Amhara Revenue Bureau

Amhara Revenue Bureau Welcome to Amhara Revenue Bureau on Facebook

በቀሪ 60 ቀናት የበጀት ዓመቱን ገቢ ዕቅድ መቶ በመቶ መጨረስ እና የ2019 ግብ ማስቀመጥ እንደሚገባ ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) መምሪያ ሃላፊዎችን አሳሰቡ።ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም (...
07/05/2026

በቀሪ 60 ቀናት የበጀት ዓመቱን ገቢ ዕቅድ መቶ በመቶ መጨረስ እና የ2019 ግብ ማስቀመጥ እንደሚገባ ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) መምሪያ ሃላፊዎችን አሳሰቡ።
ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ክቡር መንገሻ ፈንታው በቢሮው የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ተገኝተው የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።
ቢሮው በአራት መድረኮች ያከናወነው የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም መድረክ ጠንካሮችን አሞካሽቶ፣ መካከለኞችን አበረታቶ ዝቅተኞችን ደግሞ ክፍተታቸውን ለይቶ ልዩ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ ስምምነት ላይ ደርሷል።
በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ቀሪ የግንቦትና የሰኔ ወር 60 ቀናት የገቢ ዕቅዱ መቶ በመቶ የሚጠቃለልበት የማጠቃለያ ምዕራፍ እንዲሁም ለ2019 ዓ.ም አዲስ በጀት ዓመት ግብር ለመሰብሰብ የሚያስችል የዝግጅት ምዕራፍ በሚል ተወስኗል።
መምሪያ ሃላፊዎች “ጨርሶ መጀመር” በሚል መርህ የስራ አመራር ክህሎታቸውን ተጠቅመው በቀሪ 60 ቀናት የበጀት ዓመቱን ገቢ ዕቅድ መቶ በመቶ መጨረስ እና የ2019 ግብ ማስቀመጥ እንደሚገባ ቢሮ ሃላፊው በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እንዲያስፈፅሙ አሳስበዋል።
1. የደረጃ “ለ” የቀን ገቢ ጥናት በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ 130/2018 መሠረት በጥንቃቄ መመራት ማስፈፀም (ጊዜው የሚወሰን)፣
2. ኪራይ ገቢ ያልከፈሉትን ግብር ከፋዮች ተከታትሎ ማስከፈል እስከ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም፣
3. የሩብ ዓመት 25% ቅድመ-ግብር ያልከፈሉትን ግብር ከፋዮች እስከ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም፣ ተከታትሎ ማስከፈል፣
4. አማራጭ አነስተኛ ግብር 2.5 ያልከፈሉትን ግብር ከፋዮች እስከ ሚያዝያ 10/2018 ዓ.ም፣ ተከታትሎ ማስከፈል፣
5. የደረጃ “ሀ” እና ደረጃ “ለ” ዳግም ውሳኔ ወስኖ ማስከፈል እስከ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም፣
6. ወርሃዊ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሪፖርት ማስደረግና ማስፈፀም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም፣
7. የተጨማሪ እሴት ታክስ በልዩነት ወስኖ ማስከፈል እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም፣
8. ሌሎች ያልተጠቀሱ የመደበኛ ገቢዎች ላይ ርብርብ ማድረግና ገቢውን መሰብሰብ በዚህ ስር ያልተጠቀሱ መደበኛ ገቢ ላይ ሮያሊቲ ገቢን ከምንጩ ተከታትሎ መሰብሰብና ዕቅድን መቶ በመቶ መሰብሰብ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም፣
የእርሻ ስራ ግብር እና የገጠር መጠቀምያን በተለያዩ ስልቶች በመጠቀም መጨረስ እስከ ግንቦት 15/2018 ዓ.ም፣
ተርን ኦቨር ታክስ ሰብስበው ገንዘቡን ለገቢ ተቋሙ ያላስገቡ ካሉ ተከታትሎ የማስገባት ስራ መጠናቀቅ አለበት (ቀኑ ይወሰናል) ።
ውዝፍና መደበኛ ግብር ተከታትሎ ማስከፈል እስከ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም፣
የ2018 በጀት ዓመት ተግባራትን ለሚቀጥለው በጀት ዓመት ሳያሻገሩ በአዲስ መንፈስ እና ብሩህ ተስፋ ለአዲሱ በጀት ዓመት በዝግጅት ምዕራፍ ማጠናቀቅ እንዳለበት ቢሮ ሃላፊው ጥብቅ መመሪያ ሰጥተዋል።።

