ግዥ መመሪያ በተለይም ለኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ምቹ የሆነ እና ይህንን ያገናዘበ መመሪያ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡

በቀጣይም ለዚህ ፕሮግራም ማስተግበሪያ እንደ ክልል የቴክኖሎጅ ልማት ስራው በክልሉ አቅም እየተዘጋጀ ቢሆንም ለጊዜው የፌደራል መንግሰትን ለመጠቀም ቢሮው በዝግጅት ላይ መሆኑን ቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

በክልሉ 10 ተቋማት በሙከራ ትግበራ ስራ በመስራት ወደ ሌሎች ተቋማት ማለትም ክልል ቢሮዎች፣ታች ዞን ፣ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች እና ሌሎች የመንግስትን በጀት የሚጠቀሙ ተቋማት ሁሉ ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆኑ እነዚህ 10 የክልል ተቋማት ስኬታማ መሆን የራሱ ትልቅ አስተዋጽኦ ስላለው እዚህ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ሲሉ ቢሮ ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ስልጠና የተገኙት ባለሙያዎች ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት እና ተገቢ ግንዛቤ በመያዝ ከስልጠና መልስ በተቋማቸው ለሚገኙ ሌሎች ባለሙያዎች ጭምር ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው የገለጹት ቢሮ ኃላፊው በአሰራር የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጋራ እየፈታን በክልሉ ዘመናዊ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ስርዓት ስራው በእናንተ ስለሚተገበር ከስልጠና ያለፈ ኃላፊነት ያለበችሁ መሆኑን በመረዳት ለተግባሩ ስኬታማነት የድርሻችሁን እንድተወጡ ስሉ አሳስበዋል፡፡

ከአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/191YyDU2YK/
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofFinance
ዋትስአፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vb8BHKA4SpkAKHBs6M0H
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/amhara415?igsh=MTh1Nzd3dnNpaWRxMg==
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/.finance.bureau?_r=1&_t=ZS-98Pv19CAtHA
ዌብሳይት http://www.amharabofec.gov.com/
ኤክስ (ትዊተር) https://twitter.com/

10/08/2026
የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም አፈጻጸም ተገመገመየአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ ገመገመ፡፡ ቢ...
08/08/2026

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም አፈጻጸም ተገመገመ

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ ገመገመ፡፡

ቢሮዉ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በመጀመሪያዉ ዙር እንዲተገብሩ ከተመረጡ የክልል ቢሮዎች አንዱ ሲሆን በዝግጅት ምእራፍ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሰትሪንግ ኮሚቴ፤ የሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴ እና የቴክኒክ ኪሚቴ አባላት በተገኙበት ሪፖርት ቀርቦ በዝርዝር ተገምግሟል፡፡ ሪፖርቱ በቢሮዉ የሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን በቀረበዉ ሪፖርት ላይ በመመስረት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዉ ዉይይት ተካሂዶበታል፡፡

በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም እንደ ቢሮ በትኩረት ከምንፈጽማቸዉ ሥራዎች አንዱ መሆኑን የገለጹ ሲሆን እስካሁን ባለዉ ሁኔታ የተከናወኑ አበረታች ተግባራት መኖራቸዉን ጠቅሰዉ ነገር ግን ቀሪ ሥራዎችን ጊዜ የለንም በሚል መንፈስ ትኩረት ስጥተን መሥራት አለብን ያሉ ሲሆን የቢሮዉ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ስትሪንግ ኮሚቴም የቅርብ ክትትል የሚያደርግ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በዉይይቱ ወቅትም በቀጣይ ጊዚያት የሚሠሩ ሥራዎች ተለይተዉ በትኩረት እንዲፈጸሙ በመግባባት ዉይይቱ ተጠናቋል፡፡

ከአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/191YyDU2YK/
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/
ቴሌግራም https://t.me/AmharaBureauofFinance
ዋትስአፕ https://whatsapp.com/channel/0029Vb8BHKA4SpkAKHBs6M0H
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/amhara415?igsh=MTh1Nzd3dnNpaWRxMg==
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/.finance.bureau?_r=1&_t=ZS-98Pv19CAtHA
ዌብሳይት http://www.amharabofec.gov.com/
ኤክስ (ትዊተር) https://twitter.com/

Address

Bahir Dar
217

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Finance Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share