Amhara Communications

Amhara Communications Ensure smooth flow of information between the Regional Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information

Objectives

According to this Proclamation the office shall have the following objectives;
1. Ensure smooth flow of information between the Regional Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information and actively participate in the country’s affairs and, in particular, facilitate the creation of equal opportunities for those people and of the comm

unity that need special support in accessing government information;
2. Enhance the responsiveness of the Regional Government to the needs of the society throught maintaining an efficient and effective communication and information flow that serve the Regional Government organs and public sectors as a whole;

3. Promote awareness of the opportunities that the country’s developmental democratic system has brought the Region and how to fully access them;
4. Putting the constitutions basic principles and values on the community in wide and continuous way;
5. Helping awareness of the outside community with a view to develop its good will towards the Amhara Region to properly understand the historical heritages and cultural values of the region as well as the new reality emerging from the ongoing changes;


2. Helping awareness of the outside community with a view to develop its good will towards the Amhara Region to properly understand the historical heritages and cultural values of the region as well as the new reality emerging from the ongoing changes;

የሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ለልምድ ልውውጥ ባህርዳር ከተማ ገቡ፤​በሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ በአቶ ሄኖክ ሙሉነህ የተመራ የአመራርና...
04/09/2026

የሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ለልምድ ልውውጥ ባህርዳር ከተማ ገቡ፤

​በሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ በአቶ ሄኖክ ሙሉነህ የተመራ የአመራርና ባለሙያዎች ቡድን ለስራ ጉብኝትና ለልምድ ልዉዉጥ ባህርዳር ከተማ ገብቷል።

​የጉብኝት ቡድኑ በባህርዳር በላይ ዘለቀ አየር ማረፊያ ሲደርስ በአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ፣ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጋዜጠኛ ሙሉቀን ሰጥዬን ጨምሮ የቢሮዉ ምክትል ቢሮ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገዉላቸዋል።

​ቡድኑ በባህርዳር በሚኖረው ቆይታ ከአማራ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ እና ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ በመምከር የልምድ ልውውጥ እና የአጋርነት ስምምነትም ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et

"አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" የምዕራብ ደምቢያ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ጽ/ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነዉን የተማሪዎች ቁሳቁስ በ89 ሺህ 900 ብር...
04/09/2026

"አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ"

የምዕራብ ደምቢያ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ጽ/ቤት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነዉን የተማሪዎች ቁሳቁስ በ89 ሺህ 900 ብር ገዝቶ ርክክብ አደረገ።

በወረዳው የተማሪዎችን የመማሪያ ቁሳቁስ በማሟላት፣ የትምህርት ጉዞአቸውን በማበረታታትና በአጠቃላይ የትምህርት ድጋፍን በማጠናከር የሚደረገው ይህ ተግባር ትምህርት የሁሉም ሀላፊነት ነው የሚለውን እሳቤ በተግባር በማረጋገጥ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ድጋፉን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ከተቋሙ ሙያተኛች 89 ሺህ 900ብር በመሰብሰብ 108 ደርዘን ደፍተርና 11 ፓኮ እስክብሪቶ እና በርከት ያሉ የዉሃ ጀሪካኖች ተሰብስቦ ርክክብ ተደርጓል።

መረጃው የምዕራብ ደምቢያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
‎Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
‎Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
‎Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
‎You Tube: https://www.youtube.com/
‎Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
‎Website: https://www.amharacomm.gov.et

የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ያስተላለፉት መልእክት፦የሕብረተሰብ ጤና ድምር ውጤቱ በተሰማራበት ዘርፍ ሁሉ ውጤታማ ተግባር የሚከውን እና ለሀገሩ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚተጋ አም...
04/09/2026

የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ያስተላለፉት መልእክት፦

የሕብረተሰብ ጤና ድምር ውጤቱ በተሰማራበት ዘርፍ ሁሉ ውጤታማ ተግባር የሚከውን እና ለሀገሩ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚተጋ አምራች ሕብረተሰብ መገንባት ነው።

