ANRS Ethics and Anti Corruption Commission

ANRS Ethics and Anti  Corruption Commission የአማራ ክልል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ማለት ሥነ

በሥነ ምግባር እና በእዉቀት የዳበረ ትዉልድ ለመቅረፅ የትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነዉ።🌿🌿🌿🌿🌿🌿በአመለካከትና በእውቀት የዳበረ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸ እና ለሀገር ተቆርቋሪ ትውልድ መቅረ...
03/06/2026

በሥነ ምግባር እና በእዉቀት የዳበረ ትዉልድ ለመቅረፅ የትምህርት ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነዉ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿

በአመለካከትና በእውቀት የዳበረ፣ በሥነ-ምግባር የታነጸ እና ለሀገር ተቆርቋሪ ትውልድ መቅረፅ የአንድ ሀገር የረጅም ጊዜ ህልውና እና እድገት መሰረት ነው። ለዚህ ደግሞ የትምህርት ተቋማት (ከመዋለ ህፃናት እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) ግንባር ቀደም እና የማይተካ ሚና አላቸው።

ትምህርት በፈተና ውጤት እና በዕውቅና ላይ ብቻ ያተኮረ መሆን የለበትም። ተማሪዎች ያገኙትን እውቀት በዕለት ተዕለት ህይወታቸው ወደ ተግባርና ወደ ፈጠራ የሚቀይሩበት የክህሎት ማእከል መሆን አለበት።

በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናቶችና ምርምሮች የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ እና የሀገርን የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ ሽግግር የሚያፋጥኑ መሆን ይኖርባቸዋል።

ከሙስና፣ ከሌብነት፣ ከኮፒራይት እና ከሌሎች የሞራል ዝቅጠቶች የጸዳ ትውልድ ለመገንባት፣ የትምህርት ተቋማት የንቅናቄ ማእከል መሆን አለባቸው። ተማሪዎች ልዩነቶችን በውይይትና በሰላማዊ መንገድ የሚያስተናግዱበት፣ የሀገር ፍቅር ስሜት የሚገነባበት እና ለሕግ የበላይነት የሚገዙበት የዜግነት ትምህርት በተግባር መተግበር ይኖርበታል ማለት ነዉ።

መምህራንም እውቀት አስተላላፊ ብቻ ሳይሆኑ በአመለካከት፣ በሥነ-ምግባር እና በአሰራር ለተማሪዎቻቸው አርአያ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

መምህራን በዘመናዊ የማስተማር ስነ-ዘዴ እና በቴክኖሎጂ እንዲበለጽጉ ተከታታይ ስልጠናዎች ሊሰጧቸው ይገባል። ቴክኖሎጂን ለፈጠራ፣ ለእውቀት ፍለጋና ለበጎ ስራ እንጂ ለአሉታዊ ተፅእኖዎች፣ ለሀሰተኛ መረጃዎችና ለሳይበር ወንጀሎች እንዳይጠቀሙበት ሥነ-ምግባራዊ ግንዛቤ መፍጠር ያስፈልጋል።

በአጠቃላይ ትውልድን መቅረፅ ሀገርን መስራት ነው። በአመለካከቱ የቀና፣ በዕውቀቱ የላቀ፣ በጥበብና በቴክኖሎጂ የዳበረ ትውልድ ማፍራት ከተቻለ፣ የሀገርን የዴሞክራሲ፣ የፍትህ እና የብልጽግና ጉዞ አስተማማኝ ማድረግ ይቻላል ማለት ነዉ።

ሙስና የሀገር ሁለንተናዊ እድገት ማነቆ ነዉ!🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿ሙስና የአንድን ሀገር ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መሰረት በመናድ የዜጎችን ሁለንተናዊ እድገት የሚያደናቅፍ ዋና ማነቆ ነው። ሀገ...
03/06/2026

ሙስና የሀገር ሁለንተናዊ እድገት ማነቆ ነዉ!
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ሙስና የአንድን ሀገር ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መሰረት በመናድ የዜጎችን ሁለንተናዊ እድገት የሚያደናቅፍ ዋና ማነቆ ነው። ሀገርን እንደ ምስጥ ከውስጥ እየበላ የሚያደክም አደገኛ ወረርሽኝ ነው።

ለልማት፣ ለትምህርት እና ለጤና መዋል የነበረበት የህዝብና የሀገር ሀብት በጥቂት ግለሰቦች እጅ እንዲገባ ያደርጋል። በችሎታና በታማኝነት መስራት የሚፈልጉ ባለሀብቶችንና ወጣቶችን ተስፋ ያስቆርጣል ማለት ነዉ።

