ANRS Bureau of Urban and Infrastructure

ANRS Bureau of Urban and Infrastructure The Bureau is Established by Proclamation No. 280/2021 Issued under the Auspices of the ANRS Council.

22/08/2026

እንኳን ለሻደይ፣ አሸንድየ እና ሶለል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

በክልላችን ከነሐሴ ወር መጀመሪያ አንስቶ በዋግኽምራ፣ በሰሜን ውሎና አካባቢው በድምቀት የሚከበሩት ሻደይ፣ አሸንድየና ሶለል ረጅም ዘመናትን የተሻገሩ የሕዝባችን መገለጫ በዓላት ናቸው፡፡

የሻደይ፣ አሸንድየ እና ሶለል በዓል በልጃገረዶችና በወጣቶች ባሕላዊ ጨዋታ ደምቀው በአደባባይ ይከበራሉ።

ልዳገረድችና ወጣቶች በክረምቱ የለመለሙ ዕፅዋትን በመጠቀም ባሕልና እሴታቸውን የሚገልጹበት እንዲሁም ወደ ብርሃኑ የመስከረም ወር እና አዲስ ዓመት ለመሸጋገር የተስፋና የደስታ ማብሰሪያቸው ነው፡፡

ሻደይ፣ አሸንድየ እና ሶለል የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን የሚስቡ የሕዝባችን ማህበራዊ ቁርኝትና አብሮነት የሚያጠናክሩ የማይዳሰሱ ባሕላዊ ቅርሶቻችን ናቸው።

በዓላቱን ስናከብር ሕዝባችን ለዘመናት ጠብቆ ያቆያቸውን ባህላዊ እሴቶች በማክበርና በማሳደግ፣ ለተከታዩ ትውልድ ትውፊታዊ ይዘታቸውን ጠብቀን ለማስተላለፍ በጋራ በመሥራት ሊሆን ይገባል፡፡

መልካም የሻደይ፣ አሸንድየ እና ሶለል በዓል!

ውቢቷ ባህርዳር!
20/08/2026

ውቢቷ ባህርዳር!

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር    ከተማ  እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ግንባታ በቅርቡ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል።
19/08/2026

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ግንባታ በቅርቡ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል።

የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አሁናዊ ገፅታ!
18/08/2026

የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አሁናዊ ገፅታ!

የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ መገኛ የሆነችውን ደባርቅ ከተማን በጋራ እናልማ!
17/08/2026

የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ መገኛ የሆነችውን ደባርቅ ከተማን በጋራ እናልማ!

በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በፋሲሎ፣ በየካቲት 23 እና በዶና በር ትምህርት ቤቶች ያስገነባቸውን 5 ብሎክ 20 አዳዲስ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች...
17/08/2026

በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በፋሲሎ፣ በየካቲት 23 እና በዶና በር ትምህርት ቤቶች ያስገነባቸውን 5 ብሎክ 20 አዳዲስ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን ገንብቶ አስመረቀ፡፡

በምርቃ ፕሮግራሙ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) እንደገለጹት የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትና ሥራ ፕሮጀክት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል የአነስተኛ ማኅበራዊ ተቋማት ግንባታ የሚጠቀስ ሲሆን እንደ ክልል 73 የመማሪያ ክፍል የተገነቡ ሲሆን የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የምግብ ዋስትና እና ሴፍቲኔት ጽ/ቤት 5 ብሎክ 20 ክፍሎችን የያዘ ት/ቤት ተጠናቆ መመረቁ ለህጻናት ምቹ የመማር ማስተማር ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በዚህ ዘርፍ 6 የሸድ ብሎክ 254 ክፍሎች፣6 አነስተኛ የህዝብ መዝናኛ ፓርክ፣ 4 የህዝብ መጸዳጃ ቤት ግንባታዎችን በማከናወን ሁሉን አቀፍ የከተማ ልማት ላይ እያበረከተ ይገኛል ያሉት ዶ/ር ሞላ መልካሙ በአጠቃላይ በአነስተኛ ማህበራዊ ተቋማት ግንባታ በጀት ከ72ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጓል ብለዋል፡፡