ኢትዮጵያን ላለፉት 100 ዓመታት ያገለገለውን፣ ታሪካዊ ወረት እና ዘመናዊ አቅምን ያጣመረውን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን የሥራ እንቅስቃሴ ዛሬ ተመልክተናል።

የሕብረተሰብን ጤና መጠበቅ ለዘላቂ ሀገራዊ ብልጽግና መሠረት ነው። ተቋሙም በወረርሽኝ ልየታ፣ በበሽታ ክትትልና ምላሽ፣ በላብራቶሪ፣ በምርምር፣ በዲጂታላይዜሽን እና በጤና ስጋት ዝግጁነት የሀገሪቱን የጤና ሥርዓት በጥንካሬ እየደገፈ ይገኛል።

በክልሎች የድንገተኛ ሕብረተሰብ ጤና አደጋ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከላትን ማቋቋሙና የሪፈራል ላብራቶሪዎችን ማስፋፋቱ የሀገሪቱን የጤና ዝግጁነት አቅም እያጠናከረ ያለ ወሳኝ ተግባር ነው።

በቀጣይም የአፍሪካ የሕብረተሰብ ጤና የልህቀት ማዕከል ለመሆን በከፍተኛ ትጋት እየሠራ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪም የዓለም የጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል በመሆን ዓለም አቀፍ ሚናውን ለማጠናከር ብርቱ ጥረት እያደረገ ነው።

የትላንትን ታሪክ ጠብቆ፣ ዛሬን በዘመናዊነት ዋጅቶ፣ ወደ ነገ የሚገሰግስ እንደዚህ ያለ ተቋምን መደገፍና ማጠናከር ለነገ የማንለው ተግባር ነው። ኢንስቲትዩቱ የሀገርን ብልፅግና ለማፋጠን ወሳኝ አቅም በመሆኑ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
‎Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
‎Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
‎Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
‎You Tube: https://www.youtube.com/
‎Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
‎Website: https://www.amharacomm.gov.et

ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ፤‎‎በጉባላፍቶ ወረዳ የመማሪያ ቁሳቁስ መግዛት ለማይችሉ ተማሪዎች የሚውል የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።‎‎ድጋፉ የተደረገው...
04/09/2026

ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ፤

‎በጉባላፍቶ ወረዳ የመማሪያ ቁሳቁስ መግዛት ለማይችሉ ተማሪዎች የሚውል የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።

‎ድጋፉ የተደረገው “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሃሳብ በወረዳው እየተካሄደ ባለው የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ አካል ነው።

‎በመርሃ ግብሩ የተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችና ግለሰቦች የመማሪያ ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ በተለይም የቁሳቁስ እጥረት ለሚያጋጥማቸው ተማሪዎች ለማድረስ እየሠሩ ይገኛሉ።

‎በዕለቱ DEC የተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ፕሮጀክት ለጉባላፍቶ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት 6 ሺህ 769 ደርዘን ደብተር፣ 362 ፓኮ እስክሪብቶ፣ 1 ሺህ 622 ፓኮ እርሳስ፣ 9 ሺህ 736 ማስመሪያዎች፣ 9 ሺህ 736 ላጲሶች እና 9 ሺህ 736 መቅረጫዎች ድጋፍ አድርጓል።

‎የጉባላፍቶ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ደሡ እንደገለጹት፤ ድጋፉ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመንን የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ሳይገጥማቸው እንዲጀምሩ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የመማሪያ ቁሳቁስ ማሰባሰቡና የበጎ ፈቃድ ተሳትፎው እንደሚጠናከር ያስታወቁት ኃላፊው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው በትምህርት ዘመኑ እድሜው ለትምህርት የደረሰ ህጻን በመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታ እንዳይለይ ባለሀብቶችና መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ መልእክት አስተላልፈዋል።

‎ከዚህ በፊት የጉባላፍቶ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤትና ሌሎች ድርጅቶች ባደረጉት የበጎ ፈቃድ ተሳትፎ 558 ደርዘን ደብተርና 168 ፓኮ እስክሪብቶች መሰባሰባቸውም ተገልጿል።