ድሆች እና አቅም የሌላቸው ዜጎች መሰረታዊ መብቶቻቸውን እና አገልግሎቶችን እንዲያጡ ያደርጋል። በትጋት ከመስራት ይልቅ በ"እጅ መንሻ" እና በ"ብልጣብልጥነት" መክበርን እንደ አማራጭ እንዲወሰድ በማድረግ የትውልዱን ሥነ-ምግባር ያበላሻል።

ይህንን የሀገር ወረርሽኝ ለመከላከል የመንግስት ቁርጠኝነት ብቻ ሳይሆን፣ የእያንዳንዱ ዜጋ የሥነ-ምግባር እሴት መገንባት እና "እኔ ለሙስና አልተባባሪም" የሚል ጠንካራ የጋራ አቋም መያዝ ወሳኝ ነው።

02/06/2026
02/06/2026

(ግንቦት 25/2018 ዓ.ም፤ የአብክመ ሥ.ፀ.ሙ.ደ.ቅ)፦ የአማራ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የደሴ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት፣ በደሴ ከተማ የቤቶች ልማት አመራርና ባለሙያዎችን የሀብት ምዝገባ ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

ከሰላም የሚበልጥ ምንም ዓይነት የድል አክሊል የለም!🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿ክፋትን በክፋት፣ ጥላቻን በጥላቻ ለማሸነፍ መሞከር እሳትን በእሳት እንደማጥፋት ይቆጠራል። ነገር ግን መልካምነት፣ ታማኝነት፣ እ...
02/06/2026

ከሰላም የሚበልጥ ምንም ዓይነት የድል አክሊል የለም!
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ክፋትን በክፋት፣ ጥላቻን በጥላቻ ለማሸነፍ መሞከር እሳትን በእሳት እንደማጥፋት ይቆጠራል። ነገር ግን መልካምነት፣ ታማኝነት፣ እና በጎ ሥነ ምግባር ማንኛውንም ከባድ ፈተና እና ግጭት በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ታላቅ ኃይል አላቸው።

በጎ ሥነ ምግባር ያለው ሰው በሄደበት ሁሉ አመኔታን ያተርፋል። እውነተኛ ሰላም ደግሞ የሚመጣው በመተማመን ላይ ነው።

ከውጭ ለሚመጣብን አሉታዊ ተጽዕኖ በምላሹ ክፋትን ሳናፀባርቅ በበጎ ሥነ ምግባር ስንመላለስ፣ ህሌናችን ሁልጊዜም በሰላም ይሞላል። በጎ ሥነ ምግባር ልክ እንደ ብርሃን ነው፤ ጨለማን በራሱ ጊዜ እንዲጠፋ እንደሚያደርገው ሁሉ፣ መልካም ባህሪም በዙሪያችን ያሉትን ሰዎችና ማኅበረሰብ በበጎ ተጽዕኖ ይለውጣል ማለት ነዉ።

ከሰላም የሚበልጥ ምንም ዓይነት የድል አክሊል የለም፤ እውነተኛ ሰላም ደግሞ የሚገነባው በዕለታዊ በጎ ሥነ ምግባራችን እና ለሌሎች በሚኖረን ክብር ነው፡፡

ሥነ ምግባር የሁሉ ነገር መሰረት ነዉ።🌿🌿🌿🌿🌿🌿ማንኛውም እውቀት፣ ስልጣን፣ ሃብት ወይም የቴክኖሎጂ እድገት ያለ በጎ ሥነ ምግባርና ያለ ታማኝነት ከተገነባ ዘላቂ ሊሆን አይችልም። እንደውም ያ...
02/06/2026

ሥነ ምግባር የሁሉ ነገር መሰረት ነዉ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ማንኛውም እውቀት፣ ስልጣን፣ ሃብት ወይም የቴክኖሎጂ እድገት ያለ በጎ ሥነ ምግባርና ያለ ታማኝነት ከተገነባ ዘላቂ ሊሆን አይችልም። እንደውም ያለ ሥነ ምግባር የሚገነባ ስልጣኔ ፍጻሜው ጥፋት ነው።

ሥነ ምግባር መሰረት የሚሆንባቸዉ ቁልፍ ነገሮች፦
✍️ለእውነተኛ ልማትና እድገት፦ ሙስና እና አድልዎ ሳይኖር፣ አሰራሮች በግልጽነትና በተጠያቂነት ሲመሩ የሕዝብ ተጠቃሚነት ይረጋገጣል።

✍️ለፍትህና እኩልነት፦ የሕግ የበላይነትና የሰብአዊ መብቶች የሚከበሩት በግል ጥቅም የማይደለል፣ ቀጥተኛና እውነተኛ ማህበረሰብ ሲኖር ነው።

