Amhara Rural Roads Construction Agency

Amhara Rural Roads Construction Agency It is a non-profitable organization found in Amhara region working on road infrastructure developmen

የአማራ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን ከየት ወደየት


የፌዴራል መንግስት የክልል መንግስታት መፈጠርን ተከትሎ ሁሉም የገጠር መንገድ ግንባታዎች፣ ጥገናዎችና በጀታቸው ከመጋቢት ወር 1985 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ወደ ክልል መንግስታት እንዲዛወሩ አደረገ፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ኘሮጀክቶችን፣ የሰው ኃይላቸውን፣ መሳሪያና ሌሎች ቁሳቁሶችን ለየክልል ስራና ከተማ ልማት ቢሮዎች አስረከበ፡፡ የአማራ ክልል ስራና ከተማ ልማት ቢሮም በክልሉ የሚገኙ የገጠር መንገዶችን ተረክቦ የገጠር መንገዶች መምሪያ አቋቋመ፡፡የፌዴራል መንግስት የክልል መንግስታት መፈጠርን ተከትሎ ሁሉም የገጠር መንገድ ግንባታዎች፣ ጥ

ገናዎችና በጀታቸው ከመጋቢት ወር 1985 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ወደ ክልል መንግስታት እንዲዛወሩ አደረገ፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ኘሮጀክቶችን፣ የሰው ኃይላቸውን፣ መሳሪያና ሌሎች ቁሳቁሶችን ለየክልል ስራና ከተማ ልማት ቢሮዎች አስረከበ፡፡ የአማራ ክልል ስራና ከተማ ልማት ቢሮም በክልሉ የሚገኙ የገጠር መንገዶችን ተረክቦ የገጠር መንገዶች መምሪያ አቋቋመ፡፡


የገጠር መንገዶች መስፋፋት ለክልሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት መፋጠን ወሳኝ በመሆኑ ላይ የበለጠ ግንዛቤ ስለተፈጠረና በቦርድ የሚተዳደር፣ የተጠናከረ፣ ቀልጣፋ ቢሮክራሲ የሚጠቀም የገጠር መንገዶች ተቋም ማደራጀት በማስፈለጉ የገጠር መንገዶች መምሪያ የሚለው ከስራና ከተማ ልማት ተገንጥሎ ጥቅምት 1987 ዓ.ም ራሱን ችሎ መጀመሪያ በድርጅት ቀጥሎ በባለስልጣን ደረጃ ተቋቋመ፡፡የገጠር መንገዶች መስፋፋት ለክልሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት መፋጠን ወሳኝ በመሆኑ ላይ የበለጠ ግንዛቤ ስለተፈጠረና በቦርድ የሚተዳደር፣ የተጠናከረ፣ ቀልጣፋ ቢሮክራሲ የሚጠቀም የገጠር መንገዶች ተቋም ማደራጀት በማስፈለጉ የገጠር መንገዶች መምሪያ የሚለው ከስራና ከተማ ልማት ተገንጥሎ ጥቅምት 1987 ዓ.ም ራሱን ችሎ መጀመሪያ በድርጅት ቀጥሎ በባለስልጣን ደረጃ ተቋቋመ፡፡


የአማራ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን ከተቋቋመ ጊዜ ጀመሮ እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ 2756 ኪ.ሜ የአዲስ መንገድ ግንባታ ስራ ያከናወነ ሲሆን በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን፣ በህብረተሰቡና በሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች አማካኝነት 4861.9 ኪ.ሜ የአዲስ መንገድ ግንባታ ስራ ተከናውኗል፡፡ ይህም የክልሉን የመንገድ ኔትወርክ በ1986 ዓ.ም ከነበረበት 3918.6 ኪ.ሜ በ2002 ዓ.ም መጨረሻ ወደ 7617.9 ኪ.ሜ አሳድጐታል፡፡ በመሆኑም በ1987 ዓ.ም በ1000 ኪ.ሜ ስኩዬር 20 ኪ.ሜ የነበረውን የክልሉ የመንገድ ሽፋን በ2002 ዓ.ም መጨረሻ 48 ኪ.ሜ በማድረስ የመንገድ ሽፋኑን ከእጥፍ በላይ ማሳደግ ተችሏል፡፡ በመልሶ ግንባታና ተከታታይ ጥገና የበርካታ ነባር መንገዶች የጥራት ደረጃም እንዲሻሻል ተደርጓል፡፡የአማራ ገጠር መንገዶች ባለስልጣን ከተቋቋመ ጊዜ ጀመሮ እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ 2756 ኪ.ሜ የአዲስ መንገድ ግንባታ ስራ ያከናወነ ሲሆን በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን፣ በህብረተሰቡና በሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች አማካኝነት 4861.9 ኪ.ሜ የአዲስ መንገድ ግንባታ ስራ ተከናውኗል፡፡ ይህም የክልሉን የመንገድ ኔትወርክ በ1986 ዓ.ም ከነበረበት 3918.6 ኪ.ሜ በ2002 ዓ.ም መጨረሻ ወደ 7617.9 ኪ.ሜ አሳድጐታል፡፡ በመሆኑም በ1987 ዓ.ም በ1000 ኪ.ሜ ስኩዬር 20 ኪ.ሜ የነበረውን የክልሉ የመንገድ ሽፋን በ2002 ዓ.ም መጨረሻ 48 ኪ.ሜ በማድረስ የመንገድ ሽፋኑን ከእጥፍ በላይ ማሳደግ ተችሏል፡፡ በመልሶ ግንባታና ተከታታይ ጥገና የበርካታ ነባር መንገዶች የጥራት ደረጃም እንዲሻሻል ተደርጓል፡፡


በክልሉ ከሚገኘው 7617.9 ኪ.ሜ ጠቅላላ የመንገድ ኔትወርክ 3665.6 ኪ.ሜ የሚሆነው በባለስልጣኑ ስር የሚተዳደር ሲሆን 3952.3 ኪ.ሜ የሚሆነው ደግሞ በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡በክልሉ ከሚገኘው 7617.9 ኪ.ሜ ጠቅላላ የመንገድ ኔትወርክ 3665.6 ኪ.ሜ የሚሆነው በባለስልጣኑ ስር የሚተዳደር ሲሆን 3952.3 ኪ.ሜ የሚሆነው ደግሞ በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡


የነባር መንገዶች ጥገና ስራ በተመለከተ መንገዶች በየጊዜው ካልተጠኑ አገልግሎት እስከ ማቆም ሊደርሱ ስለሚችሉ ጥገና ያስፈልጋቸዋል፡፡ በመሆኑም ባለስልጣኑ ቀላልና ተከታታይ ጥገና፣ ወቅታዊ ጥገናና ድንገተኛ ጥገና ስራ በባለስልጣኑ ስር ባሉ የጎንደር፣ጐጃም፣ወሎና ደብረብርሃን የገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤቶች አማካኝነት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በክልሉ እስከ 1991 ዓ.ም ድረስ ከፍተኛ የሆነ የመንገድ መሰረተ-ልማት አለመስፋፋት ችግርና የበጀት እጥረትም ስለነበር በአብዛኛው ትኩረት ይሰጥ የነበረው ለአዲስ መንገዶች ግንባታ ስራ በመሆኑ ለነባር መንገዶች ጥገና ብዙም ትኩረት አይሰጥም ነበር፡፡ ከ1991 ዓ.ም ወዲህ ግን በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ከዋና መንገድ ጋር ያልተገናኙ በርካታ ወረዳዎች እንደዲገናኙ በመደረጉና በፌዴራል ደረጃ የመንገድ ፈንድ ጽ/ቤት ተቋቁሞ ለጥገና ስራ የበጀት ምንጭ እየሆነ በመምጣቱ ከግንባታው ጐን ለጐን የነባር መንገዶች ጥገና ስራም ትኩረት ተሰጥቶት በስፋት እየተሰራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ከ1992-2002 ዓ.ም መጨረሻ ባሉት ዓመታት በመደበኛና ወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች 16665 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ስራ ተከናውኗል፡፡ በባለስልጣኑ አስተዳደር ስር ያሉ ነባር የገጠር መንገዶች የጥገና ሽፋን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት በ1992 ዓ.ም 16.5% የነበረውን የነባር መንገዶች ጥገና ሽፋን በ2002 ዓ.ም መጨረሻ 88.3% ማድረስ ተችሏል፡፡የነባር መንገዶች ጥገና ስራ በተመለከተ መንገዶች በየጊዜው ካልተጠኑ አገልግሎት እስከ ማቆም ሊደርሱ ስለሚችሉ ጥገና ያስፈልጋቸዋል፡፡ በመሆኑም ባለስልጣኑ ቀላልና ተከታታይ ጥገና፣ ወቅታዊ ጥገናና ድንገተኛ ጥገና ስራ በባለስልጣኑ ስር ባሉ የጎንደር፣ጐጃም፣ወሎና ደብረብርሃን የገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤቶች አማካኝነት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በክልሉ እስከ 1991 ዓ.ም ድረስ ከፍተኛ የሆነ የመንገድ መሰረተ-ልማት አለመስፋፋት ችግርና የበጀት እጥረትም ስለነበር በአብዛኛው ትኩረት ይሰጥ የነበረው ለአዲስ መንገዶች ግንባታ ስራ በመሆኑ ለነባር መንገዶች ጥገና ብዙም ትኩረት አይሰጥም ነበር፡፡ ከ1991 ዓ.ም ወዲህ ግን በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ከዋና መንገድ ጋር ያልተገናኙ በርካታ ወረዳዎች እንደዲገናኙ በመደረጉና በፌዴራል ደረጃ የመንገድ ፈንድ ጽ/ቤት ተቋቁሞ ለጥገና ስራ የበጀት ምንጭ እየሆነ በመምጣቱ ከግንባታው ጐን ለጐን የነባር መንገዶች ጥገና ስራም ትኩረት ተሰጥቶት በስፋት እየተሰራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ከ1992-2002 ዓ.ም መጨረሻ ባሉት ዓመታት በመደበኛና ወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች 16665 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ስራ ተከናውኗል፡፡ በባለስልጣኑ አስተዳደር ስር ያሉ ነባር የገጠር መንገዶች የጥገና ሽፋን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት በ1992 ዓ.ም 16.5% የነበረውን የነባር መንገዶች ጥገና ሽፋን በ2002 ዓ.ም መጨረሻ 88.3% ማድረስ ተችሏል፡፡


ባለስልጣኑ በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ለህብረተሰቡ የበለጠ ተደራሽ ለመሆን ያስችለው ዘንድ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙን ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲያጐለብት የክልሉ መንግስት በተለይም በአለት አምስት አመታት የባለስልጣኑ አቅም በሰው ኃይል፣ በግንባታ መሳሪያ፣ በፋይናንስ፣ በአሰራርና በአደረጃጀት እንዲጠናከር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ በማድረጉ ባለስልጣኑ በአምስት አመቱ የመንገድ ዘርፍ ልማት በመርሃ ግብር ከ100% በላይ አፈፃፀም በማስመዝገብ ስኬታማ በሆነ መልኩ አጠናቋል፡፡ባለስልጣኑ በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ለህብረተሰቡ የበለጠ ተደራሽ ለመሆን ያስችለው ዘንድ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙን ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲያጐለብት የክልሉ መንግስት በተለይም በአለት አምስት አመታት የባለስልጣኑ አቅም በሰው ኃይል፣ በግንባታ መሳሪያ፣ በፋይናንስ፣ በአሰራርና በአደረጃጀት እንዲጠናከር ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ በማድረጉ ባለስልጣኑ በአምስት አመቱ የመንገድ ዘርፍ ልማት በመርሃ ግብር ከ100% በላይ አፈፃፀም በማስመዝገብ ስኬታማ በሆነ መልኩ አጠናቋል፡፡