መረጃው የጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et

የፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት በሊቦከምከም ወረዳ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት የትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመረ።የፌዴራል ፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት በአማራ ክልል በደቡብ ጎን...
04/09/2026

የፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት በሊቦከምከም ወረዳ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት የትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመረ።

የፌዴራል ፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦከምከም ወረዳ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ሊገነባ ነው።

በሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የፌዴራል ፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ.ር) እና ምክትል ዳይሬክተሩ ተፈራ ፈይሳን ጨምሮ የአገልግሎቱ ከፍተኛ ሥራ አሥፈጻሚዎች፣ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኀላፊዎች እና የደቡብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የፌዴራል ተቋማት ወደ ክልሎች ወርደው በዜጎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማኅበረሰቡ ድጋፍ እንዲያደርጉ ባወረዱት አቅጣጫ መሠረት የሚገነባ መኾኑ ተገልጿል።

የሚገነባው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲኾን ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት እንደሚገነባ ተገልጿል።

የፌዴራል ፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት በወረዳው ለአላቦ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ500 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው አንድ ደርዘን ደብተር፣ 12 እስክርቢቶ እና ሌሎች የትምህርት ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል።

በተጨማሪም የሥራ ኀላፊዎቹ በወረዳው ችግኝ ተክለዋል። ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን 10 ሺህ ችግኞችም ለወረዳው አበርክተዋል።

አገልግሎቱ ለችግኞች እና ለትምህርት ቁሳቁስ ድጋፉ ከ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ማድረጉን የፌዴራል ፈተና እና ምዘናዎች አገልግሎት ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ.ር) ተናግረዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et

ሳፋሪኮም በአማራ ክልል እና የርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ መልእክትየአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የሳፋሪ ኮም ከፍተኛ መሪዎችን በጽሕፈት ቤታቸው አወያይተዋል።ሳፋሪ ኮም በአማራ...
04/09/2026

ሳፋሪኮም በአማራ ክልል እና የርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ መልእክት

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የሳፋሪ ኮም ከፍተኛ መሪዎችን በጽሕፈት ቤታቸው አወያይተዋል።

ሳፋሪ ኮም በአማራ ክልል እያከናወናቸው የሚገኙትን የኔትዎርክ ተደራሽነት ሥራዎች፤ ተቋሙ እያከናወናቸው ያለው የማኅበራዊ ኀላፊነት ድጋፎች እና እያጋጠሙ ባሉ ችግሮች ዙሪያ ነው ውይይት ያካሄዱት።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፦ ሳፋሪኮም በክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው ብለዋል። በክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ መስፋፋት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ገልጸዋል።

በቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችም አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

በተጨማሪም በማኅበራዊ ኀላፊነት ላይ እያደረጉት ያለውን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት እና ለመደገፍ የክልሉ መንግሥት በትኩረት እንደሚሠራም አንስተዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሳፋሪኮም በባሕር ዳር ከተማ ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ እና ለባሕር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥልጠና ማሽኖችን ድጋፍ አድርጓል።

የሳፋሪኮም የውጭ ግንኙነት ኀላፊ አንዷለም አድማሴ በበኩላቸው፦ ሳፋሪኮም በአማራ ክልል ሰፊ ኢንቨስትመንት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የማኅበራዊ ኀላፊነቱንም በአግባቡ እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የክልሉ መንግሥት ለሳፋሪኮም እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።

በርክክቡ መልዕክት ያስተላለፋት የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ከተማ አሥተዳደሩ ከሳፋሪኮም ጋር በትብብር እንደሚሠራ ገልጸዋል።

ከተባበርን የተለወጠ ዜጋ እንፈጥራለን ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው፤ ሳፋሪኮም ማኅበራዊ ኀላፊነቱን ለመወጣት እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et


