Visit Amhara

Visit Amhara This page is dedicated to promote the diverse natural, historical & cultural heritages of Amhara region.
(1)

We constantly publish new articles, photos and other helpful information on this page to get you traveling to the Land of Amhara, Ethiopia. Visit Amhara is the official page of Amhara culture & tourism bureau, dedicated to promote the diverse natural, historical & cultural heritages of Amhara region.

ይምርሃነ ክርስቶስ ይምርሃነ ክርስቶስ ከ900 ዓመታት በፊት ከላሊበላ ከተማ 42 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኝ የተራራ ዋሻ ውስጥ የተሰራ እጅግ አስደናቂ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ከ...
02/06/2026

ይምርሃነ ክርስቶስ

ይምርሃነ ክርስቶስ ከ900 ዓመታት በፊት ከላሊበላ ከተማ 42 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኝ የተራራ ዋሻ ውስጥ የተሰራ እጅግ አስደናቂ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ከዛግዌ ዘመነ መንግስት ስመ ገናና ነገሥታት አንዱ በሆኑት ንጉሥ ወቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ የተሰራው ነው፡፡

የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በአሰራር ጥበቡ እጅግ የተለየ ሲሆን ጌጠኛ ድንጋዮች ከላይና ከታች በጥንቃቄ በተጠረቡ ሰፋፊ እንጨቶች የተያያዙና በጠንካራ ኖራ መሰል ማጣበቂያ የተለሰኑ ናቸው፡፡ ወለሉ ጠንካራ በሆነ ጥርብ ድንጋይ የተነጠፈ ሲሆን ታቹ ውሃ(ባህር) ነው፡፡ የጣራው ክፍል ወይም ኮርኒሱ ከእንጨት የተሰራና በመስቀል፣ ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብት ስዕሎች የተንቆጠቆጠ ነው፡፡ በልዩ ሁኔታ የተቀረጹ እና በመስቀልና ሐረግ ቅርጻ ቅርጾች የተጌጡ 22 የሚከፈቱ እና 4 የማይከፈቱ በድምሩ 26 መስኮቶችም አሉት፡፡

ፃድቃኔ ማርያምደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም መካነ ቅዱሳን አንድነት ገዳም በበርካታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ በልዩ ፍቅርና ክብር የምትታይ ገዳም ናት፡፡ ከሰላ ...
29/05/2026

ፃድቃኔ ማርያም

ደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም መካነ ቅዱሳን አንድነት ገዳም በበርካታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ በልዩ ፍቅርና ክብር የምትታይ ገዳም ናት፡፡ ከሰላ ድንጋይ ከተማ ምስራቅ አቅጣጫ 4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ፃድቃኔ ማርያም በአማራ ክልል ከሚገኙ ሀይማኖታዊ የቱሪስት መዳረሻዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአገር ውስጥ ጎብኝ በማስተናገድ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች፡፡ በአጼ ዘርዓያዕቆብ ዘመነ መንግስት በተመሰረተችው ታሪካዊ ገዳም መስከረም 21፣ ህዳር 21፣ ጥር 21፣ ግንቦት 21 እና ነሃሴ 16 ዓመታዊ የክብረ በዓላት ቀናት ናቸው፡፡

ዛሬ ግንቦት 21 ዓመታዊው የደብረ ምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም መካነ ቅዱሳን አንድነት ገዳም ክብረ በዓል ከትላንት ምሽት ጀምሮ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡

እንኳን አደረሳችሁ!

𝐕𝐢𝐬𝐢𝐭 𝐋𝐚𝐥𝐢𝐛𝐞𝐥𝐚
28/05/2026

𝐕𝐢𝐬𝐢𝐭 𝐋𝐚𝐥𝐢𝐛𝐞𝐥𝐚

ለባህር ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት የሰጠው የዘንባባ ፓርክ ቀደምት የከተማዋን መንደሮች በሚዘክር እና አሁናዊ ውበቷን በሚያጎላ መንገድ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ 🌴🌴🌴ውቢቷ ባህር ዳ...
28/05/2026

ለባህር ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት የሰጠው የዘንባባ ፓርክ ቀደምት የከተማዋን መንደሮች በሚዘክር እና አሁናዊ ውበቷን በሚያጎላ መንገድ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
🌴🌴🌴
ውቢቷ ባህር ዳር💕

እንኳን ለ1447ኛው የአረፋ በዓል አደረሳችሁ።መልካም በዓል❗
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የአረፋ በዓል አደረሳችሁ።
መልካም በዓል❗

መንዝ ጓሳመንዝ ጓሳ ከደብረ ብርሃን 152 ኪ.ሜ ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መሃል ሜዳ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ የማህበረሰብ አቀፍ ጥብቅ ስፍራ ነው፡፡ ጥብቅ ስፍራው ስያሜውን ...
26/05/2026

