Amhara Revenue Bureau

Amhara Revenue Bureau Welcome to Amhara Revenue Bureau on Facebook

"የታቀደው የአሻጋሪ ልማት እቅድ ስኬት በሚሰበሰበው ገቢ ይወሰናል::"  መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር )👨‍💻:- ሲሳይ አስማማውአስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎ...
03/09/2026

"የታቀደው የአሻጋሪ ልማት እቅድ ስኬት በሚሰበሰበው ገቢ ይወሰናል::"
መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር )

👨‍💻:- ሲሳይ አስማማው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
Website:- https://www.abor.gov.et/
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር እና የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የልዩ ተሸላሚነት ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሬጅዮፖሊታን ከተሞች የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣...
03/09/2026

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር እና የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የልዩ ተሸላሚነት ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡
የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሬጅዮፖሊታን ከተሞች የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ በበጀት ዓመቱ ከተሰበሰበው ጠቅላላ ገቢ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ በማበርከት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡት ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር እና ለሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የልዩ ተሸላሚነት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የሥራ እንቅስቃሴያቸውን ይበልጥ የሚያጠናክር ለእያንዳንዳቸው አንድ አንድ የኤሌክትሪክ ባጃጅ ሽልማት ተበርክቶለታል።

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📷፡- ማስተዋል ሁነኛው
አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
Website:- https://www.abor.gov.et/
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የሪጆፓሊታንት ከተሞች እውቅና ሰጠየአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሬጅዮፖሊታን ከተሞች የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙ...
03/09/2026

የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የሪጆፓሊታንት ከተሞች እውቅና ሰጠ

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሬጅዮፖሊታን ከተሞች የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ በበጀት ዓመቱ የላቀ የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዞን ገቢዎች መምሪያዎች የእውቅናና የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ተካሄዷል፡፡ በዚህም መሠረት፡-

ከአንደኛ ደረጃ ሪጆፓሊታንት ከተሞች፡-

1ኛ. ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ
2ኛ. ጎንደር ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ

ከሁለተኛ ደረጃ ሪጆፓሊታንት ከተሞች፡-

1ኛ. ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ
2ኛ. ደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ

ከሶስተኛ ደረጃ ሪጆፓሊታንት ከተሞች፡-

1ኛ. ወልዲያ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ

የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገባቸው የእውቅና ምስክር ወረቀት ሽልማት እና አንደኛ ለወጣ ሁለት ኮምፒዩተር፣ ሁለተኛ ለወጣ አንድ ኮምፒዩተር እና አንድ ፕሪንተር ተበርክቶላቸዋል።

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📷፡- ማስተዋል ሁነኛው
አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
Website:- https://www.abor.gov.et/
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዞን ገቢ መምሪያዎች እውቅና ሰጠነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሬጅዮፖሊታን ከተማ የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣ ...
03/09/2026

የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዞን ገቢ መምሪያዎች እውቅና ሰጠ

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሬጅዮፖሊታን ከተማ የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ የላቀ የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዞን ገቢዎች መምሪያዎች የእውቅናና የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ተካሄዷል፡፡ በዚህም መሠረት፡-

ከአንደኛ ደረጃ ዞኖች፡

1ኛ. የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ
2ኛ. የደቡብ ወሎ ዞን ገቢዎች መምሪያ

ከሁለተኛ ደረጃ ዞኖች፡

1ኛ. የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ገቢዎች መምሪያ
2ኛ. የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገቢዎች መምሪያ
3ኛ. የሰሜን ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ

ከሦስተኛ ደረጃ ዞኖች፡

1ኛ. የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ገቢዎች መምሪያ
2ኛ. የምዕራብ ጎንደር ዞን ገቢዎች መምሪያ
3ኛ የዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ገቢዎች መምሪያ

የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገባቸው የእውቅና ምስክር ወረቀት ሽልማት እና አንደኛ ለወጣ ሁለት ኮምፒዩተር፣ ሁለተኛ ለወጣ አንድ ኮምፒዩተር እና አንድ ፕሪንተር ሦስተኛ ለወጣ አንድ ፕሪንተር ተበርክቶላቸዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ገቢዎች መምሪያ በልዩ ሁኔታ የእውቅና ምስክር ወረቀት፣ አንድ ኮምፒዩተር ከአንድ ፕሪንተር ጋር ተበርክቶለታል።

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📷፡- ማስተዋል ሁነኛው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
Website:- https://www.abor.gov.et/
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

"የታቀደው የአሻጋሪ ልማት እቅድ ስኬት በሚሰበሰበው ገቢ ይወሰናል"  መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር )ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሪጆ...
02/09/2026

"የታቀደው የአሻጋሪ ልማት እቅድ ስኬት በሚሰበሰበው ገቢ ይወሰናል" መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር )

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞንና የሪጆፖሊታንት ከተማ የገቢ መምሪያ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻና አጋር አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ በባህር ዳር ከተማ አካሄደ።

በመድረኩ ላይ የተገኘው የቢሮው ኃላፊ መንገሻ ፈንታው ( ዶ/ር) እንደገለጹት በክልሉ የታቀደው የአሻጋሪ ልማት እቅድ ውጤታማነት በቀጥታ በሚሰበሰበው ገቢ መጠን ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ለገቢ ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

የገቢ ተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች "እኛ አልፈን ህዝባችን ይለፍ" በሚል ቁርጠኝነትና ከፍተኛ መስዋዕትነት ባከናወኑት ተግባር በበጀት ዓመቱ የተሻለ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ከመደበኛ እና ከተማ አገልገሎት ገቢ በድምሩ 100.3 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ እንደታቀደ ያስታወሱት ቢሮ ኃላፊው በተደረገ ከፍተኛ ጥረት መደበኛ ገቢ 82 ነጥብ 4 ቢሊዮን ወይም 97.2 በመቶ እና ከተማ አገልግሎት ገቢ 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወይም 67.77 በመቶ በድምሩ 93 ነጥብ 004 ቢሊዮን ብር ወይም የእቅዱን 92.66 በመቶ መሰብሰብ እንደተቻለ ገልፀዋል፡፡

የገቢ ተቋሙ በክልሉ ውስጥ የሪፎርም ሥራዎችን እያከናወኑ ከሚገኙ ተቋማት አንዱ መሆኑንና በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ደረሰኝ ሳይቆርጡ የመንግስትን የአደራ ገንዘብ የሚበሉት ላይ በቀጣይ ጠንካራ ስራ ይሰራል ብለዋል።

የ2018 በጀት ዓመት በስኬት ለማጠናቀቅ ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ስራ መሰራቱን የገለጹት ደግሞ አቶ የኔሰው መኮነን የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ ናቸው።

ሰፊ የሒሳብ መዝገብ በሚቀርብባቸው ከተሞች ላይ ኦዲተሮችን አዘዋውሮ ማሠራት መቻሉ በገቢ አሰባሰብ ሂደቱ ላይ አዎንታዊ ሚና መጫወቱን አብራርተዋል።

ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡት የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔ "ገቢ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ዳር ለማድረስ ዋና መሠረት መሆኑን ተናግረዋል።"

የተሻለ ገቢ በሚገኝባቸው የገቢ አርስቶች እና አካባቢዎች ላይ የተለየ ትኩረት አድርገን መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

ልማት ማልማት የሚያቻለው በምንሰበስበው ገቢ ልክ ስለሆነ በቀጣይ አመት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ የህዝባችንን የልማት ጥያቄ የሚመልስ ገቢ ለመሰብሰብ መስራት ይገባል ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ የመድረኩ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

የ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ መምሪያዎች የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

✍️፡- ሲሳይ አስማማው
📷፡- ማስተዋል ሁነኛው

አስተያየት እና ጥያቄ ቢኖርዎ ከዚህ ገፅ በተጨማሪ እነዚህን አድራሻዎች ይጠቀሙ
በፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- Amhara Region revenue bureau
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
Website:- https://www.abor.gov.et/
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ
መደበኛ ስልክ ቁጥሮች 058 220 57 49/ 09 47