ከደንበኞች አገልግሎት አኳያ ነባር የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸውን ከዲጅታል መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር እሰከ ሰኔ 30/2018 ማጠናቀቅ ይገባል ብለዋል።

የገቢዎች መምሪያ፣ ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች እንዲሁም የስራ ሂደት ዳይሬክተሮች፤ መንግስት ያስቀመጠውን ግብር ሰብስቦ የክልሉን ልማት የማገዝ ተልዕኮ ለመወጣት ስራወችን በቁርጠኝነት እንዲያስፈፅሙ የአደራ መልክዕት አስቀምጠዋል።

ሁላችንም አመራርና ፈጻሚዎች “እንዳንድ ቃል ተናጋሪ እንዳንድ ልብ መካሪ” ሁነን ችግር ሲገጥመን እየተመካከርን የህዝባችንን የልማት ተጠቃሚነት ለማድረጋገጥ በጋራ እንስራ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

በደሴ ገላው

ገቢ ለመሰብሰብ የሚደረግን ጥረት የክልሉ ህዝቦች ልማትን ታሳቢ አድርገው እንዲያግዙ ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ጥሪ አደረጉ።ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)የዘጠኝ...
06/05/2026

ገቢ ለመሰብሰብ የሚደረግን ጥረት የክልሉ ህዝቦች ልማትን ታሳቢ አድርገው እንዲያግዙ ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ጥሪ አደረጉ።
ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)
የዘጠኝ ወሩ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መምሪያዎች ዕርስ-በርስ የተማማሩበት እና ልምድ የተለዋወጡበት መሆኑን ተሳታዎች ገልፀዋል።
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በባህር ዳር፣ በደብረብርሀን፣ በደሴ እና በከሚሴ ከተሞች፤ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)፣ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች፣ መምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም የስራ ሂደት ዳይሬክተሮች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

ቢሮው በበጀት ዓመቱ ያቀደው የገቢ ዕቅድ እንዲሳካ ከክልል እስከ ክፍለ-ከተማ በየወሩ፣ በየሩብ ዓመቱ እየገመገመ ጥሩ አፈጻጸም ያሳዩትን ያበረታታል፤ ወደኋላ የቀሩትን ለምን? ብሎ ይገመግማል፤ ይጠይቃል ድጋፍና ክትትል ያደርጋል።
ሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከመደበኛ እና ከከተማ አገልግሎት ገቢ በድምር ውጤት አንደኛ በመሆኑ በቢሮ ኃላፊው ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶር) ልዩ ምስጋና ቀርቦለታል።
በተቃራኒው የመጨረሻውን ደረጃ በመያዝ ከኋላ የሚከተለው ደብረማርቆስ ከተማ ዕቅዱን ማሳካት ለምን ተሳነው? ምን አይነት ድጋፍና ክትትል ይደረግለት የሚሉ ሃሳቦች ተነስተው የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጦለታል።
ክቡር መንገሻ ፈንታው (ዶር) በደብረ ብርሀን ከተማ በተካሄደው መድረክ በሰጡት ማጠቃለያ ሃሳብ በዘጠኝ ወሩ በዛ ያሉ መምሪያዎች ጥሩ አፈጻጸም ቁመና ላይ ሲገኙ አንዳንዶች ደግሞ ገና ብዙ ዪሚቀራቸው መሆኑን ጠቁመዋል።
ወቅታዊ ገቢ አፈጻጸም መደበኛ ገቢ 70 በመቶ እና ከተማ አገልግሎት ገቢ 53 በመቶ በጥቅሉ ወደ 67 በመቶ ወይም 67 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን አስታውሰዋል።
ቀሪው 30 ቢሊየን ብር ገቢ አልተሰበሰበም ማለት ይህንን ያህል ገንዘብ የሚጠይቁ የልማት ስራዎች በክልላችን ሳይሰሩ ይቀራሉ ማለት ነው።

ስለሆነም ግብር በወቅቱ እንዲሰበሰብ ብሎም ግብር ከፋዮች ለቅጣትና ወለድ እንዳይዳረጉ፤ ቤት- ለቤት፣ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴ፣ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ እና በተለያዩ የቅስቀሳ አግባቦች የማንቃት እና የማሳወቅ ስራ በተቋሙ ሰራተኞች መስራት አለበት ብለዋል።

