Amhara RoadTransport and Logistics Bureau

Amhara RoadTransport and Logistics Bureau ፕሮጀክት ላንጨረስ አንጀምርም !!

የደቡብ ወሎዞን  መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ከ839 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ፤******የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መም...
19/08/2026

የደቡብ ወሎዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ከ839 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ፤
******
የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ባቀረበው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጥሪ መሠረት፣ የአሽከርካሪ ማህበራትና የተሽከርካሪ ተቋማት ከ839 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርገዋል።

በዞኑ የሚገኙ ሰባት የትራንስፖርት ማህበራት ድጋፉን ማበራከታቸውን የገለጹት የለጎ ሐይቅ ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ ሕዝብ ማመላለሻ ባለሃብቶች ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ አስመሮው ባይህ፤ ለወላጅ አልባዎችና አቅም ለሌላቸው ወገኖች ድጋፍ ማድረግ በመቻላቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

አክለውም ማህበራቸው ከ600 ደርዘን በላይ ደብተርና እስክሪብቶ ማበርከቱን ገልጸው፣ ይህ ዓይነቱ የበጎ አድራጎት ተግባር በሁሉም ዘንድ ሊቀጥል እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

በተመሳሳይ የደሴ ከተማ የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋም ሰብሳቢ አቶ በዙነህ ሀይሌባህሩ በበኩላቸው፤ በማህበሩ ሥር የሚገኙ 10 ባለሃብቶች 100 ደርዘን ደብተርና 100 ደርዘን እስክሪብቶ ማበርከታቸውን ገልጸዋል።

የዘንድሮው ድጋፍ ከቀደሙት ዓመታት በይዘቱና በመጠኑ የተሻለ መሆኑን ጠቁመው፣ የትምህርት ቁሳቁስ መግዛት ለማይችሉ ወገኖች እጅ መዘርጋት የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አሰን፤ በተደረገው እንቅስቃሴ ከ600 ደርዘን በላይ ደብተርና ከ245 ባኮ በላይ እስክሪብቶ መሰብሰቡን አብራርተዋል።

የተሰበሰበው ቁሳቁስ በዞኑ አብይ ኮሚቴ አማካኝነት እስከ ወረዳ ድረስ ላሉ አቅመ-ደካሞችና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወገኖች ልጆች እንደሚሰራጭ ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም፣ አሽከርካሪዎችና ተቋማት ባሉባቸው ችግሮችና ውጣ ውረዶች ውስጥ ሆነው ላደረጉት ወገናዊ ደጋፍና ለላቁት በጎ አድራጎት በመምሪያው ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

መረጃው የደቡብ ወሎዞን መንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ነው።

አዲሱን የደብረታቦር ከተማ መናኸሪያ ለማስጀመር የቅድመ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተኻሄደ።***በደቡብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጄስቲክስ መምሪያ የተጀመረው አዲሱ የደብረታቦ...
19/08/2026

አዲሱን የደብረታቦር ከተማ መናኸሪያ ለማስጀመር የቅድመ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተኻሄደ።
***
በደቡብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጄስቲክስ መምሪያ የተጀመረው አዲሱ የደብረታቦር ከተማ መናኸሪያ ስራ ለናስጀመር የቅድመ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሂዷል።

መናኸሪያዎች በክልል፣ በዋና ዋና ከተሞችና በዙሪያቸው ባሉ አካባቢዎች መካከል የሕዝብና የዕቃ ትራንስፖርት እንቅስቃሴን በሚገባ ለማስተባበርና ለማቀላጠፍ የተደራጁ የህዝብ ማዕከላት ናቸው።

የደቡብ ጎንደር ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጄስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳግም ጥሩነህ በአዲስ የሚገነቡ መናኸሪያዎች ደረጃቸውን ጠብቀው ስለሚገነቡ የትራንስፖርት አስራሩን ግልፅ በማድረግ ተገልጋዩን ማህበረሰብ ከህገ-ወጥ ደላሎች ይገላግላል ብለዋል።

ዘመናዊ የመናኸሪያ አገልግሎት የተሳፋሪዎችን እንግልት ይቀንሳል፣ የመንግስትንና የአካባቢውን ማህበረሰብ ገቢ ያሳድጋል ያሉት አቶ ዳግም ከደብረታቦር ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አመራሮች ጋር በመተባበር ለቅድመ አገልግሎት ማስጀመር የበቃው ይህ መነኸሪያ በዕድገት ጉዞ ላይ ለሚገኘው የደብረታቦር ከተማ ገፅታ ሰፊ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል።