በቃብትያ ሁመራ ወረዳ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ፤የቃብትያ ሁመራ ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ፅህፈት ቤት በወረዳው የሚገኙ ባለሀብቶችን በማስተባበር የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድር...
04/09/2026

በቃብትያ ሁመራ ወረዳ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ፤

የቃብትያ ሁመራ ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ፅህፈት ቤት በወረዳው የሚገኙ ባለሀብቶችን በማስተባበር የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

ፅህፈት ቤቱ ባለሀብቶችን በማስተባበር ባሰባሰበው ገንዘብ 100 ደርዘን ደብተር፣ 20 የደብተር ቦርሳዎች እና 30 ባኮ እስክሪብቶ በመግዛት ለወረዳው ትምህርት ፅህፈት ቤት አስረክቧል።

በተመሳሳይ የወረዳው መንገድና ትራንስፖርት ሠራተኞች 16 ደርዘን ደብተር 3 ባኮ እስክሪብቶ ሰጥተዋል።

የተደረገው ድጋፍ በኢኮኖሚ አቅም ደካማ ለሆኑ ተማሪዎች በመሰራጨት በትምህርት ሂደታቸው የሚያጋጥማቸውን የቁሳቁስ እጥረት ለመቅረፍ እንደሚውል ተገልጿል።

መረጃው የቃብትያ ሁመራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ኘው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et

በደቡብ ጎንደር ዞን ሰላምን ሲያውኩ የነበሩ ጽንፈኞች ተደመሰሱ።በደቡብ ጎንደር ዞን የተሰማራው የምሥራቅ ዕዝ ኮር አንድ መቶ ሰባት ፅንፈኞችን ተከታትሎ ደምስሷል። ኮሩ ከነሐሴ 01 አስከ ነሐ...
04/09/2026

በደቡብ ጎንደር ዞን ሰላምን ሲያውኩ የነበሩ ጽንፈኞች ተደመሰሱ።

በደቡብ ጎንደር ዞን የተሰማራው የምሥራቅ ዕዝ ኮር አንድ መቶ ሰባት ፅንፈኞችን ተከታትሎ ደምስሷል። ኮሩ ከነሐሴ 01 አስከ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ባካሄደው የተቀናጀ የፀረ ሽምቅ ኦፕሬሽን 51 ፅንፈኞች ሲደመሰሱ፣ 24 ቆስለዋል፣ 32 በተለያየ መንገድ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ኮሩ ባካሄደው ሕግ የማስከበር እርምጃ የተለያዩ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች፣ የነፍስ ወከፍ እና የቡድን መሳሪያ ተተኳሾች፣ የመገናኛ ሬድዮዎች እና ከኅብረተሰቡ ዘርፎ ሲገለገልባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

ከተደመሰሱት መካከል፣ ግዜ ግርማ የተባለ የፅንፈኛዉ ቡድን የአንዳቤቴ ብርጌድ የነሱ መዋቅር ፍርድ ቤት ኀላፊ፣ ሙጨ ታምር የአንበሳዉ ጋይንት ክፍለ ጦር አደረጃጀት ዘርፍ ኀላፊ፣ ሽሻነዉ ጠጋ የአንበሳዉ ጋይንት ሻለቃ አዛዥ ይገኙበታል።

የፅንፈኛዉን የጥፋት ዓላማ የተረዱ 12 አመራርና አባላት የሰላምን አማራጭ ተቀብለዉ የገቡ ሲኾን ከነዚህም ውስጥ ቻሌ አለባቸዉ የእስቴ ዴንሳ በነሱ አጠራር ኮር ዘመቻ የነበረ እና አማረ ደሴ ሞላ ሻለቃ መሪ የነበረ ይገኙበታል። ታጣቂዎቹ እንደተናገሩት፣ በፊት የፅንፈኛውን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በመከተል እና በመደናገር ገብተው ነበር። አሁን ላይ ግን እውነታውን በየዕለት ሥራዎቹ ስለተረዱና ቡድኑ የሚሠራውን ግፍ በቅርበት ስላዩ፣ ለአማራ ሕዝብ ነፃነት እንዋጋለን እያለ ግን ሕዝብን ሰላም እያሳጡ እንደኾነም ስለተረዱ የጽንፈኞችን ሥራ ሙሉ በሙሉ ጠልተነዋል ብለዋል። ሰላም ይሻላል በማለትም የሰላምን አማራጭ ተቀብለው መግባታቸውን ገልጸዋል።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ባካሄደው ፀረ-ሽምቅ ስምሪት የደቡብ ጎንደር የፀጥታ ኃይል፣ መሪዎች እና ሰላም ወዳዱ ሕዝብ ከፍተኛ ሚና መጫዎታቸውም ተገልጿል።