መንዝ ጓሳ

መንዝ ጓሳ ከደብረ ብርሃን 152 ኪ.ሜ ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መሃል ሜዳ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ የማህበረሰብ አቀፍ ጥብቅ ስፍራ ነው፡፡ ጥብቅ ስፍራው ስያሜውን ያገኘው በአካባቢው በብዛት ከሚበቅለው የጓሳ ሳር ሲሆን በውስጡም ቀይ ቀበሮ እና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ የተለያዩ የዱር እንሰሳት፣ 14 የሚሆኑ ብርቅዬ አዕዋፍት እና በዛ ያሉ የዕፅዋት ዝርያዎችን ይገኙበታል፡፡

ድንቅ መልክዓ ምድራዊ ገጽታ ያለው የመንዝ ጓሳ ጥብቅ ስፍራ ብዝሃ ሕይወት ሀብት ከ400 ዓመታት በላይ የተጠበቀው እና ዛሬን የደረሰው በአካባቢው ማህበረሰብ ነው፡፡ ማህበረሰቡ አካባቢውን ከመጠበቅ ባሻገር ጎብኝዎችን የሚያስተናግድ የማህበረሰብ ሎጅ በጥብቅ ስፍራው ያለው ሲሆን ለእንግዶች ተወዳጅ ባህላዊ ምግቦች በማቅረብ ይታወቃል፡፡

ጣና ሐይቅ - የኢትዮጵያ ጌጥየጣና ሐይቅ ከተፈጥሯዊ ፋይዳና ውበቱ ባልተናነሰ በምስጢራዊነቱ እንዲሁም በታሪክና ሀይማኖት ማህደርነቱ ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ሐይቅ ነው፡፡ በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ እ...
25/05/2026

ጣና ሐይቅ - የኢትዮጵያ ጌጥ

የጣና ሐይቅ ከተፈጥሯዊ ፋይዳና ውበቱ ባልተናነሰ በምስጢራዊነቱ እንዲሁም በታሪክና ሀይማኖት ማህደርነቱ ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ሐይቅ ነው፡፡ በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ እንደተፈጠረ የሚታመነው ጣና በአማካኝ ከሰሜን ወደ ደቡብ 75 ኪ.ሜ፣ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ደግሞ 60 ኪ.ሜ ይረዝማል፡፡ አማካኝ ስፋቱ ደግሞ 3600 ስኩየር ኪሎ ሜትር ሲሆን ጥልቀቱ 9 ሜትር ነው፡፡ ጣና በአፈጣጠሩ እና ከባሕር ወለል በላይ 1830 ሜትር ከፍታ ላይ በመገኘቱ ከተራራ ላይ ሐይቆች የሚመደበው ሲሆን ከሰሜን ሰፋ ያለና ወደ ደቡብ እየጠበበ የሚመጣ በልብ ቅርጽ አምሳል የተፈጠረ አስገራሚ ሐይቅ ነው፡፡

ከክርስቶስ ልደት በፊት በ5ኛው ክፍለ ዘመን ስለጣና የጻፈው የአቴናው ድራማ ጸሐፊ ኤስኪለስ “መዳብ የተቀባው ሐይቅ፤ የኢትዮጵያ ጌጥ” ይለዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያንም ስለ ጣና በአፈ-ታሪክ፣ በትውፊት እና በሀይማኖት ብዙ ብለዋል፡፡ ዘረ ደሸቶች የኢትዮጵያ ታሪክ መነሻ ይሉታል፡፡ አንዳንድ ምሁራን እና የሀይማኖት አባቶች ደግሞ የኩሽ ስልጣኔ መሰረት፣ የዮቶር ምድር፣ የኦሪት የመስዋዕት ቦታ፣ የታቦተ ጽዮንና የድንግል ማርያም ማረፊያ፣ የተሰወሩ ቤተ መቅደሶች መገኛ፣ የቅዱስ ያሬድ ምርጫ፣ በመንፈሳዊያን ለተጋድሎ እና ስብሃተ እግዚአብሔር ለማድረስ የተመረጠ ቅዱስ ሐይቅ ይሉታል፡፡

በኢትዮጵያ በስፋቱ ቀዳሚ በሆነው በዚህ ድንቅ ሐይቅ ላይ በሚገኙ ደሴቶች በዋጋ የማይተመኑ ውድ ሀይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቅርሶችን የያዙ 45 የሚሆኑ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ፡፡ ዓመቱን በሙሉም ሀይማኖታዊ ተጓዦችን እና ቱሪስቶች እነዚህን ገዳማት ለመጎብኘት በሐይቁ ላይ ጉዞ ያደርጋሉ፡፡ ጣና ባለው እምቅ የብዝሃ-ህይወት ሀብት የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (UNESCO) በ2007 ዓ/ም “በዓለም ሕይወተ-ክልልነት” ተመዝግቧል፡፡