ባለስልጣኑ እስከ 1997 ዓ.ም ከ7 በማይበልጡ ኘሮጀክቶች የግንባታ ስራ ያከናውን የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በአንድ ጊዜ 21 የራስ ኃይል የግንባታ ኘሮጀክትን ከፍቶ የግንባታ ስራ መስራትና 21 ኘሮጀክቶችን በአግባቡ መምራት በሚችልበት ደረጃ ላይ አቅሙን አሳድጓል፡፡ በመሆኑም በቀጣይ 5 ዓመታት ተግባራዊ ለማድረግ የተዘጋጀውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት ከሚኖረው ቁልፍ ሚና አንፃር የገጠር መንገድ መሰረተ ልማትን ማስፋፋት ወሳኝ ቅደመ ሁኔታ ነው፡፡ ባለስልጣኑ ይህንን ተልዕኮ ባገናዘበ መልኩ የአምስት አመት የመንገድ ዘርፍ ልማት ዕቅድ ያዘጋጀ ሲሆን ከፍተኛ የገጠር መንገዶች ግንባታ በማከናወን በ5 ዓመቱ መጨረሻ የክልሉን የመንገድ ኔትወርክ አሁን ካለበት 7617.9 ኪ.ሜ ወደ 11617 ኪ.ሜ በማሳደግ የመንገድ ሽፋኑን አሁን ካለበት በ1000 ካሬ .ኪ.ሜ 48 ኪ.ሜትር ወደ 74 ኪ.ሜትር ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል፡፡ በ5 ዓመቱ መጨረሻ የነባር ገጠርመንገዶች ጥገና ሽፋንም አሁን ከአለበት 88.3% ወደ 95% የሚደርስ ይሆናል፡፡ባለስልጣኑ እስከ 1997 ዓ.ም ከ7 በማይበልጡ ኘሮጀክቶች የግንባታ ስራ ያከናውን የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በአንድ ጊዜ 21 የራስ ኃይል የግንባታ ኘሮጀክትን ከፍቶ የግንባታ ስራ መስራትና 21 ኘሮጀክቶችን በአግባቡ መምራት በሚችልበት ደረጃ ላይ አቅሙን አሳድጓል፡፡ በመሆኑም በቀጣይ 5 ዓመታት ተግባራዊ ለማድረግ የተዘጋጀውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት ከሚኖረው ቁልፍ ሚና አንፃር የገጠር መንገድ መሰረተ ልማትን ማስፋፋት ወሳኝ ቅደመ ሁኔታ ነው፡፡ ባለስልጣኑ ይህንን ተልዕኮ ባገናዘበ መልኩ የአምስት አመት የመንገድ ዘርፍ ልማት ዕቅድ ያዘጋጀ ሲሆን ከፍተኛ የገጠር መንገዶች ግንባታ በማከናወን በ5 ዓመቱ መጨረሻ የክልሉን የመንገድ ኔትወርክ አሁን ካለበት 7617.9 ኪ.ሜ ወደ 11617 ኪ.ሜ በማሳደግ የመንገድ ሽፋኑን አሁን ካለበት በ1000 ካሬ .ኪ.ሜ 48 ኪ.ሜትር ወደ 74 ኪ.ሜትር ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል፡፡ በ5 ዓመቱ መጨረሻ የነባር ገጠርመንገዶች ጥገና ሽፋንም አሁን ከአለበት 88.3% ወደ 95% የሚደርስ ይሆናል፡፡


በሌላ መልኩ ሁሉን አቀፍ የገጠር መንገድ ተደራሽነት ኘሮግራም (universal Rural Road Access Program) አማካኝነት በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች ክረምት ከበጋ የሚያስኬድ መንገድ በመገንባት የቀበሌ ማዕከላቱን ከዋናና አገናኝ መንገዶች ጋር ለማገናኘት በተሰበሰበ መረጃ ከ3113 የገጠር ቀበሌዎች መካከል 918 ቀበሌዎች ከዋናና አገናኝ መንገዶች ጋር የተገናኙ ሲሆን ቀሪ 2195 ቀበሌዎችን ለማገናኘት በአምስት አመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ 18000 ኪ.ሜትር የቀበሌ መንገዶች ግንባታ ለማከናወን ዕቅድ ተይዟል፡፡ በአምስት አመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመደበኛና ወቅታዊ የጥገና አይነቶች 34640 ኪ.ሜትር የቀበሌ መንገዶች ጥገና ለመስራትም ታቅዷል፡፡በሌላ መልኩ ሁሉን አቀፍ የገጠር መንገድ ተደራሽነት ኘሮግራም (universal Rural Road Access Program) አማካኝነት በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች ክረምት ከበጋ የሚያስኬድ መንገድ በመገንባት የቀበሌ ማዕከላቱን ከዋናና አገናኝ መንገዶች ጋር ለማገናኘት በተሰበሰበ መረጃ ከ3113 የገጠር ቀበሌዎች መካከል 918 ቀበሌዎች ከዋናና አገናኝ መንገዶች ጋር የተገናኙ ሲሆን ቀሪ 2195 ቀበሌዎችን ለማገናኘት በአምስት አመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ 18000 ኪ.ሜትር የቀበሌ መንገዶች ግንባታ ለማከናወን ዕቅድ ተይዟል፡፡ በአምስት አመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመደበኛና ወቅታዊ የጥገና አይነቶች 34640 ኪ.ሜትር የቀበሌ መንገዶች ጥገና ለመስራትም ታቅዷል፡፡


የባለስልጣኑን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የበለጠ በማጠናከርና የተፈጠረውን አቅም አሟጦ በመጠቀም እንዲሁም የክልሉን ህብረተሰብ ከመቸውም ጊዜ በላቀ ደረጃ በመንገድ ልማት ስራው የሚሳተፍበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የአምስት አመቱን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል፡፡የባለስልጣኑን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የበለጠ በማጠናከርና የተፈጠረውን አቅም አሟጦ በመጠቀም እንዲሁም የክልሉን ህብረተሰብ ከመቸውም ጊዜ በላቀ ደረጃ በመንገድ ልማት ስራው የሚሳተፍበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የአምስት አመቱን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል፡፡

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን  ኤጀንሲ ባለፉት 9 ወራት 48.34 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ እና ከ4 ሽህ ኪ.ሜ በላይ በላይ የነባር መንገዶች ጥገና ማከናወኑ ተገለፀ፡፡የአማራ ገጠር መ...
20/04/2026