ቴክኖሎጅ የወለዳቸውን አገልግሎቶች ለመሰጠት ዘመናዊ መናኸሪያ የለንም ነበረ ያሉት አቶ ዳግም አሁን ግን ከደብረታቦር ከተማ አስተዳደር በተረከብነው 13ሽህ 1መቶ95 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ዘመናዊ መናኸሪያ በመገንባት ለቅድመ አገልግሎት ማስጀመሪያ በመብቃታቸው የከተማ አስተዳደሩን አመስግነዋል።

በቀጣይ ክልሉ ከፍተኛ በጀት መድቦ በመገንባት ዘመኑን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት እንዲያስችል የሁለቱም ዞኖች አስተባባሪ አመራሮች የጀመሩትን ጥያቄ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አቶ ዳግም ጠቁመዋል።

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ከንቲቫ አቶ ደሴ መኮንን አዲሱ መናኸሪያ የክልሉ መንግስት በሌሎች አቻ ከተሞች ያስገነባውን ዓይነት ዘመናዊ መናኸሪያ ለደብረታቦር እና ለዙሪያው ማህበረሰብ እንዲገነባ ላቀረብናቸው ተደጋጋሚ ጥያቄዎች የተሰጠ መልስ ነው ብለዋል።

የዛሬውን የቅድመ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ለፍፃሜ ለማብቃት ሁለቱም አስተዳደሮች በቅርበትና በትኩረት ይዘን እንሰራለን ብለዋል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ደጀኔ ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት የሰለጠኑ ህዝቦች መገለጫና የኢኮኖሚ እንብርት መሆኑን ገልፀው ዛሬ ያስጀመርነው የመናኸሪያ የቅድመ አገልግሎት መንግስት ለሚፈታቸው የህዝብ ጥያቄዎች ማሳያ ነው ብለዋል።

አዲሱ መናኸሪያ ለደብረታቦር ከተማ፣ ለደቡብ ጎንደር እና ለአጎራባች ዞኖች ትልቅ ሀብት ነው ያሉት አቶ ጥላሁን የቀጠናው ማህበረሰብ ነፃ የሆነ እንቅስቃሴ ለማድረግ የሚያስችል በዓይነቱ ልዩ የሆነ መናኸሪያ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም መናኸሪያው ሁሉን አቀፍ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ደረጃ ማድረስ የክልሉ መንግስት ኃላፊነት ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በቀጣይ ዞኑ የሚጠበቅበትን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተናግረዋል።

በደሴ ከተማ የደረቅ የጭነት ትራንስፖርት ባለንብረቶችን በማህበር ለማደራጀት ያለመ ውጤታማ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡*****የደሴ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ዛሬ ነሐ...
18/08/2026

በደሴ ከተማ የደረቅ የጭነት ትራንስፖርት ባለንብረቶችን በማህበር ለማደራጀት ያለመ ውጤታማ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡
*****
የደሴ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ዛሬ ነሐሴ 07 ቀን 2018 ዓ.ም በከተማዋ ከሚገኙ የደረቅ የጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶች ጋር ያካሄደውን የምክክር መድረክ በስኬት አጠናቋል።

የደረቅ የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ለሀገር፣ ለክልልና ለከተማችን ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆኑ፣ እየጨመረ የመጣውን የገቢና ወጪ ንግድ ፍላጎት ለማሟላት በዘርፉ ዘመናዊና የተደራጀ አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ የትራንስፖርት ሚኒስቴር የኦፕሬተር የብቃት ማረጋገጫ መመሪያ ቁጥር 968/2015 ለባለንብረቶቹ በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ከመድረኩ የተደመጡ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

የመምሪያው ኃላፊ መልእክት፡ የደሴ ከተማ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባተ እንደገለጹት፣ ባለንብረቶች በማህበር ተደራጅተው መስራታቸው ብቃታቸውን ወደ ተሻለ ደረጃ በማሳደግ በዘርፉ ጤናማ ውድድር እንዲኖር ያስችላል። አብዛኞቹ ባለንብረቶች ወጣቶች በመሆናቸው ከልማትና ማህበራዊ ተግባራት ጎን ለጎን ዘላቂ ሰላምን የመጠበቅና የማጽናት ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የህግና መመሪያ ማብራሪያ፡ የከተማዋ ትራፊክ ክፍል ኃላፊ ተወካይ ዋና ኢንስፔክተር አደፍርስ ከትራፊክ ህግጋት ጋር ተያይዞ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ የከተማው ማኔጅመንት አባላት ደግሞ በመመሪያው ነጥቦች ላይ በቂ ማብራሪያ በመስጠት ሙሉ መግባባት ላይ ተደርሷል።

የመድረኩ ዋና ዋና ውሳኔዎችና ስኬቶች፡-

• ማህበሩን ሙሉ በሙሉ ለመመስረት ስምምነት ላይ መደረሱ
• 5 አባላት ያሉት የሥራ አመራር ቦርድ (ሥራ አስፈጻሚ) መመረጡ
• 3 አባላት ያሉት የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ መመረጡ
• የማህበሩ ወርሃዊ የኮሚሽን ክፍያ መጠን በሙሉ ድምፅ መጽደቁ

