Amhara National Regional State Environment & Forest Protection Authority

Amhara National Regional State Environment & Forest Protection Authority The Authority strives to ensure the right of citizens to live in clean and unpolluted environment.

የላቀ እምርታ፣ በምርታማነት ማንሰራራት  የዘመናዊ ግብርና ምዕራፍግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሠረት ብቻ ሳይሆን፣ የምግብ ዋስትና፣ የገቢ ምንጭና የዜጎች የኑሮ መሻሻል ዋነኛ መሠረት ነው። ይ...
06/09/2026

የላቀ እምርታ፣ በምርታማነት ማንሰራራት የዘመናዊ ግብርና ምዕራፍ

ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሠረት ብቻ ሳይሆን፣ የምግብ ዋስትና፣ የገቢ ምንጭና የዜጎች የኑሮ መሻሻል ዋነኛ መሠረት ነው። ይህን ዘርፍ ከባህላዊ አሠራር በማላቀቅ ወደ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪና ምርታማ ሥርዓት መለወጥ ደግሞ የዘመኑ ቀዳሚ ተግባር ነው።

ሀገራችን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የምታከብራቸውን የጳጉሜን ቀናት መርሃ ግብር በይፋ ጀምራለች፣ “ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀን” ሆኖ የሚከበር ሲሆን በዕለቱም በበጀት ዓመቱ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ከተረጅነት ወደ ምርታማነት የሚደረገውን ሽግግር የሚያጠናክሩ ስኬቶችን የምናጎላበት ወቅት ነው።

በክልላችን በ2018 በጀት ዓመት ከተመዘገበው 7.9 በመቶ ጠቅላላ የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ የግብርናው ዘርፍ ከ5.5 በመቶ በላይ ድርሻ ማበርከቱ፣ ዘርፉ ለክልሉ ምጣኔ ሀብት ዕድገት ያለውን ወሳኝ ሚና የሚያሳይ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡት አበረታች ስኬቶችም የዘርፉን የማንሰራራት ምዕራፍ በተግባር ያረጋገጡ ናቸው።

በዚህም የለውጥ ሂደት በክልላችን በ2017/18 የምርት ዘመን 188 ሚሊዮን ኩንታል እንዲሁም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 13 ሚሊዮን ኩንታል ምርት የተገኘ ሲሆን የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት ከ978 በላይ የእርሻ ትራክተሮች ለአርሶ አደሮች መሰራጨቱ በዘመናዊ ግብርና የተገኙ ጉልህ አሻራዎች ናቸው።

በ2018/19 የምርት ዘመን 5.6 ሚሊዮን ሄክታር የሚታረስ መሬትን በመጠቀም 205 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት የተያዘው ግብ የምርታማነት ሽግግሩን የምርት አቅምን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማጠናከር ባሻገር የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማጽናት ጠንካራ መሠረት የሚፈጥር ነው።

የ25 ዓመቱ የአሻጋሪ ዕድገትና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ለዘመናዊ ግብርና ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ሲሆን የዘርፉን ተዋናዮች ስምረት በማጠናከር ከፍጆታ የተሻገረ ለገበያና ለኢንዱስትሪ የሚሆን ምርት በማምረት የአርሶ አደሩን ገቢና የኑሮ ደረጃ ማሻሻል ዋና መዳረሻችን ነው።

ይህ ለውጥ በበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት፣ በኩታገጠም እርሻ አሠራር፣ በሰፋፊና በተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በሌሎች የምርታማነት ማሳደጊያ ሥራዎች በግልጽ እየታየ ነው። የምርት መጠንን ብቻ ሳይሆን ጥራትን፣ የገበያ ትስስርንና የአርሶ አደሩን ገቢ ማሳደግ ላይ የተመሠረተው አዲሱ አቅጣጫ የዘመናዊ ግብርናን ገቢራዊነት ያረጋገጠ ነው።

በመሆኑም የ“እምርታ ቀን” በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን የምናከብርበት ብቻ ሳይሆን፣ የተገኙትን ውጤቶች በማጠናከር የበለጠ ምርታማ፣ ተወዳዳሪ፣ ዘመናዊና ዘላቂ የግብርና ስርዓት ለመገንባት ትጋትንና ቁርጠኝነትን የምናረጋግጥበት ነው።