የገቢ ተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ገቢ ለመሰብሰብ የሚያደርጉትን ጥረት የክልሉ አማራሮች፣ ባለድርሻ፣ አጋር አካላት እንዲሁም የክልሉ ህዝቦች የሚሰራውን ልማት እያዩና ታሳቢ እያደረጉ እገዛ እንዲያደርጉ ቢሮ ኃላፊው ጥሪ አድርገዋል።

የዘጠኝ ወሩ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ: በሰው ሃይል ስምሪት፣ በገቢ ዕቅድ አፈጻጸም፣ በግብር ከፋዮች ታክስ ምርመራ፣ በሰራተኞችና በግብር ከፋዮች ህግ ማስከበር ተግባራት፣ የመልካም አገልግሎት አሰጣጥ፣ የኢ-ታስ አፈጻጸም እንዲሁም ሌሎች ተግባራት ላይ ትኩረት አድርጎ ገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

አቶ አትንኩት በላይ የግብር አወሳሰን አሰባሰብና ክትትል ዋና ስራ ሂደት ዳይሬክተር በቀጣይ ስለሚሰሩ አበይት ተግባራት እንዲሁም የገቢ ክትትልና ታክስ መረጃ አስተዳደር ቡድን መሪ አቶ ስንታየሁ ታደለ ስለ ደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች ቀን ገቢ ግብት ጥናት አፈጻጸም ስልጠና ሰጥተዋል።

በመጨረሻም አስተያየት የሰጡ መምሪያ ሃላፊዎች እና የሂደት አስተባባሪዎች የዘጠኝ ወሩ ዕቅድ አፈጻፀም ግምገማ መድረክ፤ ከፍተኛ አፈጻጸም ያለው መምሪያ ከመጨረሻው አንዱ-ከሌላው በተለያዩ ተግባራት ትምህርት ያገኙበት እና ልምድ የተለዋወጡበት መሆኑን ገልጸዋል።

በደሴ ገላው

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ከሰሜን ሸዋ ዞን፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን፣ ደብረ ብርሃን እና ደብረ ማርቆስ ከተማ ገቢዎች መምሪያ የስራ ኃላፊዎች ጋር በደብረ ብርሃን ...
03/05/2026

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ከሰሜን ሸዋ ዞን፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን፣ ደብረ ብርሃን እና ደብረ ማርቆስ ከተማ ገቢዎች መምሪያ የስራ ኃላፊዎች ጋር በደብረ ብርሃን ከተማ እየገመገመ ይገኛል፡፡

ደብረ ብርሃን፡ ሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) በግምገማ መድረኩ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንደገለፁት በቀሪ ወራት የሚከናወኑ ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር የገቢ እቅድን ለማሳካት አቅጣጫ የምናስቀምጥበት መድረክ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡

ያለፉት ወራት የተግባራት አፈፃፀም በቢሮው የእቅድ ዝግጅት ክትትል ግምገማ እና በጀት አስተዳደር የስራ ሂደት አስተባባሪ በሆኑት በአቶ አያልነህ እጅጉ ቀርቦ ውይይት ከተካሄደ በኃላ የቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በደሴ ገላው

"በቀሪ ወራት የ2018 በጀት ዓመት የገቢ እቅድን ሊያሳኩ የሚችሉ ተግባራትን ቆጠሮ መስራት ይገባል፡፡" አቶ አትንኩት በላይ በአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አወሳሰንና አሰባሰብ የስራ ሂደ...
03/05/2026

"በቀሪ ወራት የ2018 በጀት ዓመት የገቢ እቅድን ሊያሳኩ የሚችሉ ተግባራትን ቆጠሮ መስራት ይገባል፡፡" አቶ አትንኩት በላይ በአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አወሳሰንና አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ

ባህር ዳር፡ ሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የ2018 በጀት አመት የገቢ እቅድን በውጤት ለማጠናቀቅ እቅድን ሊያሳኩ የሚችሉ ተግባራትን ቆጠሮ መስራት እንደሚገባ በአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር አወሳሰንና አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አትንኩት በላይ ገልጸዋል፡፡

አራተኛው ሩብ ዓመት የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካት ጥረት የምናደርግበት እና የመጭውን በጀት ዓመት ቅድመ ዝግጅት ምናደርግበት ስለሆነ ሁሉም የገቢ ተቋም አመራሮች እና ሰራተኞች በልዩ ትኩረት መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡

በቀሪ ወራት የበጀት ዓመት የገቢ ዕቅድን ሊያሳኩልን የሚችሉ ተግባራትን ቆጥረን መስጠት፣ ትኩረት ሚደረግባቸውን ተግባራትና ከተሞች፣ ወረዳዎችና ክፍለ-ከተሞችን ለይቶ መስራት እና ተግባራትን በስራ ክፍፍል እና በቅንጅት መምራት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡

ግብራቸውን ያልከፈሉ የንግድ ትርፍ እና ኪራይ ገቢ ፣ ቅድም ግብር ወይም 25 በመቶ ያልከፈሉ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮችን እና አማራጭ አነስተኛ ግብር ወይም 2.5 በመቶ መክፈል የሚገባቸውን ግብር ከፋዮች ተከታትሎ ማስከፈል ይኖርብናል ብለዋል፡፡

ዳግም ውሳኔ ያልተወሰነላቸውን መወሰን እና የተወሰነላቸውን ግብር ከፋዮች በማስከፈል የገቢ ዕቅዱን ማሳካት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢዎች ወርሃዊ ሪፖርት እንዲያደርጉ በቂ ክትትል ማድረግ እና ጠንካራ የደረሰኝ ክትትል ስራ በመስራት ችግር ያለባቸውን 50ሺ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በመቅጣት ለግብር ህጉ ተገዥ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ መስራት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

ውዝፍ ግብር ያለባቸውን ግብር ከፋዮች መረጃ በማጥራት ማስጠንቀቂያ መስጠት፣ ድርጅት በማሸግ፣ አካውንት በማገድ፣ ሃብት ንብረት በመያዝ ተቆራርጦ ገቢውን መሰብሰብ በቀሪ ወራት የሚጠበቅ ስራ ነው፡፡

ከማጠቃለያ ምዕራፍ ስራችን ትይዩ የግብር ከፋዮችን መረጃ ማጥራት፣ ኢ-ታስ ያልተመዘገቡ ግብር ከፋዮችን መመዝገብ እና ሌሎች በገቢ ተቋሙ የተለመዱ መደበኛ ስራዎች መከናወን አለባቸው ብለዋል፡፡

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📸፡- ማስተዋል ሁነኛው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

የበጀት ዓመቱን የገቢ እቅድ በውጤት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡ መምሪያ ኃላፊዎች ባህር ዳር፡ ሚያዝያ 24/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የ2018 በጀት የገቢ እቅ...
02/05/2026

የበጀት ዓመቱን የገቢ እቅድ በውጤት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡ መምሪያ ኃላፊዎች

ባህር ዳር፡ ሚያዝያ 24/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የ2018 በጀት የገቢ እቅድ በውጤት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊዎች እና የስራ ሂደት አስተባባሪዎች በዘጠኝ ወር የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ ተናግረዋል፡፡

በግምገማ መድረኩ ላይ የተሳተፉ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የስራ ኃላፊዎች እንደገለጹት ተደጋጋሚ መድረክ በመፍጠር ግብር ከፋዮች ግብራቸው በወቅቱ እንዲከፍሉ የማስተማር እና የቅስቀሳ ስራ እንደተሰራ ተናግረዋል፡፡

የመምሪያ የማኔጅመንት አባላት ክፍለ-ከተሞች ተከፋፍለው በየሳምንቱ ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ የገቢ አፈፃፀሙን ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከንግድ እንቅስቃሴቸው ጋር ተመጣጣኝ ያለሆነ ደረጃ ያላቸውን ግብር ከፋዮች ደረጃቸውን የማሻሻል እና የሊዝ ውዝፍ ያለባቸው ግብር ከፋዮች ቤት ለቤት በመቀስቀስ እንዲከፍሉ የማድረግ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡

ሌላው በመድረኩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የምዕራብ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ የስራ ኃላፊዎች "ምንም እንኳን የፀጥታው ችግር በግብር አሰባሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽኖ ቢያሳድርም ግብርን ከልማት ስራዎች ጋር በማስተሳሰር የንግዱን ማህበረሰብ ግንዛቤ ለማሳደር እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡"

በቀሪ ወራት የተሻሉ ሠራተኞችን በማስቀጠል እና ችግር ያለባቸው ላይ እርምት እርምጃ በመውሰድ የተቀመጠውን አቅጣጫ ለመፈፀም ዝግጁ መሆናቸውን ቃል ገብተዋል፡፡