"ገቢ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለመስራት መሠረት ነው" አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔነሀሴ 27/2018 ዓ.ም፤ ባህር ዳር (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞ...
02/09/2026

"ገቢ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለመስራት መሠረት ነው" አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔ

ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም፤ ባህር ዳር (የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የዞን እና የሪጆፖሊታንት ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊዎች፣ባለድርሻ እና አጋር አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙት የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ፍቅረማርያም ደጀኔ "ገቢ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለመስራት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።"

ቢሮው የታቀደውን የገቢ እቅድ ለማሳካት ከላይ እስከ ታች ያለው አመራር እና ሰራተኛ ባደረገው ጥረት የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

የቢሮው የእቅድ ዝግጅት ክትትል ግምገማና በጀት አስተዳደር የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አያልነህ እጅጉ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቧል።

በቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ ይካሄዳል፡፡

የቢሮው ሥነ-ምግባር መኮንን ተሸለሙበ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም አንደኛ በመሆንየአማራ ክልል ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን በየዓመቱ የክልል ቢሮዎችን እና የልማት ድርጅቶችን በዓመቱ መጨ...
01/09/2026

የቢሮው ሥነ-ምግባር መኮንን ተሸለሙ

በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም አንደኛ በመሆን
የአማራ ክልል ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን በየዓመቱ የክልል ቢሮዎችን እና የልማት ድርጅቶችን በዓመቱ መጨረሻ በአፈጻጸማቸው መሠረት እያወዳደረ እውቅና ይሰጣል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የሥነ-ምግባር ክፍል በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ከሁሉም ተቋማት ሲወዳደር አንደኛ በመሆኑ በቢሮው ስም ወ/ሮ ሰናይት ወ/አገኝ እውቅና ምስክር ወረቀት ተቀብለዋል።

የሥነ-ምግባር መኮንኗ ወ/ሮ ሰናይት ወ/አገኝ ሽልማቱ የሁሉም ሰራተኞች በመሆኑ “እንኳን ደስ አላችሁ!” በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በበጀት ዓመቱ 50 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ አስታወቀበአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የ2018...
28/08/2026

የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በበጀት ዓመቱ 50 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ አስታወቀ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ አደረገ።

በመድረኩ የአብክመ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አቶ አታላይ ጥላሁንን ጨምሮ ሁሉም የም/ቢሮ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው ዳይሬክተሮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን አዲስ ተቋም ሲመሰረት ፈተና እና እድሎችም እንዳሉት የገለጹት ቢሮው ኃላፊው አቶ አታላይ ጥላሁን በሚፈለገው ደረጃ ተገቢ ስራ በመስራት ጠንካራ ተቋም መገንባት እድል እንደሚሆን በማስታወቅ የተቋቋመውን ተቋም በአግባቡ በማደራጀት ውጤታማ እንዲሆን ከወዲሁ አስቦ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

የአማራ ክልል የህብረተሰብ ተሳትፎ በ6 ዓለማዎች ላይ ተመስርቶ የሚሰራ እንደሆነ የጠቆሙት ቢሮ ኃላፊው አቶ አታላይ ጥላሁን ልማት በመንግስት ብቻ ስለማይመጣ ህብረተሰቡን በማሳተፍ እና የልማቱ ባለቤት በማድረግ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ በህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፈቃድ አገልግሎት እስከ 50 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅድ የተያዘ ሲሆን እቅዱ የታሰበውን ግብ ያሳካ ዘንድ ህብረተሰቡ የተሻለ የሚጠቅመውን የልማት ስራ መርጦ እንዲሰራ በማድረግ፣ ህበረተሰቡን በአግባቡ በማሳመንና በማሳተፍ መስራት እንደሚገባም አቶ አታላይ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