የባሕርዳር ከተማ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው እንደገለጹት ትምህርት ለሀገር ልማት የጀርባ አጥንት ነው ያሉ ሲሆን በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የአፀደ ህፃናት ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ተማሪዎች ሲመጡ ናፍቋቸውና ወደውት የሚማሩባቸው ውብ፣ ጽዱና ማራኪ የማድረግ ሥራ በትኩረት መከናወኑን ገልፀዋል።

የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ነዋሪዎችን በቀጥታ በገንዘብና በሥራ ዕድል ከመደገፍ ባለፈ፣ በሕዝብ ተሳትፎ አማካኝነት እንደ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያና የአረንጓዴ ልማት መሠረተ ልማቶችን በመገንባት የከተማን ገጽታ ለመቀየር በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ ይገኛል ብለዋል ከንቲባው።

ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ በጀት ዓመት በቀጥታ በጀት መድቦ የተሻሉ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ማቀዱን የገለጹት ክቡር ከንቲባው የመማሪያ ክፍሎችንና ቤተ-መጻሕፍትን በማዘመን እንዲሁም ስማርት ክፍሎችን በመፍጠር ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

የባሕርዳር ከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ እመቤት መንግስቱ፤ ልማታዊ ሴፍቲኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የዜጎችን ኑሮ በመቀየርና የከተማዋን ገጽታ በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል። በዛሬው ዕለት በሦስት ትምህርት ቤቶች የተገነቡ 5 ብሎኮች እና 20 የመማሪያ ክፍሎች ተጠናቀው ለመማር ማስተማር ክፍት መደረጋቸውን ኃላፊዋ ገልጸዋል።

ዘጋቢ፡ ሙሉጌታ ስመኝ

የስሜን ተራራዎች መዳረሻዋ ደባርቅ በኮሪደር ልማት ላይ ናት።በከተማዋ እየተሠራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ሚናው የጎላ መኾኑን የደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል።ደባ...
15/08/2026

የስሜን ተራራዎች መዳረሻዋ ደባርቅ በኮሪደር ልማት ላይ ናት።

በከተማዋ እየተሠራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ሚናው የጎላ መኾኑን የደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ደባርቅ ከተማ በሰሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ በቅርብ ርቀት የምትገኝ የተሻለ የቱሪዝም ፍሰት ካላቸው ከተሞች መካከል አንዷ ናት።

የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጌትነት ጸጋዬ ደረጃውን የጠበቀ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በማከናወን ምቹ እና ለነዋሪዎች ተስማሚ አካባቢን ለመፍጠር እየተሠራ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከአካባቢው ማኅበረሰብ በተጨማሪ ወደ ስፍራው ለሚመጡ ጎብኝዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።

ሀሳባቸውን የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች እየተሠራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የቱሪዝም ፍሰቱን ለማነቃቃት እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማቱ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቅቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻልም ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አንስተዋል።

የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር በከተማዋ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ይበልጥ ለማጠናከር በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ለማካሄድ እየሠራ ይገኛል።

Amhara Communications

15/08/2026
15/08/2026
በአማራ ክልል በየዓመቱ በአማካኝ 975 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ለመኖሪያ ቦታ እየተሰጠ ነው።የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር በመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበራት ለተደራጁ የብሎክ እጣ የማውጣት መ...
13/08/2026

በአማራ ክልል በየዓመቱ በአማካኝ 975 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ለመኖሪያ ቦታ እየተሰጠ ነው።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር በመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበራት ለተደራጁ የብሎክ እጣ የማውጣት መርሐ ግብር እያካሄደ ነው።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር መሬት መምሪያ ኀላፊ መልካም ሥራ ካሳው ከተማ አሥተዳደሩ በአራት ሳይቶች ማለትም ወረብ፣ አዲስ ዓለም፣ መኮድ እና ሰልቸን ቦታዎች ለመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

