Amhara Water and Energy Bureau

Amhara Water and Energy Bureau The bureau established to provide potable water & energy sustainably to the people of Amhara region.

"በአንድ እጅ ሰላም፣ በሌላኛው ልማት" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መከካለኛ መሪዎች በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም እ...
29/08/2026

"በአንድ እጅ ሰላም፣ በሌላኛው ልማት" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መከካለኛ መሪዎች በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ በ2018 በጀት ዓመት ጥራት ያለው ዕቅድ መታቀዱን አስታውሰዋል። ዕቅዱን ስኬታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ መሪዎች ቃል ኪዳን ገብተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል። በትኩረት በተሠራው ሥራ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውንም ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ የፖለቲካ መረጋጋት እና የፓርቲው ቅቡልነት ከፍ እንዲል ከፍተኛ ሥራዎች መተግበራቸውን ገልጸዋል። በጀት ዓመቱ የክልሉ ዋነኛ ችግር የኾነውን የፖለቲካ ጽንፈኝነትን የታገልንበት ነው ብለዋል።

ሀገራዊ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችሉ እሴቶችን የበለጠ ለማጎልበት የሀገራችን እና የክልላችን ሕዝብ የጋራ ርዕይ እንዲኖራቸው የሚያደርጉ ሥራዎች የተሠሩበት እና ሀገራዊ ምክክር በስኬት የተካሄደበት እንደነበርም ገልጸዋል። በጀት ዓመቱ ስኬታማ ምርጫ የተካሄደበት እንደነበርም አንስተዋል።

ሰላምን፣ ፍትሕን እና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሥራ መሠራቱን ገልጸዋል። ከውስጥ እና ከውጭ የተጣመሩ አካላትን ሀገር አፍራሽ አካሄድ ለመግታት ሰፊ ሥራ መሠራቱን ነው የተናገሩት።

በክልሉ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ የተከሰተውን የተደራጀ ወንጀል ለመግታት መሠራቱንም አንስተዋል። ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት መደረጉን ነው የገለጹት። በአንድ እጃችን ሰላም እያስከበርን፣ በሌላ እጃችን ደግሞ ልማት እያለማን ውጤታማ ተግባራትን ሠርተናል ነው ያሉት።

የኑሮ ውድነትን፣ ሥራ አጥነትን እና የኢኮኖሚ መዛባትን ለማስተካከል ተሠርቷል ብለዋል። በማኅበራዊ ዘርፍም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል። በመልካም አሥተዳደር ዙሪያ ውጤታማ ተግባራት ተሠርተዋል፤ በተለይም የአገልግሎት አሠጣጥን ለማሻሻል በትኩረት ተሠርቷል ነው ያሉት። ገቢን ለማሳደግ ጥረት መደረጉንም ገልጸዋል።

ስኬታማ ሥራዎች እንደተከናወኑ ሁሉ ልናልፋቸው የማይገቡ ችግሮችም አሉ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ። የክልሉን የጸጥታ ችግር ለማስተካከል ውጤታማ ሥራዎች ቢከናወኑም አሁንም ጠንካራ ሥራ መሥራት እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። አወንታዊ ጉዳዮችን በማስፋት፤ ውስጣዊ እና ውጫዊ ተጋላጭነትን በመከላከል የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሥራት ይገባል ብለዋል።

መሪዎች በመድረኩ በቂ ግንዛቤ በመያዝ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

አዲሱ በጀት ዓመት መሠረታዊ ለውጥ የምናመጣበት መኾን አለበት ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው። መድ...
29/08/2026

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።

መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር በሁሉም ሴክተሮች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግርዋል።

ክልሉ የገጠሙትን ፈተናዎች ተሻግሮ በኢኮኖሚ እና በልዩ ልዩ የልማት መስኮች ተወዳዳሪ እንዲሆን በሁሉም ዘርፍ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የገለፁት ርእሰ መሥተዳድሩ በሰው ሃብት ልማት፣ በተቋም ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ልማት፣ ሠላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ በኩል የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አስረድተዋል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አክለውም የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅዶችን ለመተግበር የተደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው የተቋማት፣ የአመራሩ እና የባለሙያው የመፈጸም አቅም ማደግ ለሕዝባችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና ወሳኝ መሆኑንም አስረድተዋል።