አቶ ደረጀ ማንደፍሮ
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኋላፊ

የ2018 ዓ.ም ማገባደጃ ዋዜማ እና "የኢትዮጵያ መንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የምትከበረው ጳጉሜ-------------------------ዛሬ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓመቱ የመጨረሻው ...
05/09/2026

የ2018 ዓ.ም ማገባደጃ ዋዜማ እና "የኢትዮጵያ መንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የምትከበረው ጳጉሜ
-------------------------

ዛሬ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የዓመቱ የመጨረሻው ወር ተጠናቆ አስራ ሦስተኛዋ እና ልዩዋ የሽግግር ወር ጳጉሜን ለመቀበል በመላው ሀገሪቱ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል። የዘንድሮው የጳጉሜን ወር በአጠቃላይ "የኢትዮጵያ መንሰራራት" በሚል አብይ መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች በድምቀት ትከበራለች።

አዲሱን የ2019 ዓ.ም የብሩህ ተስፋ ዘመን በላቀ የሥራ ተነሳሽነት ለመቀበል ፣ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት ትልቅ ሀገራዊ ትርጉም ባላቸው ልዩ ስያሜዎች ተከፋፍለው እንደሚከተለው ይከበራሉ፦

- #የዕምርታ ቀን፡ በልማት፣ በኢኮኖሚ፣ በዘመናዊ አሰራር እና በአገልግሎት አሰጣጥ የተሻለ ሀገራዊ እና ተቋማዊ ስኬቶችን ማስመዝገብን በማሰብ፤

- #የመንስራራት ቀን፡ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በሙሉ ወደ ዕድል በመቀየር እና በፅናት ተሻግሮ፣ እንደ ሀገር በአዲስ ተስፋ እና በአዲስ አቅም ከፍታን ማለምን በማጉላት፤

- #የፅናት ቀን፡ ለተጀመሩ ሀገራዊ የልማት ራዕዮች፣ ለተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም እና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ያለንን የማይናወጥ አቋም እና ትጋት በማሳየት፤

- #የህብር ቀን፡ የጋራ መግባባትን፣ ማህበራዊ ትስስርን፣ አንድነትን እና ተባብሮ የመስራት ባህልን ይበልጥ በማጠናከር፤

- #የነገ ቀን፡ ለቀጣዩ ትውልድ የምናስረክባትን የበለጸገች ሀገር ራዕይ ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ እና የተሻለ ዘመንን በማለም የሚከበሩ ይሆናል።

ይህንን የ13ኛዋን ወር የሽግግር ወቅት አስመልክቶ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸማችንን በማጠቃለል እና ዕውቅና በመስጠት፣ እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዳችንን በማስተዋወቅ አዲሱን ዓመት ለመቀበል ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል።

መላው ህብረተሰብም የክረምቱን መጠናቀቅ ተከትሎ እነዚህን "የኢትዮጵያ መንሰራራት" ቀናት ፤ በመተሳሰብ፣ በአዲስ የስራ መንፈስ እና በብሩህ ተስፋ እንዲያሳልፋቸው መልዕክት እናስተላልፋለን።

መልካም የሽግግር ቀናት፣ መልካም አዲስ ዓመት!

የአብክመ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን

Protecting Nature While Creating Sources of IncomeAddis Ababa, September 2, 2026 — The Amhara Regional Environmental Pro...
04/09/2026

Protecting Nature While Creating Sources of Income

Addis Ababa, September 2, 2026 — The Amhara Regional Environmental Protection Authority has conducted a performance review of the 2018 Ethiopian fiscal year and introduced its plan for the 2019 fiscal year.

Speaking at the opening of the review and planning forum, Deputy Head of the Authority, Belesti Fetene, said ensuring that development projects do not cause negative impacts on the environment and communities is among the institution’s key responsibilities.

Accordingly, during the 2018 Ethiopian fiscal year:

- Approval permits were issued for more than 6,000 new projects.
- Environmental inspections were conducted on more than 5,000 previously operational projects.
- Corrective measures were taken against projects that failed to meet environmental standards.

The Deputy Head said the Authority achieved more than 90 percent of its planned activities during the fiscal year.