901 ማኅበራት እና በዚህ ውስጥ የተደራጁ 19 ሺህ 698 አባላት የሳይት እና የብሎክ ዕጣ እንደሚያወጡም ተናግረዋል።

ለማኅበራቱ በ1 ሺህ 45 ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ለመኖሪያ ቤት ተነሽ ለኾኑ 2 ሺህ 225 አርሶ አደሮች ከ4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ካሳ የመክፈል ሥራ መከናወኑን አንስተዋል።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ የመኖሪያ ቤት ማደራጀት ተከልክሎ እንደነበር አስታውሰዋል። ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ተግባር የሚያከናውን በኾኑ ክልከላውን በማንሳት ነዋሪዎች እንዲደራጁ እና ቦታ እንዲያገኙ ተሠርቷል ብለዋል።

ከ26 ሺህ በላይ የመኖሪያ ቤት ፈላጊዎች መመዝገባቸውን ነው የተናገሩት። ከዚህ ውስጥ ትክክለኛ መረጃን ያቀረቡ 19 ሺህ 698 ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ማግኘታቸውንም ተናግረዋል።

በቴክኖሎጅ የታገዘ ተደጋጋሚ የማጣራት ሥራ በማከናወን 5 ሺህ 772 የመኖሪያ ፈላጊዎች ትክክለኛ መረጃ የሌላቸው እና ለማጭበርበር በመሞከራቸው እንዲቀነሱ ተደርጓል ነው ያሉት።

1 ሺህ 325 ሰዎች በቅሬታ መልስ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። ተነሽ ከኾኑ ከ2 ሺህ 225 አርሶ አደሮች ውስጥ 1 ሺህ 704 አርሶ አደሮች 500 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ ይሰጣቸዋል ነው ያሉት። በማጣራት የአርሶ አደሮች ልጆች 150 ካሬ ሜትር ቦታ እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

በዘላቂነት ራሳቸውን እንዲያደራጁ እና ቤተሰቦቻቸውን እንዲያግዙ ይሠራል ብለዋል። "ቅድመ ክፍያውን ወደ ካሳ የቀየርነው የማኅበረሰቡን ችግር በመረዳት የቤት ባለቤት እንድትኾኑ ነው" ሲሉም አንስተዋል።

በቀጣይ 67 የቤት ማኅበራትን ለማጣራት እና ቦታ ለመሥጠት እየተሠራ ነው ብለዋል። በቅርቡ አዲስ ማኅበራትን በማደራጀት ቦታ ለመሥጠት እንደሚሠራም ገልጸዋል። ባልተገባ መንገድ እና በማጭበርበር ቦታ ለማግኘት የሚሞክሩ ግለሰቦችን የመቆጣጠር እና ተጠያቂ የማድረግ ተግባር እንደሚከናወንም ተናግረዋል።

"ሠርታችሁ እንድትኖሩበት እና ወልዳችሁ እንድትስሙበት እንጅ እንድትሸጡት የመኖሪያ ቦታ አልሠጠንም እና አደራችሁን ተወጡ" ብለዋል።

የአማራ ክልል ከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ.ር) በክልሉ ከ 2006 እስከ 2018 ዓ.ም 12 ሺህ 673 ነጥብ 70 ሄክታር መሬት ለማኅበረሰቡ የመኖሪያ መሥሪያ ቦታ መሰጠቱን ገልጸዋል። 307 ሺህ 270 ሰዎችም ተጠቃሚ መኾናቸውን አንስተዋል። በክልሉ በአማካኝ በየዓመቱ 974 ነጥብ 9 ሄክታር መሬት ለመኖሪያ ቦታ እንደሚሰጥ ነው የተናገሩት።

መንግሥት የቤት ልማት ፖሊሲን በማውጣት ማኅበረሰቡ የቤት ልማት ተጠቃሚ እንዲኾን እየሠራ ነው ብለዋል። ቁጠባን አጠናክሮ በመቀጠል፤ የከተሞችን የገቢ አቅም በማሳደግ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት፤ የቤት ግንባታ በፍጥነት እንዲጀመር በማድረግ እና የልማት ተነሺዎችም በሚያገኙት ካሳ በአግባቡ እንዲጠቀሙ ማገዝ በቀጣይ ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መኾኑንም አሳስበዋል።

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Bureau of Urban and Infrastructure posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share