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ባለፉት 9 ወራት 48.34 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ እና ከ4 ሽህ ኪ.ሜ በላይ በላይ የነባር መንገዶች ጥገና ማከናወኑ ተገለፀ፡፡
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የ2018 ዓ.ም የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በ12/08/2018 ዓ.ም በተካሄደበት ወቅት እንደተገለፀዉ ኤጀንሲዉ ባለፉት 9 ወራት 56.08 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ 48.34 ኪ.ሜ መንገድ በመገንባት የ9 ወሩን ዕቅድ 86.2%፣የዓመቱን ዕቅድ ደግሞ 47.32% ፈፅሟል፡፡ የተለያየ መጠን ባላቸዉ ስትራክቸሮች ግንባታ በበጀት ዓመቱ 227 የተለያየ መጠን ያላዉ ስትራክቸሮች ለመገንባት ታቅዶ በ153 የተለያየ መጠን ባላቸዉ ስትራክቸሮች በተለያየ የአፈፃፀም ደረጃ ላይ የሚገኙ ግንባታዎች እየተከናወኑ እንደሆነ በዉይይቱ ተገልፆል፡፡
በነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ዘርፍ ኤጀንሲዉ ባለፉት 9ወራት በመደበኛ እና በወቅታዊ የጥገና ዓይነቶች 5,164.61 ኪ.ሜ የነባር ገጠር መንገዶች ጥገና ለማከናወን አቅዶ 4,506.84 ኪ.ሜ መንገድ በመጠገን የ9 ወሩን ዕቅድ 87.26%፣የዓመቱን ዕቅድ ደግሞ 74.64% ማሳካት እንደተቻለ በዉይይቱ ተመልክቷል፡፡
ኤጀንሲዉ በበጀት ዓመቱ ግንባታ ለማከናወን በዕቅድ ከያዛቸዉ 34 የመንገድ/ድልድይ ፐሮጀክቶች መካከል በፈተና ዉስጥ ሆኖ በ32 ፕሮጀክቶች ግንባታ እያከናወነ እንደሆነ እና የ9 ወሩ አፈፃፀም በበጀት ዓመቱ ከተያዘዉ ዕቅድ አንፃር ሲታይ ዉሱንት ያለበት ቢሆንም ከባለፈዉ ዓመት ተመሣሣይ ወቅት አንፃር ሲታይ ግን የተሻለ እንደሆነ በዉይይቱ ተመልክቷል፡፡
አሁን ላይ በተለይ በዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ደረጃ የተከሰተዉ የነዳጅ እጥረት በግንባታ እና ጥገና ሥራዉ ላይ ጫና እያሳደረ ቢሆንም የሚያጋጥሙ ችግሮችን ተጋፍጦ የግንባታ እና ጥገና ሥራዎችን በማከናወን የኤጀንሲዉን አፈፃፀም ከፍ ለማድረግ ሁሉም የኤጀንሲዉ አመራር እና ሰራተኛ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት በዉይይቱ ተገልፆል፡፡አሁን ካለዉ የነዳጅ እጥረት አንፃር ነዳጅን በቁጠባ ለመጠቀም እንዲቻል የስትራክቸር ግንባታዎችን የማከናወን እና በበጀት ዓመቱ ለማጠናቀቅ በዕቅድ ለተያዙ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ ነዳጅ እና ሌሎቸ የግንባታ ግብዓቶችን ማሟላት እንደሚገባም በዉይይቱ ተመልክቷል፡፡ኤጀንሲዉ በበጀት ዓመቱ 6/ስድስት/ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ ለዉይይት ከቀረበዉ ሪፖርት ለመረዳት ተችሏል፡፡
በኤጄንሲዉ ዕቅድ አፈፃፀም ዉይይት የኤጀንሲዉ ዋና መ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም ከክልሉ ፕላን ኮሚሽን ጥሪ የተደረገላቸዉ ባለሙያዎች ተሣታፊ ሆነዋል፡፡

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም  አደረሳችሁ!በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆንላች...
09/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆንላችሁ ኤጀንሲው መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
መልካም የትንሳኤ በዓል!
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ

የመኮይ- ማጀቴ መንገድ ለህብረተሰቡ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የተለያዬ መጠን ያላቸው ድልድዮች ግንባታ እየተከናወነ ነው፡፡የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በበጀት ዓ...
09/04/2026

የመኮይ- ማጀቴ መንገድ ለህብረተሰቡ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የተለያዬ መጠን ያላቸው ድልድዮች ግንባታ እየተከናወነ ነው፡፡
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በበጀት ዓመቱ የግንባታ ስራ ከሚያከናውንባቸው 33 የመንገድ/ድልድይ ፕሮጀክቶች መካከል 39.55 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው እና በ2009 ዓ.ም የተጀመረው የመኮይ- ማጀቴ መንገድ ስራ ኘሮጀክት አንዱ ነው፡፡ የመኮይ- ማጀቴ መንገድ ስራ ኘሮጀክት ኤጀንሲው የተለያዬ መጠን ያላቸው ድልድዮች ግንባታ ከሚያከናውንባቸዉ ኘሮጀክቶች መካከልም ተጠቃሽ ኘሮጀክት ነው፡፡
የመኮይ- ማጀቴ መንገድ ስራ ኘሮጀክት የመንገድ ግንባታዉ ቀደም ብሎ የተከናወነ ቢሆንም በርካታ አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ ማከናወን የሚጠይቅ ኘሮጀክት በመሆኑ መንገዱ ለህብረተሰቡ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዬ መጠን ያላቸው ድልድዮች ግንባታ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ እስከ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ባለው ጊዜ ውስጥም በርካታ አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ትላልቅ ድልድዮች ተገንብተዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመት በመኮይ- ማጀቴ መንገድ ስራ ኘሮጀክት ኤጀንሲው ከክልሉ መንግስት በተመደበ ብር 27,597,194.00 /ሃያ ሰባት ሚሊዮን አምስት መቶ ዘጠና ሰባት ሽህ አንድ መቶ ዘጠና አራት ብር/ በጀት 40 ሜትር ርዝመት ያለው የሳል ወንዝ ድልድይ ግንባታ እና ሁለት አነስተኛ ድልድዮች ግንባታ ለማከናወን አቅዶ የግንባታ ስራ እያከናወነ ሲሆን እስከ መጋቢት መጨረሻ 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ የሳል ወንዝ ድልድይ የግንባታው 65% ተጠናቋል፡፡ የሁለት አነስተኛ ድልድዮች ግንባታ ደግሞ በአማካኝ 61% የሚሆነው የግንባታ ስራ ተከናውኗል፡፡
የመኮይ- ማጀቴ መንገድ ስራ ኘሮጀክት በሰሜን ሸዋ ዞን የአንፆኪያገምዛ እና የኤፍራታናግድም ወረዳ ነዋሪዎችን የመንገድ ተጠቃሚ በማድረግ የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮች ለመፍታት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት የመንገድ ኘሮጀክት ነው፡፡ ኘሮጀክቱ በተለይ በአካባቢው በመስኖ የሚለሙ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በወቅቱ ወደ ገበያ ለማድረስ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡

የጎንደር ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 9 ወራት 660.7 ኪ.ሜ የነባር መንገዶች ጥገና አከናወነ።የጎንደር ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ስ...
09/04/2026

የጎንደር ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 9 ወራት 660.7 ኪ.ሜ የነባር መንገዶች ጥገና አከናወነ።
የጎንደር ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ስር ከሚገኙ 6 ጥገና ጽ/ቤቶች መካከል አንዱ ሲሆን በ2018 በጀት አመት በ37 የጥገና መስመሮች 939.40 ኪ.ሜ የነባር መንገዶች ጥገና ለማከናወን አቅዶ ባለፉት 9 ወራት በ26 የጥገና መስመሮች 660.7 ኪ.ሜ መንገድ በመጠገን የ9 ወሩን እቅድ 83.22%፣ የአመቱን እቅድ ደግሞ 70.3% አከናውኗል።
በጎንደር ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ባለፉት 9 ወራት ከተከናወነው 660.7 ኪ.ሜ የነባር መንገዶች ጥገና መካከል 572.11 ኪ.ሜ የሚሆነው በመደበኛ የጥገና ስልት የተከናወነ ሲሆን 88.59 ኪ.ሜ የሚሆነው ደግሞ በወቅታዊ የጥገና ስልት የተከናወነ ነው።
ጥገና ጽ/ቤቱ ባለፉት 9 ወራት ካከናወነው 660.7 ኪ.ሜ የነባር መንገዶች ጥገና መካከል 497.79 ኪ.ሜ የሚሆነው በመሳሪያ ሀይል የተጠገነ ሲሆን ቀሪው 162.91 ኪ.ሜ የሚሆነው ደግሞ በሰው ሃይል የጥገና ስልት የተጠገነ ነው።
የጎንደር ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት በአሁኑ ወቅት ከአምባ ጊዮርጊስ- ወይራ በር- ስላሬ፣ ማክሰኝት- ደጎማ እና ዛሪማ- ወራቆ ባሉ 3/ሶስት/ የጥገና መስመሮች በአጠቃላይ 96.1 ኪ.ሜ ርዝመት ያላቸው ነባር መንገዶችን በመደበኛ የጥገና አይነት እየጠገነ ሲሆን በቁስቋም- ሮቢት የጥገና መስመር ደግሞ የስትራክቸር ጥገና ስራ እያከናወነ ይገኛል።

በሰሜን ወሎ ዞን የቡግና ወረዳን በደቡብ ጐንደር ዞን ከሚገኘው መቀጠዋ ወረዳ ጋር የሚያስተሳስር የአይና-ቆብ-ዘብሎ-ተከዜ-አጊሣ መንገድ ግንባታ እየተከናወነ ነው፡፡በክልሉ ሰሜን ወሎ እና ደቡ...
07/04/2026

በሰሜን ወሎ ዞን የቡግና ወረዳን በደቡብ ጐንደር ዞን ከሚገኘው መቀጠዋ ወረዳ ጋር የሚያስተሳስር የአይና-ቆብ-ዘብሎ-ተከዜ-አጊሣ መንገድ ግንባታ እየተከናወነ ነው፡፡
በክልሉ ሰሜን ወሎ እና ደቡብ ጐንደር ዞን መካከል ያለውን ከዞን ዞን የመንገድ ትስስር ለማጠናከር እና የአካባቢውን ህብረተሰብ የመንገድ ትራንስፖርት ችግር ለመፍታት በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ከሚከናወኑ የመንገድ ኘሮጀክቶች መካከል 130 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው እና በ2010 ዓ.ም የተጀመረው የአይና-ቆብ-ዘብሎ-ተከዜ-አጊሣ መንገድ ግንባታ ተጠቃሽ ነው፡፡
የአይና-ቆብ-ዘብሎ-ተከዜ-አጊሣ መንገድ ኘሮጀክት እስከ 2017 ዓ.ም በተከናወነው የግንባታ ስራ ከጠቅላላ ርዝመቱ 39.52 ኪ.ሜ የሚሆነው የመንገድ ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን በተያዘው በጀት ዓመት ከክልሉ መንግስት በተመደበ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት 4 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ የቅየሳ ስራ 2.5 ኪ.ሜ፣ የምንጣሮና ጠረጋ 1 ኪ.ሜ ፣የአፈር ድልዳሎ ስራ 0.8 ኪ.ሜ አከናውኗል፡፡ የግንባታ ማሽነሪ እጥረት እና ብልሽት፣ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት የካቲት መጀመሪያ አካባቢ ስራ መጀመር እና ግንባታው የሚከናወንበት አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የአለት ቆረጣ ስራ የሚጠይቅ አስቸጋሪ የቦታ አቀማመጥ ያለው መሆን የኘሮጀክቱ የግንባታ ስራ በተያዘው እቅድ መሰረት እንዳይከናወን አሉታዊ ጫና ያሳደሩ ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸው፡፡
የአይና-ቆብ-ዘብሎ-ተከዜ-አጊሣ መንገድ ግንባታ በሰሜን ወሎ ዞን የቡግና ወረዳ እና በደቡብ ጐንደር ዞን የመቀጠዋ ወረዳ ነዋሪዎችን የመንገድ ተጠቃሚ በማድረግ በመንገድ ተደራሽነት ችግር ምክንያት ህብረተሰቡን እያጋጠመ ያሉ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች እንዲፈቱ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው መንገድ ነው፡፡
የአይና-ቆብ-ዘብሎ-ተከዜ-አጊሣ መንገድ ግንባታ ከአይና- ዛጐች-ጥጥራ እና ከክምር ድንጋይ- አጃ-መቀጠዋ (አጊሣ) ከሚገነቡ የመንገድ ኘሮጀክቶች ጋር የሚተሳሰር መንገድ በመሆኑ በሰሜን ወሎ እና በደቡብ ጐንደር ዞኖች መካከል ያለውን የመንገድ ኔትወርክ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጠናከር በማድረግ ረገድም ትልቅ ጠቀሜታ ይሰጣል፡፡

