Amhara Communications

Amhara Communications Ensure smooth flow of information between the Regional Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information

Objectives

According to this Proclamation the office shall have the following objectives;
1. Ensure smooth flow of information between the Regional Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information and actively participate in the country’s affairs and, in particular, facilitate the creation of equal opportunities for those people and of the comm

unity that need special support in accessing government information;
2. Enhance the responsiveness of the Regional Government to the needs of the society throught maintaining an efficient and effective communication and information flow that serve the Regional Government organs and public sectors as a whole;

3. Promote awareness of the opportunities that the country’s developmental democratic system has brought the Region and how to fully access them;
4. Putting the constitutions basic principles and values on the community in wide and continuous way;
5. Helping awareness of the outside community with a view to develop its good will towards the Amhara Region to properly understand the historical heritages and cultural values of the region as well as the new reality emerging from the ongoing changes;


2. Helping awareness of the outside community with a view to develop its good will towards the Amhara Region to properly understand the historical heritages and cultural values of the region as well as the new reality emerging from the ongoing changes;

"ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የአማራ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ትልቅ ዋጋ ከፍሏል" በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤትበአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ...
02/06/2026

"ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የአማራ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ትልቅ ዋጋ ከፍሏል" በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል። ምክር ቤቱ የአማራ ሕዝብ ለዴሞክራሲ በከፈለው መሥዋዕትነት ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን አስታውቋል።

23 የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚገኙበት ይህ ምክር ቤት፣ ምርጫው በነፃነት እና ያለምንም ተጽዕኖ የተካሄደ እና ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ መሆኑን ገልጾ፣ ለመላው የአማራ ሕዝብ እና ለምርጫው ስኬት ድርሻ ለነበራቸው አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴሃን) ሊቀመንበር እና የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ እንደገለጹት፣ ምርጫው ዜጎች ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤትነታቸውን ያረጋገጡበት እና ለሀገራችን የዴሞክራሲ ልምምድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ታሪካዊ ክስተት ነው።

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተዓማኒ ሆኖ መከወኑን የገለጹት ሰብሳቢው፣ በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ብለዋል።

ሕዝቡ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በነቂስ ወጥቶ መሳተፉን እና "ይሆነኛል፤ ይበጀኛል" የሚለውን መምረጡን አቶ ተስፋሁን ጠቁመዋል። ምርጫውን ለማደናቀፍ ከውስጥም ከውጭም ጥረቶች ቢደረጉም፣ በጀግናው የፀጥታ ሠራዊት ማክሸፍ በመቻሉ ለሁሉም የፀጥታ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድኅረ-ምርጫ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን በፀጋ ለመቀበል ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን አቶ ተስፋሁን አሳስበዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሃገራዊ ምርጫ፣ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ፍጹም በሆነ ሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።​የመምሪያው...
02/06/2026

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሃገራዊ ምርጫ፣ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ፍጹም በሆነ ሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

​የመምሪያው አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኡመር መሀመድ እንደገለጹት፤ በአስተዳደሩ በሚገኙ 3 የምርጫ ክልሎች እና 396 የምርጫ ጣቢያዎች የተካሄደው ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሰላማዊ፣ ስልጡን እና ስኬታማ በሆነ መንገድ ተጠናቋል ብለዋል።

ዋና ኢንስፔክተር ኡመር መሀመድ ​በብሔረሰብ አስተዳደሩ የተካሄደው ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ እና ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ እንዳሉት

​ለመላው ሰላም ወዳድ ሕዝባችን፣ከምርጫው መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ማጠቃለያው ድረስ ሕግን በማክበር፣ ሰላምን በማስቀደም እና ከፍተኛ የዜግነት ኃላፊነት ስሜት በማሳየት ለቆማችሁ፤

​ለጸጥታ አካላት በሙሉ፣የሕዝብን ደህንነት ለመጠበቅና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ሌት ተቀን ያለመታከት በቁርጠኝነት ለደከማችሁ መላው የፖሊስ፣ የፖሊስ አጋዥ እና በየደረጃው ለምትገኙ የመንግሥት መዋቅሮች፤

​ለሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች፣ በሕዝቡ መካከል የሰላም፣ የፍቅር እና የደህንነት እሴቶች እንዲጎለብቱ በማስተማር እና በማስታረቅ ግንባር ቀደም ሚና ለተጫወታችሁ፤

​ለባለድርሻ አካላት፦ በሂደቱ ላይ ንቁ ተሳትፎ ላደረጋችሁ መላው አካላት በሙሉ፤ ​በራሴ እና በፖሊስ መምሪያው ስም ከልብ የመነጨ የላቀ ምስጋናዬን እና አክብሮቴን አቀርባለሁ ብለዋል።

Oromo zone communication/kominikeeshini mootummaa Godina saba oromoo

"ሰባተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተጠናቋል።" ኮ/ር ደርበዉ አዳነየሰባተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት በከተማችን ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተከናዉኗል ያሉት የወልድያ ...
02/06/2026

"ሰባተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተጠናቋል።" ኮ/ር ደርበዉ አዳነ

የሰባተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት በከተማችን ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተከናዉኗል ያሉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ደህንነት መምሪያ ኃላፊ ኮ/ር ደርበዉ አዳነ ተናገሩ።

ኮማንደር ደርበዉ እንዳሉት፤ ህዝባችን ያለምንም ስጋት ድምጹን እንዲሰጥ የጸጥታ መዋቅራችን ከፍተኛዉን ሚና ተጫዉታል ብለዋል።

የጸጥታ መዋቅሩ እንቅልፍ ሳያምረዉ ፣ብርድና ቁሩ ሳይበግረዉ ምርጫዉን ሊያደናቅፉ የሚችሉ አካላትን በንቃት በመጠበቅና በመከላከሉ ድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን ሰላማዊ እንዲሆን አስችሎታል ብለዋል።

ህዝቡም መንግስት ለመመስረት የሚያስችለዉን ድምጹን በሰአቱ ተገኝቶ መስጠቱ ምን ያህል ህግ አክባሪ እንደሆነ እና ለህገ-መንግስታዊ ስርአት ተገዥ መሆኑን የሚያሳይ በመሆኑ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

በመጨረሻም የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ሰላማዊ እንዲሆን ለተሳተፉ የጸጥታ አካላት በሙሉ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

መረጃው የወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ነው።

የወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ጊዜአዊ የምርጫ ውጤት እየተመለከቱ ነው።በወልድያ ከተማ ምርጫ ክልል በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ውጤቶች እየተገለጹ ይገኛሉ።የወልድያ ከተማ ነዋሪዎችም ጊዜያዊ የም...
02/06/2026

የወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ጊዜአዊ የምርጫ ውጤት እየተመለከቱ ነው።

በወልድያ ከተማ ምርጫ ክልል በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ውጤቶች እየተገለጹ ይገኛሉ።

የወልድያ ከተማ ነዋሪዎችም ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶችን በየምርጫ ጣቢያዎቹ እየተመለከቱ ነው።

አሚኮ በከተማዋ ተዘዋውሮ በተመለከተባቸው የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ ጊዜያዊ ውጤቶች ግልጽ በኾነ ቦታ ተለጥፈው ሕዝቡ እየተመለከታቸው መኾኑን ታዝቧል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የቆቦ ከተማ ፖሊስ  ጽ/ቤት አስታወቀ።በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ  7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የከተማው  ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ፈን...
02/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የቆቦ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ 7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ፈንታው ውዱ አሳውቀዋል።

አዛዡ እንደተናገሩት፤ በከተማው የተካሄደው ምርጫ ያለምንም የጸጥታ ችግር በትላንትላው እለት ሲካሄድ ውሎ በሰላም ተጠናቋል ብለዋል።

ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን ለሰሩ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፤ለፌዴራል ፓሊስ፣ለከተማው የጸጥታ መዋቅር፤ለምርጫ አስፈጻሚዎች እና ለህዝቡ ምስጋና አቅርበዋል።

North Wollo Communication ሰሜን ወሎ ኮሙኒኬሽን

በደብረ ብርሃን ከተማ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ መኾን ጀምሯል።​በደብረ ብርሃን ከተማ በሚገኙ የተለያዩ ምርጫ ጣቢያ ማኅበረሰቡ የ...
02/06/2026

በደብረ ብርሃን ከተማ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ መኾን ጀምሯል።

​በደብረ ብርሃን ከተማ በሚገኙ የተለያዩ ምርጫ ጣቢያ ማኅበረሰቡ የተለጠፈውን የድምጽ ውጤት እየተመለከተ ነው።

"ማንም ይመረጥ ማን የሕዝብ ድምጽ ማክበር ይገባል" የቆቦ ከተማ ነዋሪዎችበሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤት ለሕዝብ ይፋ እየተደረገ ይገኛል።የምርጫ...
02/06/2026

"ማንም ይመረጥ ማን የሕዝብ ድምጽ ማክበር ይገባል" የቆቦ ከተማ ነዋሪዎች

በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤት ለሕዝብ ይፋ እየተደረገ ይገኛል።

የምርጫ ጣቢያዎችን ጊዜያዊ ውጤት ሲመለከቱ አሚኮ ያገኛቸው የቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ምርጫው ነፃ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ኾኖ በመጠናቀቁ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አጠቃላይ ውጤቱን እስከሚያሳውቅ ድረስ በትዕግሥት እንደሚጠብቁ ጠቁመው "ማንም ይመረጥ ማን የሕዝብ ድምጽ ሊከበር ይገባል" ብለዋል።

የምርጫውን ውጤት በጸጋ መቀበል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግድ መኾኑንም ነው ነዋሪዎቹ ያስረዱት።

ከምርጫው በኋላ ከሚመሠረተው መንግሥት ጋር ሕዝቡ በልማት እና በሰላም ዙሪያ ተባብሮ መሥራት እንዳለበትም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

በሰሜን ሸዋ ዞን አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ማጀቴ/መኮይ/ ምርጫ ክልል ስር ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራው ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤቶች መለጠፍ ጀምረዋል።
02/06/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ማጀቴ/መኮይ/ ምርጫ ክልል ስር ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራው ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤቶች መለጠፍ ጀምረዋል።

መራጩ የምርጫ ጣቢያዎችን ጊዜያዊ ውጤት እየተመለከተ ነው።===በሰሜን ሸዋ ዞን አሳግርት ወረዳ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ በተደረገባቸው ምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ውጤቶችን እየተመለከቱ ይገኛል።በትናንት...
02/06/2026

መራጩ የምርጫ ጣቢያዎችን ጊዜያዊ ውጤት እየተመለከተ ነው።
===
በሰሜን ሸዋ ዞን አሳግርት ወረዳ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ በተደረገባቸው ምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ውጤቶችን እየተመለከቱ ይገኛል።

በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በአሳግርት ወረዳ ጫጫ ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

በዚህም መራጩ ጊዜያዊ ውጤቶችን በምርጫ ጣቢያዎችና ለሕዝብ እይታ ግልጽ በሆኑ ቦታዎች እየተመለከተ ነው።

Asagirt Communication - አሳግርት ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን

‎በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ በሊበን የምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራው ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤቶች እየተገለጹ ነው።‎‎የወረዳው ነዋሪዎችም በየምርጫ ጣቢያዎች የ...
02/06/2026

‎በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ በሊበን የምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራው ተጠናቅቆ ጊዜያዊ ውጤቶች እየተገለጹ ነው።

‎የወረዳው ነዋሪዎችም በየምርጫ ጣቢያዎች የተለጠፈውን ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት እየተመለከቱ ይገኛሉ።

Address

Amhara Region
Bahir Dar
P.O.BOX607

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Communications:

Share