ሠላም ባለባቸው አካባቢዎች ላይ ጠንካራ ክትትል እና ድጋፍ በማድግ ያልተሰበሰበ ገቢን ለመሰብሰብ እንሰራለን ያሉት ደግሞ የደቡብ ጎንደር እና የሰሜን ጎጃም የስራ ኃላፊዎች ናቸው፡፡

የፀጥታ ችግሩ የደረሰኝ ክትትሉ እንዲቀዛቀዝ አንዳደረገው በውይይቱ ላይ ተነስቷል፡፡

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📸፡- ማስተዋል ሁነኛው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

"የገቢ እቅዱን ለማሳካት በቀሪ ወራት ጠንካራ የክትትል ስራ ይሠራል፡፡" መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ  ኃላፊባህር ዳር፡ ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢ...
01/05/2026

"የገቢ እቅዱን ለማሳካት በቀሪ ወራት ጠንካራ የክትትል ስራ ይሠራል፡፡" መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

ባህር ዳር፡ ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ከዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በባህር ዳር ከተማ አካሄዷል፡፡

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት ለግብር ከፋዮች ተደጋጋሚ ትምህርት በመስጠት እና ውይይቶችን በማድረግ ግብር የመክፈል ባህልን ማሳደግ ይኖርብናል ብለዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ገቢ ተቋሙ እቅድ እንዲያሳካ በቀሪ ወራት ጠንካራ የክትትል እና ድጋፍ ስራ እንደሚሰራ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

የተጀመሩ የልማት ስራዎች ቀጣይነት የሚኖራቸው በበጀት ዓመቱ የታቀደው የገቢ እቅድ ሲሳካ ስለሆነ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለገቢ አሰባሰቡ አጋዥ መሆን አለበት ብለዋል፡፡

በቀሪ ወራት ያሉ የገቢ ምንጮችን በመለየት የታቀደውን የገቢ እቅድ ለማሳካት የገቢ ተቋሙ አመራሮች እና ሰራተኞች በቁርጠኝነት መስራት እንደሚኖርባቸው ገልፀዋል፡፡

ያልፈፀምናቸውን ተግባራት ከሌሎች ልምድ በመውሰድ በቀሪ ወራት በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝግብ መስራት ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔ ተናግረዋል፡፡

ለገቢ አሰባሰብ ስራችን አጋር እና ባለድርሻ ከሆኑ አካላት ጋር ውይይቶችን ማድረግ እና የደረሰኝ አቆራረጥ ላይ ክትትል የማድረግ ስራ በቀጣይም መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

ሌላው በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ የኔሰው መኮነን እንደተናገሩት የገቢ እቅድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ እንደመሄዱ የዚሁ ፈፃሚ የሆነው የተቋማችን አመራር እና ሰራተኛ በእውቀትና በክህሎት እያደገ መምጣት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

ቴክኖሎጅ መጠቀም የግብር ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ እና ዘላቂ ገቢ እንዲኖር የሚያደርግ ዋና መሳሪያ ስለሆነ ገቢ ተቋሙ በትኩረት የሚሰራበት ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ የቢሮው የእቅድ ዝግጅት ክትትል ግምገማ እና በጀት አስተዳደር የስራ ሂደት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አያልነህ እጅጉ ያለፉት ወራት የተግባራት አፈፃፀም ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛ እና ከተማ አገልግሎት ገቢ በድምሩ 100 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ እና ባለፉት 9 ወራት በታክስ አሰባሰቡ ዙሪያ አበረታች ውጤት እየተመዘበ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

እስከ ሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም ከመደበኛ እና ከተማ አገልግሎት ገቢ በድምሩ 66 ነጥብ 394 ቢሊዮን ብር ገቢ የተሰበሰበ ሲሆን አፈፃፀሙም በዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው እቅድ አኳያ 66 ነጥብ 15 በመቶ ይይዛል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን፣ ኮምቦልቻ ከተማ፣ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን፣ አዊ ብሔረሰብ ዞን፣ ወልዲያ ከተማ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን እና ምዕራብ ጎንደር ዞን ገቢዎች መምሪያ የእቅዳቸውን ከ67 ነጥብ 3 በመቶ በላይ የሰበሰቡ ሲሆኑ ሰሜን ጎጃም ዞን፣ ዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን፣ ሰሜን ወሎ፣ ሰሜን ጎንደር ዞን፣ ደሴ ከተማ፣ ደብረታቦር ከተማ፣ ደቡብ ጎንደር ዞን እና ደብረ ማርቆስ ከተማ ገቢዎች መምሪያ የእቅዳቸውን ከ60 በመቶ በታች የሰበሰቡ መሆናቸው በቀረበው ሰነድ ላይ ተመላክቷል፡፡
በዚህ የግምገማ መድረክ የባህር ዳር ከተማ፣ የሰሜን ጎጃም ዞን፣ የአዊ ብሔረሰብ ዞን፣ የምዕራብ ጎጃም ዞን እና የደቡብ ጎንደር ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊዎች እና አስተባባሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📸፡- ማስተዋል ሁነኛው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