✍️ለቀጣዩ ትውልድ፦ ሀገርን የሚረከበው ወጣት ትውልድ በትጋት፣ በሀቀኝነት እና በሀገር ፍቅር ስሜት እንዲያድግ ትልቁን ድርሻ ይይዛል።

ይህንን ታላቅ እሴት በተግባር ማዋል፣ ማስተማር እና ማጠናከር የሁላችንም የዕለት ተዕለት ኃላፊነት ነው።

ትዉልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

መልካም ሰራተኛ የተቋም "አምባሳደር" ነው።🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿አንድ መልካም፣ ታማኝ እና ስራውን በቅንነት የሚያከናውን ሰራተኛ የተቋሙ የጀርባ አጥንት ከመሆኑም በላይ ተሻግሮ የተቋሙ ገፅታ እና መስተ...
31/05/2026

መልካም ሰራተኛ የተቋም "አምባሳደር" ነው።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

አንድ መልካም፣ ታማኝ እና ስራውን በቅንነት የሚያከናውን ሰራተኛ የተቋሙ የጀርባ አጥንት ከመሆኑም በላይ ተሻግሮ የተቋሙ ገፅታ እና መስተዋት (አምባሳደር) ነው።

ተቋሙ በወረቀት ላይ የሰፈሩትን እንደ ታማኝነት፣ ግልፅነት፣ እና ጥራት ያሉ መልካም እሴቶች ወደ መሬት አውርዶ በተግባር ለህዝብና ለተገልጋይ የሚያሳየው በሰራተኛው መልካም ባህሪ እና የስራ ተነሳሽነት ነው።

ተገልጋዮች ስለ አንድ ተቋም ያላቸው አመለካከት የሚወሰነው በቀጥታ ከሚያገኟቸው ሰራተኞች በሚያገኙት መስተንግዶ ነው። መልካም ሰራተኛ የህዝብን አመኔታና ክብር ያተርፋል።

እንዲህ አይነቱ ሰራተኛ ከተቋሙ ውጭም ቢሆን በባህሪው፣ በሥነ-ምግባሩ እና ለስራው ባለው ታማኝነት የተቋሙን ስም ከፍ ያደርጋል፤ ለሌሎችም አርአያ ይሆናል።

በአጭሩ "መልካም ሰራተኛ የስራ ቦታውን ክብርና ስም በሁሉም ቦታ የሚወክል ህያው አምባሳደር ነው!"

በምርጫ ሥነ-ምግባር መመራት የዲሞክራሲያዊ ስልጣኔ ማረጋገጫ ነዉ።🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿በምርጫ ሥነ-ምግባር መመራት የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን ስኬታማነትና የሕዝብን የሥልጣን ባለቤትነት የሚያረጋግጥ...
29/05/2026

በምርጫ ሥነ-ምግባር መመራት የዲሞክራሲያዊ ስልጣኔ ማረጋገጫ ነዉ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

በምርጫ ሥነ-ምግባር መመራት የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን ስኬታማነትና የሕዝብን የሥልጣን ባለቤትነት የሚያረጋግጥ ዋነኛ መሠረት ነው። ይህ ሐሳብ ለአንድ ሀገር የፖለቲካ ብስለትና ማኅበራዊ ዕድገት እጅግ ወሳኝ የሆኑ በርካታ እውነታዎችን ያካትታል።

አንድ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ግልጽና በሕግና በሥነ-ምግባር የሚመራ ሲሆን፣ ሕዝቡ በምርጫው ሂደትና በውጤቱ ላይ ያለው እምነት ይጨምራል። ድምፁ ዋጋ እንዳለው የሚያምን ዜጋ ደግሞ በነፃነትና በንቃት በዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ውስጥ ይሳተፋል።

ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲም ሆነ ዕጩ ተወዳዳሪ በሥነ-ምግባር ደንቦች ሲገዛ፣ ውጤትን በፀጋ የመቀበልና የሕዝብን ውሳኔ የማክበር ባሕል ይዳብራል። ይህ ደግሞ ምርጫን ተከትሎ ሊመጡ የሚችሉ ግጭቶችንና አለመረጋጋቶችን በማስቀረት፣ ሀገርን ወደ አስተማማኝ ሰላምና ልማት ይመራታል።

የምርጫ ሥነ-ምግባር የሌሎችን መብት ማክበርን፣ ከጥላቻ ንግግር መቆጠብንና ሕግ መከተልን ያጠቃልላል። ይህ ሲሆን ተፎካካሪዎች እርስ በርስ ከመጠቃቀስ ይልቅ በአማራጭ ሐሳቦችና ፖሊሲዎች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲከራከሩም ያደርጋቸዋል።