የጋራ ግንዛቤ ለጋራ ስኬት መሠረት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ከታለመው ርዕይ ለመድረስ ተቋማት ተቀናጅተው መሥራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በመርሐ ግብሩ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የፖለቲካ ስራዎችን አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅድ እያቀረቡ ሲሆን የክልሉ የ2019 በጀት ዓመት የፖለቲካ ስራዎች ዕቅድ እንዲሁም የአሻጋሪ ዕድገት እና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ እንደሚደረግም የተያዘው መርሐ ግብር ያመላክታል።

በአቀስታ ከተማ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነበደቡብ ወሎ ዞን አቀስታ ከተማ አስተዳደር 029 (የነሽ አገር) ቀበሌ ከ5...
29/08/2026

በአቀስታ ከተማ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ

በደቡብ ወሎ ዞን አቀስታ ከተማ አስተዳደር 029 (የነሽ አገር) ቀበሌ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገለጸ።

የከተማዋን እና የአካባቢውን የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ የተቀረፀው ይህ "Water 4 Life" (ውሃ ለህይወት) ፕሮጀክት፣ በወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ (World Vision Ethiopia) አማካኝነት የተገነባ ነው።

የፕሮጀክቱን መጠናቀቅና እርክብክብ አስመልክቶ በተካሄደው ስነ-ስርዓት ላይ የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ ዘለቀ ተሰማ፣ የአቀስታ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የከተማዋ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው አጋር አካላት ተገኝተዋል።

በዕለቱ የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ ዘለቀ ተሰማ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በሰዓት 30,000 ሊትር ውሃ የማቅረብ አቅም ያለው ሲሆን፣ የከተማዋን የውሃ ጥም በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያቃልል ተናግረዋል።

ይህ በአቀስታ ከተማ አስተዳደር እና በወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ትብብር የተገነባው ግዙፍ ፕሮጀክት 5 ኪሎ ሜትር የውሃ መስመር ተዘርግቷል።200 ሜትር ኩብ (200,000 ሊትር) ውሃ የመያዝ አቅም ያለው የነሽ የውሃ ታንከር ተገንብቷል።እንዲሁም 3 የትምህርት ቤት የውሃ ቦኖዎችን ጨምሮ ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጡ በርካታ የውሃ ማከፋፈያዎች ተዘጋጅተዋል።

ይህ ህዝባዊ መሠረተ ልማት ለአቀስታ ከተማ እና አካባቢዋ ነዋሪዎች ትልቅ ተስፋን ያሰነቀ ከመሆኑም በላይ ለዘመናት የቆየውን የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት በጥራት እና በዘላቂነት እንደሚፈታ ታምኖበታል።

የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ለምህንድስና ባለሙያዎች የሚሰጠውን የተግባር ስልጠና አስጀመረ፤​የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ የክልሉን ሕዝብ የመጠጥ ውኃ ፍላጎትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረ...
29/08/2026

የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ለምህንድስና ባለሙያዎች የሚሰጠውን የተግባር ስልጠና አስጀመረ፤

​የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ የክልሉን ሕዝብ የመጠጥ ውኃ ፍላጎትና ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በክልልና በዞን ደረጃ ለሚሠሩ የጥናት፣ ዲዛይን እና ሃይድሮሎጂ ምህንድስና ባለሙያዎች የሚሰጠውን የተግባር ስልጠና ማስጀመሩን ገለጸ።

ከነሐሴ 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ13 ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ ስልጠና በኮምፒውተራይዝድ ዲዛይን፣ በግንባታ ቁጥጥርና ክትትል እንዲሁም በኮንትራት አስተዳደር ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ ስልጠናዉ በፌዴራል ባለሙያዎች የሚሰጥ ነው።

​የስልጠና መድረኩን በይፋ የከፈቱት የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር ኢንጂነር) የመጠጥ ውኃ ለሰው ልጅ ሕልውና መሠረታዊ እንደመሆኑ መጠን በተለይም የአየር ንብረት ለውጥና የደን ጭፍጨፋ ሥጋት በደቀኑበት በአሁኑ ወቅት የዘርፉ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ እጅግ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