የግምገማ መድረኩ ተሞክሮዎችን በማቀያየር የታቀደውን የገቢ እቅድ ለማሳካት የሚያግዝ ይሆናል፡፡ አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊባህር ዳር፡ ሚያዝያ 22/2018...
30/04/2026

የግምገማ መድረኩ ተሞክሮዎችን በማቀያየር የታቀደውን የገቢ እቅድ ለማሳካት የሚያግዝ ይሆናል፡፡ አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ

ባህር ዳር፡ ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ከዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ፍቅረማርያ ደጀኔ በመክፈቻ ንግራቸው የግምገማ መድረኩ ተሞክሮዎችን በማቀያየር የታቀደውን የገቢ እቅድ ለማሳካት የሚያግዝ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ የቢሮው ያለፉት ወራት የተግባራት አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ከተካሄደ በኃላ በበጀት ዓመቱ የታቀደውን የገቢ እቅድ ለማሳካት በቀጣይ ወራት መከናወን ያለባቸው ተግባራት ላይ አቅጣጫ እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡

በገቢ አሰባሰብ ተግባራት ላይ መልካም አፈፃፀም ያላቸው መምሪያዎች ልምዳቸውን ለሌሎች የሚያስተላልፉበት የውይይት መድረክ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በዚህ የግምገማ መድረክ የባህር ዳር ከተማ፣ የሰሜን ጎጃም ዞን፣ የአዊ ብሔረሰብ ዞን፣ የምዕራብ ጎጃም ዞን፣ የደቡብ ጎንደር ዞን እና የደብረ ታቦር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊዎች እና አስተባባሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📸፡- ማስተዋል ሁነኛው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

ሙሰኞች ሙስናን ለመፈፀም የሚጠቀሙባቸው ዋና ዋና መንገዶች ሙስና በተለያየ መልኩና መንገዶች ሊፈጸም የሚችል ውስብስብ ወንጀል ቢሆንም፣ በብዛት የሚፈጸምባቸው ዋና ዋና መንገዶች የሚከተሉት ናቸ...
29/04/2026

ሙሰኞች ሙስናን ለመፈፀም የሚጠቀሙባቸው ዋና ዋና መንገዶች

ሙስና በተለያየ መልኩና መንገዶች ሊፈጸም የሚችል ውስብስብ ወንጀል ቢሆንም፣ በብዛት የሚፈጸምባቸው ዋና ዋና መንገዶች የሚከተሉት ናቸው።

✍️ ጉቦ (Bribery) ፦ ይህ በብዛት የሚታወቅ የሙስና ዓይነት ሲሆን፣ አንድ ግለሰብ የሚፈልገውን ጥቅም ለማግኘት ወይም ያለአግባብ አገልግሎት እንዲፋጠንለት ለባለሥልጣን ወይም ለሠራተኛ የሚሰጠው/የሚቀበለው ክፍያ፣ ስጦታ ወይም ማንኛውም ዓይነት ጥቅም ነው። ይህም በጥሬ ገንዘብ፣ በቁሳቁስ ወይም በወደፊት ቃል ኪዳን ሊፈጸም የሚችል ነው።

✍️ የምዝበራ ተግባር (Embezzlement) ፦ ለሥራ ተብሎ በአደራ የተሰጠንን የሕዝብ ወይም የመንግሥት ሀብትና ንብረት ለግል ጥቅም ማዋልን የሚያጠቃልል ሲሆን፤ የገንዘብ ስርቆት፣ የመንግሥት ንብረትን ለግል ፍላጎት መጠቀም ወይም የሂሳብ ሰነዶችን በማጭበርበር ገንዘብ መውሰድን ያካትታል።