ይምጡና በጣና ሐይቅ ላይ የማይረሳ ጊዜን ያሳልፉ!

https://t.me/+KEEJOwzdA-s5OTQ8

ታዋቂው ቲክታከር Dylan Page -  የቤተክርስቲያን ህግን በማክበር በቅዱስ ላሊበላ ጉብኝት አደረገ
24/05/2026

ታዋቂው ቲክታከር Dylan Page - የቤተክርስቲያን ህግን በማክበር በቅዱስ ላሊበላ ጉብኝት አደረገ

23/05/2026

በጣና ሀይቅ ላይ የተከሰተውን የጀልባ አደጋ ይመለከታል!
=================
በጣና ሀይቅ ላይ በሰሞኑ ስለተከሰተው የዓሣ ማስገሪያ ጀልባዎች አደጋ በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ገጾች የተዛቡ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ። ተቋማችን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በቦታው ከነበሩ አካላት መረጃዎችን በማጣራት የሚከተለውን እውነታ ለህዝብ ማሳወቅ ይፈልጋል።
አደጋው ግንቦት 12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ገደማ በሀይቁ ላይ በተፈጠረ ከፍተኛ ሞገድ ምክንያት ሁለት የዓሣ ማስገሪያ ጀልባዎች ላይ የተከሰተ የመስጠም አደጋ ነው።
በወቅቱም በአካባቢው የነበሩ ሌሎች ዓሣ አጥማጆች ባደረጉት ፈጣን እና የተቀናጀ ጥረት፣ ተጨማሪ የሰው ህይወት እንዳይጠፋ የነፍስ አድን ስራ ተከናውኗል። ይሁን እንጂ እስካሁን ባለን የተረጋገጠ መረጃ መሰረት በአደጋው የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን በታላቅ ሀዘን እንገልጻለን።
ህብረተሰቡ እና የማህበራዊ መገናኛ ተጠቃሚዎች ትክክለኛውን መረጃ ከሚመለከተው ተቋማት እና ባለሙያዎች ብቻ እንዲወስዱ እና ያልተጣሩ የሀሰት ወሬዎችን ከማሰራጨት እንዲቆጠቡ በጥብቅ እናሳስባለን።

ጣና ቂርቆስበኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ቀደምት ሀይማኖታዊ ቦታዎች መካከል አንዱ የጣና ቂርቆስ ገዳም ነው፡፡ ከኦሪት እስከ ክርስትና የረጅም ዓመት ታሪክ ባለቤት የሆነው ጣና ቂርቆስ ገዳም የሚገ...
20/05/2026

ጣና ቂርቆስ

በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ቀደምት ሀይማኖታዊ ቦታዎች መካከል አንዱ የጣና ቂርቆስ ገዳም ነው፡፡ ከኦሪት እስከ ክርስትና የረጅም ዓመት ታሪክ ባለቤት የሆነው ጣና ቂርቆስ ገዳም የሚገኘው በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ አስተዳደር ከጣና ሐይቅ ምስራቅ ዳርቻ ነው፡፡ ገዳሙ ክረምት ሙሉ በሙሉ በሐይቁ የሚከበብ ሲሆን በበጋ ወቅት ከየብስ ጋር የሚገናኝበት ማራኪ ቀጭን ተፈጥሯዊ መንገድ አለው፡፡

የጣና ቂርቆስ ገዳም ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት የኦሪት መስዋዕት የቀረበበት፣ ታቦተ ጽዮን ለረጅም ዓመታት ያረፈችበት፣ ቅድስት ድንግል ማርያም በስደት ለ13 ወራት የቆየችበት፣ ቅዱስ ያሬድ የዜማ እና ድጓ መጻሕፍቱን የደረሰበት፣ የኢትዮጵያን ውድ ቅርሶችን ለማከማቻ የተመረጠ እንዲሁም ከአራቱ የኢትዮጵያ መናብርት አንዱ የነበረ ድንቅ ሀይማኖታዊ መዳረሻ ነው፡፡

ከባህር ዳር ከተማ የሦስት ሰዓት የጀልባ ጉዞ ርቀት ላይ በሚገኘው ጣና ቂርቆስ ከጥንታዊው የጣና ቂርቆስ ገዳም በተጨማሪ ደምበዛ ቁስቋም፣ ቅዱስ ያሬድ እና ፅዮን ማርያም የሚባሉ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናትም ይገኛሉ፡፡ ጥንታዊውን የኢትዮጵያ ታሪክና ቅርስ ለመረዳት፣ ለሀይማኖታዊ ጉዞ እንዲሁም ማራኪውን የጣና ሐይቅ ምስራቃዊ ዳርቻ ለመመልከት ተመራጭ የሆነውን የጣና ቂርቆስ ገዳም ትጎበኙ ዘንድ ግብዣችን ነው፡፡

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Visit Amhara posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Visit Amhara:

Share