የዘርፉን ጥራት ለማስጠበቅ በእውቀትና በክህሎት የበቁ ባለሙያዎች የሚያስፈልጉ በመሆኑ የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ የቢሮው ዋነኛ ትኩረት እንደሆነ የጠቆሙት ቢሮ ኃላፊው፤ ጥራት ያለው የውኃ መረብ ዲዛይን መሥራት፣ የተጀመሩ ግንባታዎችን ጥራትና የጊዜ ገደብ ጠብቆ ማጠናቀቅ እንዲሁም በኢነርጂ ዘርፍ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን ለማኅበረሰቡ ማዳረስ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

አክለውም ሰልጣኞች ከስልጠናው የሚያገኙትን እውቀትና ክህሎት ወደ ታች በማውረድ በወረዳ ደረጃ ለሚገኙ ባለሙያዎች ተመሳሳይ ስልጠና እንዲሰጡና ማኅበረሰቡ የልማት ተቋማቱ ባለቤት እንዲሆን በትጋት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የህዝቡን የመጠጥ ውሀ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የርብ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡የደብረታቦር ከተማ መጠጥ ውሀና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ከባለድርሻና አጋ...
27/08/2026

የህዝቡን የመጠጥ ውሀ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የርብ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

የደብረታቦር ከተማ መጠጥ ውሀና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ከባለድርሻና አጋር አካላት ጋር የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ባንቴ ሁኔ በ2018 በጀት ዓመት የተከናዎኑትን ተግባራ እቅድ አፈጻፀም ሪፖርት እና በተያዘው በጀት ዓመት የሚከናዎኑትን ተግባራት እቅድ አቅርበዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት በርካታ ተግባራት መፈፀማቸውን አንስተው 10 ጥልቅ የውሀ ጉድጓዶች ለማህበረሰቡ የውሀ አቅርቦት አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የከተመዋ የመጠጥ ውሀ አቅርቦት ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመው ለአንድ ሰው በቀን 80 ሊትር ውሀ የሚያስፈልግ ቢሆንም ማቅረብ የተቻለው ግን 24 ሊትር ውሀ መሆኑን ጠቅሰው የውሀ ሽፋኑም 16 ፐርሰንት እንደሆነ አሳውቀው ያለውን የመጠጥ ውሀ ችግር ለመፍታት መተጋገዝ አለብን ብለዋል፡፡

አቶ ባንቴ በተያዘው በጀት ዓመት የሚከናዎኑትን ተግባራት እቅድም ያቀረቡ ሲሆን የውሀ ሽፋንን ማሳደግ፣ የውሀ ብክነትን መቀነስ፣ የውሀ መስመር ብልሽትን መከላከል፣ አዲስ የውሀ ደንበኞችን ማሳደግ፣ ሶስት ጥልቅ የውሀ ጉድጓዶችን ማስቆፈር፣ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በማሻሻል ገቢን ማሳደግ እና ሌሎችንም ተግባራት ለመፈፀም መታቀዱን አመላክተው የህዝቡን የመጠጥ ውሀ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የርብ ውሀ ፕሮጀክት እንዲሰራ ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የተሳተፉ አካላትም በሰጡት ሀሳብ የከተመዋን ህዝብ የመጠጥ ውሀ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የርብ ውሀ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን መተባበር እንደሚገባ ተናግረው ለአጭር ጊዜ መፍትሄ ደግሞ ማህበረሰቡን በማነቃነቅ እና በማሳተፍ ጥልቅ የውሀ ጉድጓዶች እንዲሰሩ ማድረግ አለብን ብለዋል፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣውን የውሀ ቆጣሪ ስርቆት ለመከላከል ህብረተሰቡ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር ሊሰራ እንደሚገባም ጠቁመው እየተከሰተ ያለውን የውሀ ብክነት ለማስቀረት ህብረተሰቡ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት ገልፀው ማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሀ ተጠቃሚ ለማድረግ ሁላችንም በባለቤትነት ይዘን መስራት አለብን ብለዋል፡፡