✍️ አድልዎ እና ዘመድ አዝማድ (Nepotism and Cronyism)፦ ይህ ደግሞ ብቃትንና መመሪያን መሠረት በማድረግ ፈንታ፤ በዝምድና፣ በጓደኝነት ወይም ትውውቅ ላይ ተመስርቶ ጥቅማ ጥቅሞችን መስጠት ነው። መገለጫውም፣ ለሥራ የማይመጥኑ ሰዎችን መቅጠር፣ ጨረታዎችን ለቅርብ ሰዎች መስጠት ወይም ማዕረግን ያለአግባብ መስጠት ነው።

✍️ ማጭበርበር (Fraud) ፦ እውነታን በመደበቅ፣ ሰነዶችን በመለወጥ ወይም የሐሰት መረጃዎችን በማቅረብ ያለአግባብ ጥቅም ማግኘት ሲሆን፤ የሐሰት ደረሰኞችን ማዘጋጀት፣ ያልተከናወኑ ሥራዎችን እንደተከናወኑ አድርጎ ሪፖርት ማድረግ ወይም የጨረታ ሰነዶችን ማጭበርበር የሚሉት መገለጫዎች ናቸው።

✍️ ማስገደድ (Extortion) ፦ አንድ ባለሥልጣን ወይም ሠራተኛ የተሰጠውን ሥልጣን በመጠቀም፣ ሌላውን አካል በማስፈራራት ወይም ተጽዕኖ በመፍጠር ጥቅም እንዲሰጠው የሚያደርግበት መንገድ ነው። "ይህን ካላደረግክ ሥራህ አይሰራም" በማለት ተገልጋዩን በማስጨነቅ መንገድ የሚፈፀም ነው።

✍️ የጥቅም ግጭት (Conflict of Interest) ፦ ይህ አንድ ግለሰብ ያለበትን የሕዝብ አደራና ኃላፊነት ከግል ጥቅሙ ጋር የሚጋጭበት ሁኔታ ሲፈጠርና ለግል ጥቅሙ ቅድሚያ ሲሰጥ የሚፈጠር ሲሆን፤ አንድ የውሳኔ ሰጭ አካል የራሱ ወይም የቅርብ ዘመዱ ድርጅት በሚሳተፍበት ጨረታ ላይ ውሳኔ ሲሰጥ የሚፈጠር ነው።

✍️ የተገቢ ያልሆነ ተጽዕኖ ንግድ (Influence Peddling) ፦ ከባለሥልጣናት ጋር ያለን ቅርበት ወይም ትውውቅ በመጠቀም፣ በሌላ አካል ላይ ተጽዕኖ ለማሳደርና ለዚህም ተግባር ክፍያ ወይም ጥቅም መቀበል ነው።

በአጠቃላይ፣ እነዚህ የሙስና መንገዶች ተቋማዊ አሰራርን በማዳከም፣ ፍትህን በማጓደል እና የሀገርን የልማት ጉዞ በመግታት ረገድ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳሉ። እነዚህን ክፍተቶች ለመድፈን ግልጽነት እና ተጠያቂነት ያለበትን የዲጂታል አሰራር መዘርጋት እንደ ዋነኛ መፍትሔ ይወሰዳል።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

በምዕራብ ጎጃም ዞን በግንባታ ላይ ያሉ የአስፓልት መንገድ መሠረተ-ልማቶች 1. ከቡሬ–አጋምሳ–ነቀምት፣  2. አርብ ገበያ–ሰከላ–ቲሊሊ፣  3. ጅጋ–ቋሪት–አርብ ገበያ፣  3. ከቡሬ-ሽንዲ-ጎመ...
29/04/2026

በምዕራብ ጎጃም ዞን በግንባታ ላይ ያሉ የአስፓልት መንገድ መሠረተ-ልማቶች

1. ከቡሬ–አጋምሳ–ነቀምት፣
2. አርብ ገበያ–ሰከላ–ቲሊሊ፣
3. ጅጋ–ቋሪት–አርብ ገበያ፣
3. ከቡሬ-ሽንዲ-ጎመር፣
4. ደብረ ማርቆስ-ደብረ ኤሊያስ-ቁጭ፣
5. ደምበጫ-ፈረስ ቤት-ሰቀላ-ቢቡኝ፣
6. ማንኩሳ- ብር ሸለቆ
7. የሚሸፍነው ኪ.ሜ 366 ርዝመት ናቸው ።

