Bahirdar Zuria Communication

Bahirdar Zuria Communication 07448

04/06/2026
ለቢሮ አገልግሎት የሚዉል G+7 ዘመናዊ ህንጻ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለበሰሜን ጎጃም ዞን በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ  ለቢሮ አገልግሎት የሚዉል G+7 ዘመናዊ ህንጻ ግንባታ የዞንና የወረዳ...
04/06/2026

ለቢሮ አገልግሎት የሚዉል G+7 ዘመናዊ ህንጻ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ

በሰሜን ጎጃም ዞን በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ለቢሮ አገልግሎት የሚዉል G+7 ዘመናዊ ህንጻ ግንባታ የዞንና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

የባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ጋርዳቸው መኩሪያ በህንጻ ግንባታ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተገኝተው እንደተናገሩት የባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ለአገልግሎት አሰጣጥ ምቹ ያልሆኑ ተቋማት ያሉበት በመሆኑ የቢሮ ህንጻ ግንባታ መጀመሩ ለሰራተኞችና ለተገልጋዮች ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል።

በ3ሺ 280ካሬ ሜትር የቦታ ስፋት ያለው G+7 የቢሮ ህንጻ ግንባታ ለመጀመር ወደ ስራ መገባቱን የገለጹት አቶ ጋርዳቸው በምእራፍ አንድ የመሰረትና የስላቭ እንዲሁም በምእራፍ ሁለት የግንባታ ሂደት ከG+1 እስከ G+7የሚከናወን የግንባታ ሂደት ያለው ሲሆን ግንባታውን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 998 ሚሊየን ብር እንደሚወስድ ገልጸዋል።

የምዕራፍ 1 ግንባታውን የመቅደላ ኮንስትራክሽን በ113ሚሊየን ብር ለመስራት ውል በመውሰድ ስራ መጀመሩን የገለጹት ኃላፊው ህንጻውን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከመንግስት፣ከማህበረሰቡ፣ከነጋዴው፣ከመንግስት ሰራተኞችና ከአልሚ ማህበረሰቡ በቅንጅት ለመስራት እንደታሰበ ገልጸዋል።

የባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ተመስገን ደጋረገ በበኩላቸው የተጀመረው የህንጻ ግንባታ
ለሠራተኞች ምቹ የስራ ቦታን ለመፍጠር እና የዘመነ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት እጅግ የሚያግዝ መሆኑንም ገልጸዋል።

ተመካክረን፣ ተጋግዘን፣ ተወያይተንና አንድነታችን አጠናክረን ህዝባችንን አስተባብረን ለመገንባትም ይሁን ለማስመረቅ እንሰራለን ያሉት አቶ ተመስገን የሚገነባው የወረዳ አስተዳደር ህንጻ የነበረውን የቢሮ ጥበትና ምቹ ያልሆነ የስራ አካባቢ ችግርን እንደሚያቃልልም ገልጿል ።

03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ የተሰማውን ደስታ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፀጥታ ኃይል አካላት እንዲሁም ሕዝቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተወጡት ሀገራዊ ኃላፊነት እና ላሳዩት ፅናትም ምክር ቤቱ ያለውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጿል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው፣ “ልዩነቶቻችንን እና ችግሮቻችንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመፈታት በምርጫው የታየውን ሰላም በማስቀጠል የበኩላችንን ሚና እንወጣ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ እንቁም” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

03/06/2026

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"

ክቡር አረጋ ከበደ
የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር

በወረዳው የጤና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከ20 በላይ  የጤና ፕሮጀክቶች በ196 ሚሊየን ብር  እየተገነቡ ነው።በሰሜን ጎጃም ዞን በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ የጤና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከ20በ...
03/06/2026

በወረዳው የጤና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከ20 በላይ የጤና ፕሮጀክቶች በ196 ሚሊየን ብር እየተገነቡ ነው።

በሰሜን ጎጃም ዞን በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ የጤና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከ20በላይ የጤና ፕሮጀክቶች በ196ሚሊየን ብር እየተገነቡ መሆኑን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።

የባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል በሁሉ የጤና መሠረተ ልማትን በማስፋፋት ለማኅበረሰቡ ሁሉን አቀፍ፣ ፍትሐዊ እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በወረዳው በመንግሥት እና በዪኒሴፍ የገንዘብ ድጋፍ ከ20 በላይ የጤና ፕሮጀክቶች 196ሚሊየን ተመድቦላቸው እየተገነቡ ሲሆን የተጀመሩ የጤና ተቋማትን ማጠናቀቅ፣አዳዲስ ግንባታወችን ማካሄድ፣ጤና ጣቢያወችን ጽዱና ማራኪ ማድረግና ሌሎችም ስራወች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

በወረዳው ከዚህ በፊት ግንባታቸው ተጀምሮ በተለያየ ምክንያት ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን የማጠናቀቅ ስራ መሰራቱን የገለጹት አቶ ዳንኤል በተያዘው በጀት አመት የሮቢት ጤና ጣቢያ ደረጃ ማሳደግ፣የቅንባባ ቀዶ ህክምና ግንባታ የማጠናቀቅ፣በርካታ መጸዳጃ ቤቶች በአንዳሳና በአቡነሐራ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በወረዳው ከሚገነቡ ፕሮጀክቶች መካከል የይነሳ ጤና ጣቢያ ደረጃ ማሳደግ ፣የሰቀለጥ ጤና ባለሙያወች መኖሪያ ቤት ግንባታ፣የወረዳ ማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ቤት እንዲሁም የወንዳጣ ሁሉን አቀፍ ጤና ኬላ ግንባታወች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

በተያዘው በጀት አመት የጤና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ አዲስ የጤና ፕሮጀክቶች ተጀምረው በፍጥነት ግንባታቸው እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት አቶ ዳንኤል ወጅር ግንብና ወንዳጣ ቀበሌወች ላይ አጠቃላይ ጤና ኬላ ግንባታወች ፣እንዲሁም ይጎዲ ወገልሳ እና ማቋል መሰረታዊ ጤና ኬላ ግንባታወች በፍጥነት እየተገነቡ መሆኑን ጠቁመዋል።

በወረዳው የጤና ተቋማትን ሳቢና ማራኪ ለማድረግ 11.5 ሚሊየን ብር ወጭ በማደረግ በአንዳሳ፣ቅንባባ ፣ላታ እና ይነሳ ጤና ጣቢያወች ባዞላ የማንጠፍ እና ጤና ተቋማትን ጽዱ የማድረግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ኃላፊው ተናግረዋል።

03/06/2026
03/06/2026

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahirdar Zuria Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share