He also noted that efforts to protect and develop forest resources over the past two to three years have contributed to an increase in the region’s forest coverage. During the fiscal year, more than 249 million birr was collected and generated as government revenue from the movement and trade of charcoal, incense, gum and other forest products.

However, he identified budget constraints and the destruction of institutional property due to security challenges as among the major obstacles faced by the Authority.

For the 2019 fiscal year, the Authority has identified several priority areas, including strengthening the proper management of forest-product trade, providing special protection for natural forests, increasing the number of protected forests, and strengthening environmental pollution monitoring and enforcement.

Leaders of zonal institutions participating in the forum said that during the 2018 fiscal year, efforts were made to identify local natural resources, organize community associations and attract investors to generate income from forest products. They also highlighted the employment opportunities created for young people in the sector.

Going forward, they said they will work more closely with producers, investors and young people living in areas rich in incense, charcoal, myrrh and gum resources to increase income generation while ensuring sustainable use of natural resources.



አቡነ ዮሴፍ ተራራ  የተፈጥሮ የቱሪዝም መስህብ  ላስታ ወረዳ  ሰሜን ወሎ ዞን!!!💫ከላሊበላ ከተማ በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።💫ከባህር ጠለል በላይ 4282 ሜትር ከፍታ ያለው  ነው...
04/09/2026

አቡነ ዮሴፍ ተራራ የተፈጥሮ የቱሪዝም መስህብ ላስታ ወረዳ ሰሜን ወሎ ዞን!!!

💫ከላሊበላ ከተማ በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።
💫ከባህር ጠለል በላይ 4282 ሜትር ከፍታ ያለው ነው ፡፡

💫በውስጡ የተለያዩ አገር በቀል እፀዋቶች አስታ፣ ጀበራ እንዲሁም ቀይ ቀበሮ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ፣ ሰሳና ነብር ይገኛሉ።

🌞በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ላይ በተደረገ ጥናት 43 አይነት አጥቢ እንስሳት እና 221 አይነት ወፎችም ይኖሩበታል። አቡነ ዮሴፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የአዕዋፍ መኖሪያዎች በወፍት ሃብቱ ሁለተኛ ነው።

💫ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙት ጭላዳ ዝንጀሮ እና ቀይ ተኩላ ይገኛሉ ።

"የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት አስተማማኝ እና ዘላቂነት ያለው የስነ ሕዝብ መረጃ የሚመነጭበት ነው" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎ...
04/09/2026

"የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት አስተማማኝ እና ዘላቂነት ያለው የስነ ሕዝብ መረጃ የሚመነጭበት ነው" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

የአማራ ክልል ሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት የቴክኖሎጂ ቀጥታ ምዝገባ ሲስተም ማስተዋወቅ እና የ2018 በጀት ዓመት የዞኖች እና የከተማ አሥተዳደሮች የዕውቅና መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

በመርሐ ግብሩ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል

የአማራ ክልል ሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ኀላፊ መዓዛ በዛብህ የምዝገባ አገልሎቱን ከወረቀት ወደ ቀጥታ ምዝገባ ማሸጋገራቸውን ገልጸዋል። ከወረቀት ወደ ቴክኖሎጂ የተደረገው ሽግግር ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት፣ የሃብት ብክነትን ለመከላከል፣ ሀሰተኛ ሰነድን ለመከላከል፣ ጊዜ እና ጉልበትን ለመቆጠብ ያስችላል ነው ያሉት።

ሁሉንም የምዝገባ ጣቢያዎች ወደ ቴክኖሎጂ ለማሻገር የሌሎች እገዛ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። ከወረቀት ወደ ቴክኖሎጂ የተደረገው ጉዞ ስኬታማ እንደኾነ አንስተዋል።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እውን እንዲኾን በትብብር መሥራት እንደሚገባም ገልጸዋል። እየተደረገ ያለው ምዝገባ ለሕግ፣ ለስታትስቲክስ እና ሌሎች ሥራዎች እንደመረጃ ኾኖ ያገለግላል ብለዋል።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ለመንግሥት አሥተዳደር ውጤታማነት አስተማማኝ እና ዘላቂነት ያለው የስነ ሕዝብ መረጃ የሚመነጭበት ነው ብለዋል። የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ መረጃ የመንግሥት እና የሕዝብ አሥተዳደር ግንኙነትን የሚያሳልጥ፣ በመረጃ ላይ የተመሠረተ የልማት እና የመልካም አሥተዳደር ዕቅዶች እንዲታቀዱ፣እንዲጎለብቱ እና ውጤታማ እንዲኾኑ የሚያደርግ ሥርዓት ነው ብለዋል።