በመድረኩ ተሳታፊዎች ለተነሱት የተለያዩ ሀሳቦችም አቶ ባንቴ ሁኔ እና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት መልስና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደበበ አክሎግ እንደተናገሩት ከጊዜ ወደ ጊዜ የከርሰ ምድር ውሀ እየቀነሰ መምጣቱን በአንጻሩ የውሀ ፍላጎት እየጨመረ ያለበት ሁኔታ መኖሩን ገልፀው የመጠጥ ውሀን በአግባቡ ለማቅረብ ማህበረሰቡን በማስተባበር እንዲያግዝ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ህዝቡ የሚያነሳውን የርብ ፕሮጀክት ዳር ለማድረስ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ እንደ ፈለጉ ተንቀሳቅሶ ለመስራት የሚስችል ባለመሆኑ ሰላም እንዲመጣ ለማድረግ ሁሉም መስራት እንዳለበት አስገንዝበው ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠር አለብን ብለዋል፡፡

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና የውሀ ድርጅቱ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ደሴ መኮንን በበኩላቸው የከተመዋ ውሀ ተቋም ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን እና አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት አንስተው ስራዎች በተሻለ መንድ እንዲከናዎኑ ለማድረግ መተጋገዝ አለብን ብለዋል፡፡

የህዝቡን የመጠጥ ውሀ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የርብ ፕሮጀክት እውን እንዲሆን ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበው ማህበረሰቡን በማነቃነቅ እንዲሳተፍ እና የውሀ ስራን እንዲያግዝ ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመው እየተፈፀመ ያለውን የቆጣሪ ስርቆት ለመከላከል በቅንጅት መስራት አለብንም ብለዋል፡፡

በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ላላቸው የውሀ ተቋማት እና የውሀ ድርጅቱን በተለያየ መንገድ ላገዙ አካላት እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን ትልቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ደግሞ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል፡፡

"ለጋራ ርዕይ የሚታትር፣ በዓላማ የተግባባ እና የጋራ ግብ ያለው አመራር ማረጋገጥ ተችሏል" ~ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ"አርቆ ማየት አልቆ መሥራት" በሚል መሪ መልዕክት የአማራ ክልል የ...
26/08/2026

"ለጋራ ርዕይ የሚታትር፣ በዓላማ የተግባባ እና የጋራ ግብ ያለው አመራር ማረጋገጥ ተችሏል" ~ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

"አርቆ ማየት አልቆ መሥራት" በሚል መሪ መልዕክት የአማራ ክልል የ2018 በጀት ዓመት የአሻጋሪ እድገትና ዘላቂ የልማት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ እንዳሉት የ2018 በጀት ዓመት በጋራ ትጋትና ጥረት የአሻጋሪ እድገትና ዘላቂ የልማት ዕቅዳችንን ከንድፈ ሃሳብ ባሻገር ተግባራዊ ውጤቶችን ያየንበት ዓመት ነበር ብለዋል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አያይዘውም የአሻጋሪ እድገት እና የዘላቂ ልማት ዕቅዱን በባለቤትነት ይዞ የሚፈጽም፣ በጋራ ርዕይ ላይ የሚታትር፣ በዓላማ የተግባባ እና የጋራ ግብ ያለው አመራር ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።

የተቋማትን የመፈጸም አቅም በማሳደግ እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማላቅ አምራች እና ተወዳዳሪ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መገንባት እንደሚያስፈልግም ርእሰ መሥተዳድሩ አስረድተዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የነበሩ ስኬቶቻችን በማስቀጠል እና የአፈጻጸም ችግሮቻችን በማረም ለቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት በጋራ መቆም እና በዕቅድ ተመሥርተን መፈጸምን ባሕል ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እየተሳተፉበት በሚገኘው በዚህ መድረክ የፓርቲ እና የመንግስት የ2018 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም እቅድ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበትም ተገልጿል።

ከዓመታት መጓተት በኋላ መገጭ የመስኖ ግድብ 33 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውኃ ይዟልለበርካታ ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተት የቆየው የመገጭ ግድብ ፕሮጀክት፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተደረገ...
25/08/2026

ከዓመታት መጓተት በኋላ መገጭ የመስኖ ግድብ 33 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውኃ ይዟል

ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተት የቆየው የመገጭ ግድብ ፕሮጀክት፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተደረገለት ከፍተኛ ክትትልና አገራዊ ርብርብ አሁን ላይ መጠናቀቅ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

✅ መገጭ የመስኖ ግድብ 33 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውሃ ይዟል

✅ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ግንባታ ስራ 94 በመቶ ተጠናቅቋል!