አቶ አታላይ አክለውም የእቅዱን ግቦች ለማሳካት የምንከተላቸውን የማስፈጸሚያ ስልቶች በአግበቡ በመያዝ ወደ ስራ መግባትና የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ስራን በአግባቡ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ለክልላችን ህዝብና ለሚመለከታቸው አጋር አካላት ተገቢ ግንዛቤ በመፍጠር ውጤታማ አፈጻጸም እንዲኖር ሁላችንም የድርሻችንን በመወጣት ለክልላችን ልማት መስራት ይገባል ሲሉ ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

በሌላ በኩል የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ ያየህ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመትን እቅድ ትውውቅ አቅረበው ያስገመገሙ ሲሆን በመድረኩ በተሰጠው ግብዓት መሰረት እቅዱን የበለጠ በማጠናከር ተዘጋጂቶ ለዞኖችና ወረዳዎች ጭምር በማውረድ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል፤ሁሉም የክልሉ ህዝብና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለዘርፉ ውጤታማነትና ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል፡

የግብር ከፋዮች ስልጠናና የድጋፍ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ተገለጸነሐሴ 22/2018 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)የክልል ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በአዲሶቹ የገቢ ግብር አዋጆችና የ...
28/08/2026

የግብር ከፋዮች ስልጠናና የድጋፍ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ተገለጸ

ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)
የክልል ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በአዲሶቹ የገቢ ግብር አዋጆችና የንግድ ገቢ ግምት ጥናት ዙሪያ በዞን መምሪያዎች፣ በሜትሮፖሊታን መምሪያዎች፣ በከተሞች እና ወረዳ ገቢ ጽህፈት ቤቶች ተሰማርተው የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን አሳልጠዋል፣ የግብር ትምህርትና ቅስቀሳ ስራ ሰርተዋል።

በተፈጠሩ መድረኮች፤ ለደረጃ “ሀ” እና “ለ” ግብር ከፋዮች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና ለነዋሪው ህዝብ ስለግብር አስፈላጊነት፣ ባለፈው በጀት ዓመት የተሰበሰበው ገቢ አገልግሎት እና የአዲሱ በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ግንዛቤ ተሰጥቷል።

የዞን አስተዳዳሪዎች፣ ከንቲባዎች እና የፓርቲ ኃላፊዎች ማህበረሰቡን በማወያየት ግብር ከህዝብ ለህዝብ አገልግሎት የሚውል መሆኑን በማስገንዘብ ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል።

ግብር ከፋዮች የተሰጣቸውን ገለጻ አድንቀው ተከታታይ ግንዛቤ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

ያለደረሰኝ ከሚገዙ ነጋዴዎች ጋር አለመመጣጠን፣ የግብዓት ታክስ አወራረድ እና በሌሎች ስም ስለሚፈጸሙ ሽያጮች የተነሱ ጥያቄዎች ተለይተው በቂ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቷል።

ቢሮው ከተለመደው የሩቅ ክትትል ወጥቶ የክልል ልዩ ስልጠናና ክህሎት ያላቸው አመራሮችንና ባለሙያዎችን በቀጥታ እስከ መምሪያ እና ገቢ ጽ/ቤት ድረስ በማውረድ የቅርብ ድጋፍና ክትትል ማድረግ የክልሉን ገቢ ዓቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳድገው ታምኖበታል።

በመድረኮቹ ከተደረጉ ውይይቶች ባለፈ፣ ግብር ሰብሳቢው አካል እና ግብር ከፋዮች ለየዞኑና ለከተማው ልማት የሚውል ገቢ በትክክል እና በፍትሃዊነት እንዲሰበሰብ የጋራ መግባባትና ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ከተነሱት የግብዓት ታክስ አወራረር እና የገበያ ውድድር አለመመጣጠን ጋር የተያያዙ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ቀጣይነት ያለው የባለድርሻ አካላት ውይይትና የህግ ማብራሪያ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

በደሴ ገላው

Address

Bahir Dar
746

Opening Hours

Monday 08:30 - 00:30
Tuesday 08:30 - 00:30
Wednesday 08:30 - 00:30
Thursday 08:30 - 00:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 02:30 - 00:30

Telephone

+251582265776

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Revenue Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Revenue Bureau:

Shortcuts

Share