ተደራሽ እና ጥራት ያለው መረጃ ማመንጨት ደግሞ በብዙ እንደሚጠቅም ገልጸዋል። ለዘመናዊ እና ጥራት ላለው መረጃ ትኩረት እንደተሰጠውም አንስተዋል።

የመረጃ ተደራሽነት እና ጥራት ችግርን ለመቅረፍ ቴክኖሎጂ ወሳኝ መኾኑንም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ከተጀመረ የቆዬ ታሪክ ቢኖረውም በተደራሽነቱ እና በጥራቱ ፈተና ውስጥ ቆይቶ የኖረ ነው ብለዋል። ለዓመታት በፈተና ውስጥ የቆዬውን ሥራ የሚያሻሽለው በቴክኖሎጂ መደገፍ መኾኑን ገልጸዋል።

ሥራውን በቴክኖሎጂ የደገፉ ሀገራት የመንግሥት አሥተዳደርን ቀልጣፋ እና ውጤታማ ማድረግ መቻላቸውን አንስተዋል። ሥራውን በቴክኖሎጂ መደገፍ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ የመረጃ ጥራትን ለማረጋገጥ ያስችላል ነው ያሉት።

በወረቀት የሚደረግ ምዝገባ ( የሰው ንክኪ) ተደራሽነትን ከማዛባቱም በላይ የመረጃ ጥራት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አለው ብለዋል። ሥራውን በቴክኖሎጂ መደገፍ ግልጽ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ መረጃን ለመያዝ እንደሚያስችል ነው የተናገሩት።

የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት በርካታ ባለድርሻ አካላት ተዋናይ የሚኾኑበት መኾኑን ገልጸዋል። የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት በሚሰጠው ውጤት የማይጠቀም ተቋም እና የኅብረተሰብ ክፍል እንደሌለ ተናግረዋል። ይህ ዘርፍ የማኅበረሰብ ምህንድስና ተደርጎ ይወሰዳል ነው ያሉት።

መረጃን ተደራሽ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት ከወረቀት ወደ ቴክኖሎጂ በመሸጋገሩ ደስተኛ መኾናቸውን ተናግረዋል። ቴክኖሎጂ ወጭን ይቆጥባል ብሎም የመረጃ ደኅንነትን ይጠብቃል ነው ያሉት።

©አሚኮ

ባሕር ዳርን ውብ እና ጽዱ ማድረግ የሁሉም ነዋሪዎች ኀላፊነት ነው።በባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ፤ ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ መልዕክት የ2018/19 በጀት...
03/09/2026

ባሕር ዳርን ውብ እና ጽዱ ማድረግ የሁሉም ነዋሪዎች ኀላፊነት ነው።

በባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ፤ ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ መልዕክት የ2018/19 በጀት ዓመት የክረምት የበጎ ፍቃድ የጽዳት ዘመቻ መርሐ-ግብር ተካሂዷል።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ ሰብለ ዘውዱ የጽዳት ዘመቻው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን መነሻ በማድረግ ባሕር ዳር ከተማን ውብ እና ጽዱ የማድረግ ዓላማ ይዞ መካሄዱን ተናግረዋል።

በዘመቻው እንደ ከተማ አሥተዳደር በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።

ሁለተኛ ወሩን በያዘው በከተማዋ የዜጎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተመዘገቡ በርካታ በጎ ፈቃደኞች በንቃት እየተሳተፉ መኾናቸውን አንስተዋል።