መረጃው የምሥራቅ ዕዝ ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et

"ሙዚየሙ ተመራማሪዎቻችን በዳኝነት እና በፍትሕ ሥርዓቱ ታሪክ ውስጥ ያለፈውን ረጅም ሂደት በአንድ ቦታ ላይ ለማግኘት ያስችላቸዋል" መንገሻ አየነ (ዶ.ር)የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳ...
04/09/2026

"ሙዚየሙ ተመራማሪዎቻችን በዳኝነት እና በፍትሕ ሥርዓቱ ታሪክ ውስጥ ያለፈውን ረጅም ሂደት በአንድ ቦታ ላይ ለማግኘት ያስችላቸዋል" መንገሻ አየነ (ዶ.ር)

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት እና የፍትሕ አካላትን ታሪክ ጠብቆ ለማቆየት፣ በፍትሕ ዘርፉ ተሳታፊ ለሆኑ ዳኞች፣ ዐቃቤ ሕጎች፣ ፖሊስ፣ ጠበቆች እና የሕግ ተማሪዎች የእውቀት ምንጭ የሚሆን፣ የዳኝነት እና የፍትሕ አካላት በማሕበረሰብ ግንባታ ላይ ያላቸውን ሚና ማኅበረሰቡ እንዲረዳ የሚያስችል እና እምነት የሚያሳድግ፣ ለተመራማሪዎች የግብአት ምንጭ የሚሆን፣ ትውልድ የፍትሕ ሥርዓት ከየት ጀምሮ የት እንደደረሰ እንዲረዳ የሚያስችል የፍትሕ ሙዚየም አደራጅቶ ለጎብኝዎች ክፍት አድርጓል።

በሙዚየሙ ውስጥም፦ ፍትሐ ነገሥትን ጨምሮ የመጀመሪያ የተጻፈ ሕገ መንግሥት፤ የመጀመሪያ የዳኝነት እና የፍትሕ አካላት ማቋቋሚያ ሕጎች ፣ ቀደምት ውሳኔዎች፣ ፎቶዎች እና አልባሳቶች የያዘ፤ የሕግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ምስለ ችሎት የሚያካሂዱበትን አዳራሽ ጨምሮ ሌሎች ከዳኝነት እና ከፍትሕ ሥርዓቱ ጋር የተያያዙ ታሪካዊ ቁሳቁሶች ይገኛሉ።

በሙዚየሙ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት መንገሻ አየነ (ዶ.ር)፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የገነባው የፍትሕ ሙዚየም " ህያው ላይብረሪ"መሆኑን ጠቅሰው፣ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ጋር በአጋርነት እና በትብብር ለሚሰራው የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የሙዚየሙ መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

ሙዚየሙ ተማሪዎቻችን እና ተመራማሪዎቻችን እንደ ሀገር በዳኝነት እና በፍትሕ ሥርዓቱ ታሪክ ውስጥ ያለፈውን ረጅም ሂደት በአንድ ቦታ ላይ ለማግኘት ያስችላቸዋል ብለዋል።

ይሄንን ማድረግ የነበረባቸው ዩኒቨርስቲዎች ነበሩ ያሉት ዶክተር መንገሻ፣ ትክክለኛ መሪዎች ተቋማትን ይገነባሉ፣ ይህንን ላደረጉ የተቋሙ መሪዎች አመሰግናለሁ ብለዋል።