29/04/2026
ኅብረተሰቡ ነዳጅን ከመቆጠብ ባለፈ ኮንትሮባንድን በመታገል የዜግነት ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ  (ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም) የኃይል ሉዓላዊነት ጉዞ ከአስከፊ ...
29/04/2026

ኅብረተሰቡ ነዳጅን ከመቆጠብ ባለፈ ኮንትሮባንድን በመታገል የዜግነት ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ

(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም)
የኃይል ሉዓላዊነት ጉዞ ከአስከፊ አደጋ የታደገን በመሆኑ ኅብረተሰቡ ነዳጅን ከመቆጠብ ባለፈ ኮንትሮባንድን በመታገል የዜግነት ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገልጿል::

አገልግሎቱ ያወጣው መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል።

ከቀውስ ባሻገር መሻገር በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነትና በሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት ምክንያት ዓለም አቀፉ የነዳጅ አቅርቦት ተቋርጦ፣ የበርካታ ሀገራት ማደያዎች እየተዘጉና ማኅበራዊ ቀውሶች እየተባባሱ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በተወሰነም ደረጃ ቢሆን ይህንን ከባድ ፈተና መቋቋም የቻለችው መንግሥት ላለፉት ስምንት ዓመታት በታዳሽ ኃይል (ውኃ፣ ነፋስ፣ ፀሐይና ጂኦተርማል) ላይ ባከናወናቸው ግዙፍ ስትራቴጂያዊ ፕሮጀክቶች ነው።

የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ የኃይል አማራጮችና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EV) ንቅናቄ ዛሬ የሕልውናችን ዋስትና ሆነዋል።
እነዚህ መሠረተ-ልማቶችን መንግሥት አስቀድሞ ዝግጅት ባያደርግባቸው ኖሮ ሀገሪቱ በከፋ የኢኮኖሚ መሽመድመድና የዋጋ ንረት ውስጥ ትወድቅ ነበር። የጎዴ የተፈጥሮ ጋዝ ማጣሪያም የኢነርጂ ሉዓላዊነታችንን ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።

በአሁኑ ወቅት መንግሥት ለትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሊውል የነበረን በጀት የዓለም አቀፍ የዋጋ ንረት ጫና በዜጎች ላይ እንዳይበረታ በሚል በቢሊዮን የሚቆጠር የነዳጅ ድጎማ እያደረገ ይገኛል።

ይሁን እንጂ ይህ ድጎማ ለኮንትሮባንድና ለጥቁር ገበያ ዓላማ እንዲውል አይፈቀድም። የነዳጅ ኮንትሮባንድን መከላከል የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳይ በመሆኑ መንግሥት ከጸጥታ አካላትና ከኅብረተሰቡ ጋር በመሆን የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን ይቀጥላል።

በአጠቃላይ የጀመርነው የኃይል ሉዓላዊነት ጉዞ ከአስከፊ አደጋ የታደገን በመሆኑ ኅብረተሰቡ ነዳጅን ከመቆጠብ ባለፈ ኮንትሮባንድን በመታገል የዜግነት ድርሻውን ሊወጣ ይገባል። የዛሬው መዋቅራዊ ሽግግራችን ለነገው ዘላቂ ብልጽግና መሠረት ነው።

ከ6 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ 1 ሺህ 452 ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ ነው ከ6 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 1 ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገ...
28/04/2026

ከ6 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ 1 ሺህ 452 ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ ነው

ከ6 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 1 ሺህ 452 የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ትምህርት ቤቶቹን ሚኒስቴሩ ከክልሎች ጋር በመተባባር በሁሉም ክልሎች አንደሚገነባ ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቶቹ በአጭር ጊዜ ውስጥ በጥራት ተገንብተው ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ዝግጁ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

በዚህም 87 ሺህ 120 ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲገቡ ያደርጋል ያሉት ሚኒስትሩ÷ የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ጥራት ያለውን ትምህርት ለማዳረስ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑንም አመልክተዋል።

ለዚህም ሚኒስቴሩ ከሁሉም ክልል ትምህርት ቢሮዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል።

Address

Bahir Dar
746

Opening Hours

Monday 08:30 - 00:30
Tuesday 08:30 - 00:30
Wednesday 08:30 - 00:30
Thursday 08:30 - 00:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 02:30 - 00:30

Telephone

+251582265776

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Revenue Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Revenue Bureau:

Share