የተያዙ ተግባራትም በውጤታማነት እየተፈጸሙ መኾኑን አብራርተዋል። በጎ ፈቃድ አገልግሎቱ እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም ይቀጥላል ያሉት ኀላፊዋ ቀሪ ተግባራትም በውጤታማነት ይተገበራሉ ነው ያሉት።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር አካባቢ ጥበቃ ጽዳት እና ውበት ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ጽጌረዳ አበበ የጽዳት ዘመቻው ማኅበረሰቡ ተሞክሮውን በመውሰድ ለከተማዋ ጽዳት እና ውበት አጋር እንዲኾን በዐቢይ እና በቴክኒክ ኮሚቴ በጋራ የተካሄደ ነው ብለዋል።

ከአጋር አካላት ጋር ተቀናጅቶ ውብ እና ጽዱ ባሕር ዳርን ለመፍጠር እየተሠራ መኾኑንም ተናግረዋል።

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የጽዳት ዘመቻ የውኃ ማፋሰሻ ቦዮችን የማጽዳት፤ የ20/50 ሜትር ራዲየስ ሞዴል መንደር የመፍጠር፤ አረንጓዴ ተክሎችን የመትከል፤ መጤ አረሞችን የማስወገድ እና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ መኾኑን አብራርተዋል።

ዘመቻው ለበጋው መደበኛ የጽዳት ተግባር አጋዥ እንደሚኾንም ተናግረዋል።

በጽዳት ዘመቻው የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው ባሕር ዳርን ውብ እና ጽዱ ማድረግ የሁሉም ነዋሪዎች ኀላፊነት ነው ብለዋል።

በዘመቻው ተሳትፎ ያደረጉትም ባሕር ዳር ጽዱ ስትኾን ተጠቃሚዎቹ ራሳችን ነን በሚል እሳቤ መኾኑን ገልጸዋል።

የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ አስፈላጊ መኾኑንም ተናግረዋል።

የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ግብ ተኮር ተግባራት የላቀ አፈፃፀም ላከናወኑ የዞንና የከተማ አስ/አካ/ጥ/ተጽ/ቤቶች እውቅና ሰጠ። ​የክልል ባለስልጣ...
02/09/2026

የአማራ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ግብ ተኮር ተግባራት የላቀ አፈፃፀም ላከናወኑ የዞንና የከተማ አስ/አካ/ጥ/ተጽ/ቤቶች እውቅና ሰጠ።

​የክልል ባለስልጣን ተቋሙ የ2018 ዓም አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓም ዕቅድ ትውውቅ መድረክ የሁሉም ዞንና ከተማ አስተዳድር ኋላፊዎች፣ ቡድን መሪዎች እንዲሁም የባለስልጣኑ ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት አካሄዷል።

በዚሁ መሠረት በዓመቱ አበይት ተግባራት አበረታች ውጤት ላስመዘገቡ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለወጡ የምስክር ወረቀትና የላፕቶ ኮምፒውተር ሽልማት የተበረከተ ሲሆን:-
#ከዞን ተ/ጽ/ቤቶች
ምስራቅ ጎጃም= 1ኛ፣ ሰሜን ሸዋ= 2ኛ፣ ማዕከላዊ ጎንደር=3ኛ የወጡ ሲሆን
#ከሪጂኦፓሌታንት #ከተማ አስተዳድሮች
ባህርዳር ከተማ =1ኛ ፣ ደብረብርሃን 2ኛ ፣ጎንደር ከተማ =3ኛ
በመውጣት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ነሃሴ 27/2018 ዓ.ም
ባህርዳር

02/09/2026
 #ይህ የኢትዮጵያ የውኃ ማማ የሆነው ፣ ጎጃም ዕንብርት ላይ የሚገኘው ጮቄ ተራራ ከፊል ገፅታው ነው! #የአለምን ትኩረት የሳበው ድንቅ የተፈጥሮ ውበት ያደረበት ስፍራ ! #የአለም ምረጥ የቱ...
01/09/2026

#ይህ የኢትዮጵያ የውኃ ማማ የሆነው ፣ ጎጃም ዕንብርት ላይ የሚገኘው ጮቄ ተራራ ከፊል ገፅታው ነው!

#የአለምን ትኩረት የሳበው ድንቅ የተፈጥሮ ውበት ያደረበት ስፍራ !
#የአለም ምረጥ የቱሪዝም መንደር የተባለለት ውብ ቦታ !!

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara National Regional State Environment & Forest Protection Authority posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share