ለመማር ማስተማሩ እና ለምርምር ሥራዎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የተናገሩት ዶክተር መንገሻ አየን፣ የሙዚየሙ መገንባት እና ሥራ መጀመር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዋነኛ የመረጃ ግብዓት መሆኑን ተናግረዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
‎Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
‎Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
‎Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
‎You Tube: https://www.youtube.com/
‎Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
‎Website: https://www.amharacomm.gov.et

በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገነባው ሙዚየም የኢትዮጵያን የፍትሕ ሥርዓት በዲጅታልና በቁስ ሰንዶ የያዘ ነው።የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተገበራቸው ካሉ የተቋምና የሰው ኃይል ...
04/09/2026

በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገነባው ሙዚየም የኢትዮጵያን የፍትሕ ሥርዓት በዲጅታልና በቁስ ሰንዶ የያዘ ነው።

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተገበራቸው ካሉ የተቋምና የሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና የዘመናዊ ዳኝነት አገልግሎት መስጫ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ በተጨማሪ የሀገሪቱን እና የክልሉን የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ከጥንታዊ አሠራር እስከ ዘመናዊው ሥርዓት የሚዳስስ የፍትሕ ሙዚየም ግንባታ ይገኝበታል።

ለሙዚየሙ የሚሆን ዘመናዊ ሕንጻ ከመገንባት እስከ ማደራጀት እና ለጎብኝዎች ክፍት ማድረግ በርካታ ሂደቶችን አልፏል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ። ሙዚየሙ ርዕሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ፣ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ እና ሌሎችም መሪዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ለጎብኝዎች ክፍት ሆኗል።

በመረሀግብሩ ላይ የሙዚየሙን መገንባት እና መደራጀት አስፈላጊነት ለእንግዶቹ ያስረዱት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው፣ የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓቱ የሀገሪቱ ታሪክ አንድ አካል መሆኑን ገልጸው ፣ ይህንን ታሪክ አደራጅቶ ለትውልድ ለማስተላለፍ፣ ትውልዱ የሀገሪቱን የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ከጅማሮው እስከ አሁን ድረስ መረዳት እንዲኖረው ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሙዚየሙን ለማደራጀት ዘመናዊ ሕንጻ ከመገንባት ጀምሮ፣ ለሙዚየሙ ግብዓት የሚሆኑ ታሪካዊ ሰነዶችን፣ መዛግብትን፣ የፎቶ፣ የድምጽ እና የቁሳቁስ ግብዓት ለመሰብሰብ እና ለማደራጀት ከክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ጨምሮ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሌሎች የሥራ ክፍል ኀላፊዎችን ያካተተ ቡድን ተቋቁሞ ዓመቱን ሙሉ ሲሠራ መቆየቱን አብራርተዋል።

ሙዚየሙ በሀገሪቱ የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ላይ ምርምሮችን ለሚያካሂዱ ተመራማሪዎች፣ የሕግ ተማሪዎች፣ ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ተቋማትና ግለሰቦች በማጣቀሻነት የሚያገለግሉ የሰነድና የምስል ክምችቶች አሉት። ለፖሊሲ እና ሌሎች የዳኝነት እና የፍትሕ ስትራቴጂክ ሰነዶች ዝግጅት የሚያገለግሉ ግብዓቶች የሚገኙበት ማዕከልም ነው ብለዋል።

የፍትሕ ሙዚየሙ በከፊል ዲጂታል ሆኖ የተደራጀ ሲኾን፣ የሕግ ተማሪዎች እና እጩ ዳኞች የሚለማመዱበት ምስለ ችሎት ጨምሮ መደበኛ ችሎት መከታተል የሚችሉበትን የዲጂታል አገልግሎት የያዘ ነው። ሙዚየሙ ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት ተደርጓል።

#አሚኮ

Address

Amhara Region
Bahir Dar
P.O.BOX607

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Communications:

Shortcuts

Share