የተረጋጋና ሥነ-ምግባራዊ ምርጫ የሚያካሂዱ ሀገራት በዓለም አቀፍ መድረክ ያላቸው አመኔታና ክብር ከፍ ይላል። ይህ የዲሞክራሲያዊ ስልጣኔ መገለጫ በመሆኑ የውጭ ኢንቨስትመንትንና የዲፕሎማሲ ግንኙነትን ያጠናክራል።

በአጠቃላይ ምርጫ በቁጥር መብለጥ ብቻ ሳይሆን፣ ሂደቱ በምን ያህል የሞራልና የሕግ ልዕልና ተከናውኖ የሕዝብን እውነተኛ ፍላጎት አሳካ የሚለው ነው "ስልጣኔን" የሚለካው። ሥነ-ምግባር የሌለው ምርጫ ቅርጹ ዲሞክራሲ ቢመስልም፣ ይዘቱ ግን ባዶና ለትርምስ የሚጋብዝ ይሆናል።

በ2018 በጀት ዓመት በተከናወኑ የመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከኮሚሽኑ ሰራተኞች ጋር ዉይይት ተካሄደ።🌿🌿🌿🌿🌿🌿ግንቦት 21/2018 ዓ.ም/ አብክመ ሥ.ፀ.ሙ.ኮ/ የአብክመ የሥነ ምግባርና የፀረ...
29/05/2026

በ2018 በጀት ዓመት በተከናወኑ የመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከኮሚሽኑ ሰራተኞች ጋር ዉይይት ተካሄደ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ግንቦት 21/2018 ዓ.ም/ አብክመ ሥ.ፀ.ሙ.ኮ/ የአብክመ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት በተከናወኑ የመልካም አስተዳደር ተግባራት ዙሪያ የኮሚሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ዉይይት ተካሄደ።

በበጀት አመቱ ኮሚሽኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ግልጽነትና ጠያቂነት ያለዉ አገልግሎት ለማስፈን፣ የአሠራር ሥርዓቶችን ለማስተካከል፣ በእውቀትና በችሎታ ላይ የተመሠረተ የሰው ኃይል ለማሟላትና የሰራተኞችን ጥቅማጥቅም ለማስከበር በርካታ ስራዎች እንደተሰሩ ተገልጿል።

እንደኮሚሽንም ያጋጠሙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍም በተያዘዉ የአጭር፣ የመካከለኛ እና የእረዥም ጊዜ እቅድ ተፈፃሚ መሆናቸዉ ተመላክቷል።

የኮሚሽኑ ምክ/ኮሚሽነር ማሩ ቸኮል በመድረኩ በመገኘት ንግግር ያደረጉ ሲሆን አንድ ተቋም የተጣለበትን ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነት በብቃት መወጣት የሚችለው ጠንካራና ግልጽነት የሰፈነበት መልካም አስተዳደር ሲገነባ ነው ብለዋል።

ሁሉም በተሰማራበት የሥራ መስክ የሙያ ሥነ ምግባርን በማክበር፣ ለሕዝብ ታማኝ በመሆን እና የአገልግሎት አሰጣጣችንን በማዘመን በትኩረት ከሰራን ለመልካም አስተዳደር መስፈን ትልቅ አስተዋጾኦ እናበረክታለን ብለዋል።

አክለዉም ምክ/ኮሚሽነሩ የእያንዳንዳችን ታማኝነት፣ ታታሪነትና ለፍትሃዊነት የምናሳየዉ ቁርጠኝነት የተቋማችን ገጽታ የሚገነባ ትልቁ አቅማችን በመሆኑ ለላቀ ለውጥና ለህዝብ እርካታ በጋራ በርትተን ልንሰራ ይገባል በማለት መልክታቸዉን አስተላልፈዋል።

"ትዉልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!"

//ተጨማሪ የኮሚሽኑን መረጃ ለማግኘት ሊንኩን ANRS Ethics and Anti Corruption Commissionissionanrseac
??ቴሌግራም_ https://t.me/Anrs_Ethics_Anti_Corruption_comm
??ዋትስ አፕ_ https://chat.whatsapp.com/Bo9Co45id7XKF8E5WsuI5h
??ዩትዩብ_ https://www.youtube.com/
👉ቲክቶክ_https://vm.tiktok.com/ZMrQ9aESA/

Address

Bahir Dar
1796

Opening Hours

Tuesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Ethics and Anti Corruption Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share