በለዉጥ ሥራ አመራር እና ኢንፎርሜን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡ለአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋናዉ መ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞ...
03/04/2026

በለዉጥ ሥራ አመራር እና ኢንፎርሜን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡
ለአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋናዉ መ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች የለዉጥ ሥራ አመራር እና ኢንፎርሜን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) ለተቋማዊ ስኬት ያለዉን ፋይዳ የሚያስገነዝብ ሥልጠና በ25/7/2018 ዓ.ም ተሰጥቷል፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዉ በለዉጥ ሥራ አመራር እና ኢንፎርሜን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) የሥራ ሂደት የተዘጋጀ ሲሆን ስለ ለዉጥ ሥራ አመራር ምንነት፣በካይዘን ፅንሰ ሀሳብ፣ በመረጃ አያያዝና አደረጃጀት እንዲሁም በኤጀንሲዉ እየተተገበሩ ባሉ የሶፍትዌር ቴክኖሎጂዎች ዙሪያ የስልጠናዉ ተሳታፊዎች ግንዛቤ እንዲይዙ ተደርጓል፡፡
በስልጠና መድረኩ የተገኙት የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቀለሙ ሙሉነህ በሰጡት አስተያየት አሁን ካለዉ ቴክኖሎጂ ጋር አብሮ የሚሄድ አቅም መገንባት አስፈላጊ በመሆኑ በቴክኖሎጂ ዙሪያ ያለንን ግንዛቤ ለማሳደግ እና በቴክኖሎጂ ትግበራ ያለንን ክፍተት ለመሙላት ስልጠናዉ ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዉ ተሳታፊዎች በበኩላቸዉ ሥልጠናዉ በቴክኖሎጂ ትግበራ እንዲሁም በመረጃ አያያዝ እና አደረጃጀት ሂደት የሚታዩ ክፍተቶችን የሚሞላ በመሆኑ በቀጣይ መሰል ሥልጠናዎች ጥገና ጽ/ቤት እና ፕሮጀክት ድረስ በተጠናከረ መልኩ መሰጠት እንዳለባቸዉ ጠቁመዋል፡፡

በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘዉ  የጊናአገር-ሰጦን -መተህብላ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የጠቅላላ ርዝመቱ 35.7%(ፐርሰንት) የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፡፡በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘዉ እና ...
03/04/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘዉ የጊናአገር-ሰጦን -መተህብላ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የጠቅላላ ርዝመቱ 35.7%(ፐርሰንት) የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፡፡
በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘዉ እና 48 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የጊናአገር-ሰጦን -መተህብላ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በ2013 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን እስከ መጋቢት አጋማሽ/2018 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ የግንባታ ሥራ በአማካይ የጠቅላላ ርዝመቱ 35.7% ግንባታ ተጠናቋል፡፡
በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የሚከናወነዉ የጊናአገር-ሰጦን -መተህብላ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በአብዛኛዉ ሞቃታማ የአየር ፀባይ ባለበት አካባቢ የሚከናወን እና ከፍተኛ የቆረጣ ሥራ የሚጠይቅ አስቸጋሪ መልዕክዓ-ምድር ካላቸዉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን ፕሮጀክቱ በተያዘዉ በጀት አመት ከክልሉ መንግስት በተመደበ ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት 5 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ እስከ መጋቢት አጋማሽ/2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ የቅየሳ ሥራ 5ኪ.ሜ፣የምንጣሮና ጠረጋ ሥራ 4.8 ኪ.ሜ፣ የአፈር ድልዳሎ ሥራ 4.6 ኪ.ሜ በመፈፀም በአማካይ ሥራ 1.63 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ አከናዉኗል፡፡
የጊናአገር-ሰጦን -መተህብላ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የበጀት አመቱን ዕቅድ ለመፈፀም ጥረት በማድረግ ላይ የነበረ ፕሮጀክት ሲሆን በዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ደረጃ በተፈጠረዉ የነዳጅ እጥረት ምክንያት ከመጋቢት 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ የግንባታ ሥራዉ እንደቆመ ከፕሮጀክቱ ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል፡፡
የጊናአገር-ሰጦን-መተህብላ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በሰሜን ሸዋ ዞን የአሳግርት ወረዳን ከበረኸት ወረዳ ጋር በማገናኘት የአካባቢዉ ህብረተሰብ የመንገድ ትራንስፖርት ችግር የሚፈታ እና በአካባቢዉ በመስኖ ልማት የሚለሙ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ሌሎች እንደ ማሾ እና ጤፍ የመሳሰሉ ምርቶች በስፋት በሚመረቱበት አካባቢ የሚገነባ መንገድ በመሆኑ ህብረተሰቡ በአካባቢዉ ለሚያከናዉነዉ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች/ግብአቶች ዝዉዉር በማቀላጠፍ ረገድ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለዉ መንገድ ነዉ፡፡ ከአጎራባች የአፋር ክልል ነዋሪዎች ጋር ያለዉ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር በማድረግ ረገድም ትልቅ ጠቀሜታ ይሰጣል፡፡

በዋግኸምራ  ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ ወረዳ በኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ስራ ኘሮጀክት የሚከናወነው የፃና ወንዝ ድልድይ (ቁጥር-2) ግንባታ 86% ተጠናቀቀ፡፡በክልሉ ዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ...
02/04/2026

በዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ ወረዳ በኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ስራ ኘሮጀክት የሚከናወነው የፃና ወንዝ ድልድይ (ቁጥር-2) ግንባታ 86% ተጠናቀቀ፡፡
በክልሉ ዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ ወረዳ በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ስራ ኘሮጀክት እየተገነባ ያለው እና 40 ሜትር ርዝመት ያለው የፃና ወንዝ ድልድይ (ቁጥር-2) 65% የሚሆነው የድልድዩ ግንባታ ባለፈው ዓመት የተከናወነ ሲሆን በተያዘው በጀት ዓመት 35% የሚሆነውን የድልድዩን ግንባታ በማከናወን ድልድዩን ለማጠናቀቅ በተያዘው እቅድ መሰረት እስከ መጋቢት 22/2018 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ የድልድዩ የአርማታ ሙሌት ስራ ተከናውኖ አጠቃላይ የድልድዩ ግንባታ 86% ተጠናቋል፡፡
በዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ ወረዳ የሚገነባው እና 63.26 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ስራ ኘሮጀክት በ2008 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን የጠቅላላ ርዝመቱ 58% የሚሆነው የመንገዱ ግንባታ ስራ ተከናዉኗል፡፡
የኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ለህብረተሰቡ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለስትራክቸር ግንባታ ትኩረት በመስጠት የተለያዬ መጠን ያላቸው አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ በመከናወን ላይ ሲሆን ሞቃታማውን የአካባቢው የአየር ፀባይ በመቋቋም እየተገነባ ያለዉ የፃና ወንዝ ድልድይ (ቁጥር-2) ግንባታም የዚሁ አካል ነው፡፡
በበጀት ዓመቱ ለሚከናወነው የፃና ወንዝ(ቁጥር-2) ግንባታ ከክልሉ መንግስት ብር 13,424,038.00 /አስራ ሶስት ሚሊዮን አራት መቶ ሃያ አራት ሽህ ሰላሳ ስምንት ብር/ በጀት የተመደበ ሲሆን በቀሪ ጊዜያት የድልድዩን ግንባታ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል፡፡
የኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ግንባታ በክልሉ ዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ ወረዳ የሚገኙ 8 ቀበሌዎችን ርዕስ በርስ እና ከሰቆጣ -ኒሯቅ-መቀሌ ከሚወስደው ዋና መንገድ ጋር በማገናኘት የአካባቢውን ህብረተሰብ የመንገድ ተደራሽነት ችግር በመፍታት ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡ መንገዱ በአካባቢዉ በመስኖ የሚመረቱ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች በወቅቱ ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የተለያዩ የትምህርት፣ የጤናና የግብርና ግብአቶችን ወደ አካባቢው ለማድረስ እንዲሁም ከአጐራባች የትግራይ ክልል ነዋሪዎች ጋር ያለው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጠናከር በማድረግ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና አስተዳደራዊ ፋይዳ ያለው መንገድ ነው፡፡
በክልሉ ዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን አበርገሌ ወረዳ ከኒሯቅ-ሴሪያ መንገድ ግንባታ በተጨማሪ ከክልሉ መንግስት በሚመደብ በጀት የአካባቢዉን ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግ 31 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የኒሯቅ -ሲቃላ-ተከዜ መንገድ ግንባታም እየተከናወነ ይገኛል፡፡

የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት  የጠቅላላ ርዝመቱ 57%(ፐርሰንት)   የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፤ በበጀት ዓመቱ የተለያዬ መጠን ያላቸዉ ስትራክቸሮች ግንባታም እየተከናወነ ...
30/03/2026

የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የጠቅላላ ርዝመቱ 57%(ፐርሰንት) የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፤ በበጀት ዓመቱ የተለያዬ መጠን ያላቸዉ ስትራክቸሮች ግንባታም እየተከናወነ ነዉ፡፡
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በተያዘዉ በጀት ዓመት ለአነስተኛ፣መካከለኛ እና ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም ለቱቦ ቀበራ ሥራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት የስትራክቸር ግንባታ ከሚከናወንባቸዉ ፕሮጀቶች መካከል በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የሚገኘዉ እና 52 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አንዱ ነዉ፡፡
የመካነብርሃን -ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በ2012 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ ግንባታ የጠቅላላ ርዝመቱ 57.8% የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፡፡ፕሮጀክቱ በተያዘዉ በጀት ዓመት ከክልሉ መንግስት በተመደበ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት ከ4 እስከ 15 ሜትር ርዝመት ያላቸዉ 3/ሦሥት/ አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም የቱቦ ቀበራ ሥራዎችን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ መጋቢት አጋማሽ 2018 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ የግንባታ ሥራ የአንድ አነስተኛ ድልድይ ግንባታ ተጠናቋል፡፡ የ2 /ሁለት/ አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ ደግሞ የግንባታቸዉ 65% እና 20% ተከናዉኗል፡፡በ4/አራት/ ቦታዎች የሚከናወን የቱቦ ቀበራ ሥራም ተጠናቋል፡፡
የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በክልሉ በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የሚገኙ እና በመንገድ ያልተገናኙ 7/ሰባት/ ቀበሌዎችን ርዕስ በርስ እና ከዋና መንገድ ጋር በማገናኘት የአካባቢዉን ህብረተሰብ የሚያጋጥሙ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮች እንዲፈቱ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡

የማጀቴ- ወጀድ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት  40ሜትር ርዝመት ያለዉ የአመዴበሽር  ወንዝ ድልድይ ግንባታ እያከናወነ ነዉ፡፡በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን 25 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የማጀቴ -ወጀድ መንገድ ...
28/03/2026

የማጀቴ- ወጀድ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት 40ሜትር ርዝመት ያለዉ የአመዴበሽር ወንዝ ድልድይ ግንባታ እያከናወነ ነዉ፡፡
በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን 25 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የማጀቴ -ወጀድ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በ2013 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን በተያዘዉ በጀት ዓመት ፕሮጀክቱ 40 ሜትር ርዝመት ያለዉ የአመዴ በሽር ወንዝ ድልድይ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል፡፡
የአመዴበሽር ወንዝ ድልድይ ግንባታ ከክልሉ መንግስት በተመደበ ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት እየተከናወነ ሲሆን እስከ መጋቢት አጋማሽ 2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ የድልድዩ ግንባታ 47.5% የሚሆነዉ ተከናዉኗል፡፡የድልድዩ ግንባታ በአሁኑ ወቅት የተለያዬ መጠን ያለዉ የአርማታ ብረት አቅርቦት የሚፈልግ ሲሆን የድልድዩን ግንባታ በተያዘዉ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል፡፡
የማጀቴ- ወጀድ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በሰሜን ሸዋ ዞን የኤፍራታናግድም ወረዳን ከመንዝጌራ ወረዳ ጋር በማገናኘት የአካባቢዉን ህብረተሰብ የመንገድ ትራንስፖርት ችግር የሚፈታ ከመሆኑም በላይ በአካባቢዉ ለሚከናወን የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የባህር ዛፍ ደን ልማት የገበያ ዕድል ይፈጥራል፤ የተለያዩ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ግብአቶች/ምርቶች ዝዉዉር እንዲሳለጥ በማድረግ ረገድም ትልቅ ጠቀሜታ ይሰጣል፡፡