✅ ዋናው ግድብ ሙሌት 9 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ይደርሳል

✅ አሁን ላይ 8 ነጥብ 25 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ተሞልቷል፤

✅ ቀሪው አንድ ነጥብ 15 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ የግድብ ሙሌት በቅርቡ የሚጠናቀቅ ይሆናል

✅ የግድቡ ትርፍ ውኃ ማፋሰሻ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል

✅ መስኖ ውሃ መቆጣጠሪያ ሲቪል ስራ መቶ በመቶ ተጠናቋል

✅ ኤሌክትሮ መካኒካል ስራው አጭር ጊዜ የሚጠናቀቅ ይሆናል

✅የመስኖ ውኃ ማስወጫ፣ መጠንና ኃይል መቆጣጠሪያ ገጠማ ተከናውኗል፣

✅ ለጎንደር ከተማ ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚሆን ውሃ ማስወጫ ቱቦና መቆጣጠሪያ ገጠማ ተጠናቋል

✅ የሎት 2 የወንዝ መቀልበሻ የአናት ስራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል

✅ የሎት 2 የዋና ቦይ 3 ኪሎ ሜትር ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፤

✅ ቀሪ የዋና መስኖ ቦይና ሁለተኛ የመስኖ ቦይ ግንባታ ስራው እየተፋጠነ እንደሚገኝ የመስኖና ቆላማ አከባቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።

የመደመር መንግሥት ሜጋ ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ባለፈ በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳና በሚፈለገው የጥራት ደረጃ የማጠናቀቅ አዲስ የሥራ ባህል እንዲዳብር ያስቻሉ በርካታ የልማት ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

የመገጭ ግድብ ግንባታ በተለይም ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደረገለት ጥብቅ አመራርና ቁጥጥር አጠቃላይ አፈጻጸሙ 94 በመቶ መድረሱ ተገልጿል። ፕሮጀክቱ በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ይጠበቃል።

እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) አደረሳችሁ!!ይህን በዓል የምናከብረው የዓለሙ እዝነት፣ ለሠናዮች መልካሙን አብሣሪ፣ ለተከታዮቻቸው ሐላል እና ...
25/08/2026

እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) አደረሳችሁ!!

ይህን በዓል የምናከብረው የዓለሙ እዝነት፣ ለሠናዮች መልካሙን አብሣሪ፣ ለተከታዮቻቸው ሐላል እና ሐራሙን አስተማሪ የሆኑት ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮና መልካም ሥራ የሚታወስበት፣ የሚዘከሩበትና የሚወደሱበት በመሆኑ ነው።

የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) መልካም ተግባራት ሳይደበዝዙ በድምቀት፣ ሳይሻሩ በህያውነት ዛሬም ድረስ አሉ። ይህን በዓል በጋራ ስናከብር በተሟላ የመልካምነት ዕሴት፣ በፍቅር እና በአብሮነት፣ በሰላም፣ በመተሳሰብ እንዲሁም የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት ሊሆን ይገባል።

የመገጭ ግድብ ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሷል በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የመገጭ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ መድረሱን የመስኖና ቆላ...
25/08/2026

የመገጭ ግድብ ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሷል

በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የመገጭ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ መድረሱን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ የመገጭ የግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ለተውጣጡ ጋዜጠኞች አስጎብኝቷል።

ሚኒስቴሩ የኢትዮጵያን በምግብ ራስን የመቻል ጉዞ የሚያሳኩ የመስኖ ልማት መሰረተ ልማቶችን እያስፋፋ ይገኛል።

ከእነዚህ መሰረተ ልማቶች መካከል በአማራ ክልል ጎንደር አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው መገጭ ግድብ አንዱ ሲሆን ግድቡ ከተጀመረ ረዘም ያለ ጊዜ አስቆጥሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግድቡ በፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረትም በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት ግድቡን ለማጠናቀቅ በተደረገው ርብርብ አሁን ላይ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ደርሷል።

በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የመስኖ ፕሮጀክቶች ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ እንጂነር አሸናፊ ሊካሳ በሰጡት ማብራሪያ ግንባታው በመጓተቱ ምክንያት ግንባታውን ይዞ የነበረው ተቋራጭ በአዲስ እንዲተካ መደረጉን አንስተዋል።

አሁን ላይም ግድቡን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የውሃ መስኖ መቆጣጠሪያው ሲቪል ስራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ጠቁመው፤ የኤሌክትሮ መካኒካል ስራው በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

ግድቡ በአሁኑ ወቅት ውሃ መያዝ መጀመሩን ጠቅሰው፤ እስካሁን 33 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ መያዙንም ተናግረዋል።

የግድቡ ግንባታ 94 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ የግዱቡ የውሃ ማስተንፈሻ ስፒልዌይ ስራም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

የግድቡ ግንባታ መሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በርካታ ነዋሪዎችን በመስኖ ልማትና በመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

በደቡብ ወሎ ዞን በለጋምቦ ወረዳ ከ200 በላይ አባወራዎች ከጸሃይ ሃይል በሚመነጭ  ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑበደቡብ ወሎ ዞን በለጋምቦ ወረዳ በሚገኘው 021 ደለል ቀበሌ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክ...
23/08/2026

በደቡብ ወሎ ዞን በለጋምቦ ወረዳ ከ200 በላይ አባወራዎች ከጸሃይ ሃይል በሚመነጭ ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

በደቡብ ወሎ ዞን በለጋምቦ ወረዳ በሚገኘው 021 ደለል ቀበሌ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሶላር ሚኒ-ግሪድ (Solar Mini-Grid) ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን የወረዳው ውሃና ኢነርጂ ጽ/ቤት አስታወቀ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ኡመር ካሳ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በዋናነት የብሔራዊ ግሪድ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቀላሉ በማይደርስባቸው የገጠር አካባቢዎች ለሚኖሩ ዜጎች የመብራት አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው።

በደለል ቀበሌ በ«ዋተር ፎር ላይፍ» (Water for Life/SIF) ፕሮጀክት የተገነባው ይህ ሚኒ-ግሪድ ከ200 በላይ አባወራዎችን በየቤታቸው የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያና ቁሳቁሶችን በመገጠም ቀጥተኛ ተጠቃሚ አድርጓል።

አገልግሎቱ ለቤት ውስጥ መብራት ብቻ ሳይሆን የቀበሌ ማዕከላትን ለማዘመን፣ የትምህርትና ጤና ተቋማት አገልግሎትን ለማጠናከር፣ የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማፋጠን እና የማህበረሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው።

በወረዳ ደረጃ ፕሮጀክቱ በ24 ትምህርት ቤቶች፣ በጤና ኬላዎችና ጤና ጣቢያዎች እንዲሁም በ3 ሚኒ-ግሪዶች ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል።

በቀጣይ ፕሮጀክቱን ወደ 4 ሚኒ-ግሪዶችና 76 የትምህርት ተቋማት ለማድረስ የታቀደ ቢሆንም፣ በአካባቢው ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የትግበራ አፈጻጸሙ በሚፈለገው ደረጃ አለመሆኑ ተመላክቷል።
ፕሮጀክቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል።

አገልግሎቱ ሳይቋረጥ በዘላቂነት እንዲቀጥል 4 አባላት ያሉት ልዩ ኢንተርፕራይዝ ተደራጅቶ በቅርበት እንዲያስተዳድረው ተደርጓል።

ኃላፊው አቶ ኡመር ካሳ አክለው እንደገለጹት፤ ይህ የሶላር ሚኒ-ግሪድ የመላው ማህበረሰብ የጋራ ሀብት በመሆኑ ነዋሪው በጥንቃቄ እንዲጠቀምበት፣ እንዲጠብቀውና እንዲንከባከበው ጥሪ አቅርበዋል።
ለጋምቦ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን

Address

Poly Peda Street
Bahir Dar
088

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Telephone

+251582201704

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Water and Energy Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Water and Energy Bureau:

Shortcuts

Share