የአምባጊዮርጊስ-መረባ-ሳንጃ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ 60%(ፐርሰንት) አከናወነ፡፡የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በበጀት ዓመቱ የግንባታ ሥራ ከሚያከናዉንባቸ...
27/03/2026

የአምባጊዮርጊስ-መረባ-ሳንጃ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ 60%(ፐርሰንት) አከናወነ፡፡
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በበጀት ዓመቱ የግንባታ ሥራ ከሚያከናዉንባቸዉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነዉ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የወገራ ወረዳን ከታች አርማጭሆ ወረዳ የሚያገናኘዉ የአምባጊዮርጊስ-መረባ-ሳንጃ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት 74.5 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ እና በ2013 ዓ.ም የተጀመረ ፕሮጀክት ነዉ፡፡
ፕሮጀክቱ በ2018 በጀት ዓመት 4 ኪ.ሜ መንገድ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ እስከ መጋቢት አጋማሽ 2018 ዓ.ም ባለዉ ጊዜ የቅየሳ ሥራ 4ኪ.ሜ፣የምንጣሮ እና ጠረጋ ሥራ 4ኪ.ሜ፣የአፈር ድልዳሎ ሥራ 4 ኪ.ሜ፣ በአጠቃላይ በአማካይ ሥራ 2.4 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ በማከናወን የበጀት ዓመቱን ዕቅድ 60% መፈፀም ችሏል፡፡ በ10/አስር/ ቦታዎች የቱቦ ቀበራ ሥራዎችም ተከናዉነዋል፡፡
በፕሮጀክቱ እንደ ሲሚንቶ እና ነዳጅ የመሳሰሉ የግንባታ ግብዓቶች እጥረት በሥራ ላይ ጫና እያሳደሩ ቢሆንም በፈተና ዉስጥ ሆኖ በመሥራት ዕቅዱን ለማሳካት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የአምባጊዮርጊስ-መረባ-ሳንጃ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት ከጎንደር-አምባጊዮርጊስ-ደባርቅ-አዲአርቃይ እና ከጎንደር-ሳንጃ-ሰሮቃ-ዳንሻ-ሁመራ ከሚወስዱ የአስፋልት መንገዶች እንዲሁም ከማሰሮደንብ-አብርሃጅራ ከሚወስደዉ የጠጠር መንገድ ጋር የሚተሳሰር በመሆኑ የህብረተሰቡን የመንገድ ተደራሽነት ችግር የሚፈታ ከመሆኑም በላይ የአካባቢዉ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ በማድረግ ረገድ ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ሴት ሰራተኞች የሴቶች ማህበር በቀጣይ ወራት በሚያከናውናቸው ተግባራት እቅድ ላይ በመወያየት አፀደቁ።የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ...
25/03/2026

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ሴት ሰራተኞች የሴቶች ማህበር በቀጣይ ወራት በሚያከናውናቸው ተግባራት እቅድ ላይ በመወያየት አፀደቁ።
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ሴት ሰራተኞች የአማራ ሴቶች ማህበር አባል ሲሆኑ በበጀት አመቱ ቀጣይ ወራት የሚያከናውኗቸውን ተግባራት የተመለከተ እቅድ በማዘጋጀት ከአባላት ጋር በመወያየት እቅዱን አፅድቀዋል።
የእቅድ ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቀለሙ ሙሉነህ ተደራጅቶ መንቀሳቀስ ሚናን በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ስለሆነ መደራጀት አቅም መሆኑን ገልፀው ማህበሩ ተደራጅቶ የሴቶችንና የተቋሙን ችግር የሚፈታና የሴቶችን ተነሳሽነት የሚጨምር ውጤታማ የሚያደርግ ጠንካራ ማህበር እንጅ ማህበር ተደራጅቷል ለማለትና ለስም ብቻ የተደራጀ ሊሆን እንደማይገባ አስገንዝበዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አያይዘውም ለወደፊቱ የማህበሩ እቅድ የተቋሙ የፊዚካል ስራ እቅድ ሲቀርብ አብሮ ቀርቦ ከተቋም ስራ ጋር ተመጋጋቢ ሆኖ እንዲፈፀም ማድረግ የሚገባ መሆኑንና እንደተቋም ማህበሩን ለማጠናከር የሚጠበቀውን ሁሉ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
የተቋሙን የሴቶች ማህበር እቅድ ያቀረቡት የማህበሩ ሊቀመንበር ወ/ሮ አበባየ አምላኩ እቅዱን በዝርዝር ለማህበሩ አባላት ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው እቅድ ላይ ሰፊ ውይይት በማካሄድ እቅዱን ለያዳብሩ የሚችሉና ማህበሩ የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያግዙ አስተያየቶች ተሰጥው በአባላት ሙሉ ድምፅ እቅዱ ፀድቋል።
በእቅዱ ላይ ውይይት ሲካሄድ የክልሉን ሴቶች ማህበር በመወከል የተገኙት የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሮ መሰረት ሞላ በበኩላቸው መደራጀት ተሰሚነት እንዲኖር ለማድረግ፣ ጫና በመፍጠር መብትን ለማስከበር፣ ልምድ ለመለዋወጥ እንዲሁም ከሀገር ሀብት እኩል ተጠቃሚ ለመሆን ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው የተቋሙ ሴቶች በዚህ መልክ መደራጀት ጥሩ መሆኑን አንስተዋል።
የገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ሴት ሰራተኞች በህዳር ወር 2018 ዓ.ም በክልሉ ሴቶች ማህበር አማካኝነት በማህበር መደራጀት ስላለው ጠቀሜታና አስፈላጊነት በተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት የማህበሩ አባል ለመሆን ስምምነት ላይ በመደረሱ ማህበሩ የተመሰረተ መሆኑ ይታወሳል።

Address

Ethiopia , Amhara
Bahir Dar

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
18:00 - 19:00
Tuesday 09:00 - 17:00
18:00 - 19:00
Wednesday 09:00 - 17:00
18:00 - 19:00
Thursday 09:00 - 17:00
18:00 - 19:00
Friday 09:00 - 17:00
18:00 - 19:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251582201711

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Rural Roads Construction Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Rural Roads Construction Agency:

Share