ይህ የምስረታ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁ በደሴ ከተማ የሚሰጠውን የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ላቀ የብቃት ደረጃ እንደሚያሸጋገረው ከተሳታፊዎች የተገለፀ ሲሆን፣ የተመረጡት አመራሮችም ኃላፊነታቸውን ለጠቅላላ ጉባኤው አሳውቀዋል።

17/08/2026

የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ከጎጃም በርና ጣና በር የሕዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያዎች ጋር በመተባበር በባህር ዳር ከተማ ለ250 ተማሪዎች የደብተርና የእስክሪብቶ ድጋፍ አደረገ።

የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ለ250 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፤*****የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ከጎጃም በርና ጣና በር ...
15/08/2026

የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ለ250 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፤
*****
የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ከጎጃም በርና ጣና በር የሕዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያዎች ጋር በመተባበር በባህር ዳር ከተማ ለ250 ተማሪዎች የደብተርና የእስክሪብቶ ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉ የ90 ቀን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅድ አካል ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተማሪ አንድ ደርዘን ደብተሮችና የእስክሪብት ቁሳቁሶች ተበርክቶለታል።

በድጋፍ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘውዱ ማለደ፤ በተቋሙ ሥር የሚገኙ የሕዝብ ትራንስፖርት ማኅበራትና የአሽከርካሪ ማሠልጠኛ ተቋማት የማኅበረሰቡን ጫና የሚያቃልሉ በርካታ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ዘውዱ አክለውም፣ በመናኸሪያዎች በኩል ከ18.7 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ለ255 አረጋውያንና የመኖሪያ ቤት ችግር ላለባቸው ዜጎች የቤት ጥገናና ግንባታ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም፣ በ2018 በጀት ዓመት ከአቅም በላይ ለሆኑ ከ10 ሺህ በላይ ዜጎች ነፃ የትራንስፖርትና የኪስ ገንዘብ ድጋፍ መደረጉን አቶ ዘውዱ ገልጸዋል።

ቀደም ሲል ባልተገባ አሠራርና ሕገ-ወጥ ተግባራት ይታሙ የነበሩ መናኸሪያዎች አሁን አሠራራቸውን በመቀየር ለማኅበረሰቡ በጎ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ ዘውዱ፤ ለዚህ ተግባር ድጋፍ ላደረጉ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ምስጋና አቅርበዋል።

የቢሮው የትራንስፖርት አገልግሎት ስምሪት ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው መርሻ በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮግራም በክልል ደረጃ 12.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ድጋፍ ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በባህር ዳር ከተማ ከሚገኙት ጣና በርና ጎጃም በር መናኸሪያዎች 220 ሺህ ብር ገደማ በማሰባሰብ ለ250 ተማሪዎች ይህ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉንም ጠቁመዋል።

ከድጋፉ ተጠቃሚዎች መካከል ወይዘሮ አፀደ ምህረት፣ አቶ ምትኩ ይትባረክና ተማሪ ቃልኪዳን አስቻለው፤ ያገኙት ድጋፍ ያልጠበቁት እንደነበርና ለትምህርት ይወጣ የነበረውን ወጪ በመቀነስ ትልቅ እፎይታ መፍጠሩን በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል።

የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፉ ተማሪዎች ያለባቸውን የትምህርት ወጪ በመቀነስ በትምህርታቸው ላይ እንዲያተኩሩ የሚያግዝ ሲሆን፣ የመናኸሪያዎቹ በጎ ፈቃድ ተግባርም የማኅበረሰቡን ጫና ለማቃለል የሚያበረክተውን ሚና እንደሚያጠናክር በመርሐግብሩ ተገልጿል።

የኩታበር ወረዳ ህዝብ አርአያነት | በደቡብ ወሎ በማህበረሰብ ተሳትፎ እየተገነቡ ያሉ አስደናቂ የመንገድ ፕሮጀክት
11/08/2026

የኩታበር ወረዳ ህዝብ አርአያነት | በደቡብ ወሎ በማህበረሰብ ተሳትፎ እየተገነቡ ያሉ አስደናቂ የመንገድ ፕሮጀክት

በደቡብ ወሎ ዞን ኩታበር ወረዳ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የትራንስፖርትና የመሠረተ ልማት ጥያቄ ለመመለስ ...

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የሐምሌ ወር አፈጻጸምን ገመገመ።****ደብረ ብርሃን፦ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን መን...
11/08/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ የሐምሌ ወር አፈጻጸምን ገመገመ።
****
ደብረ ብርሃን፦ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ተቋማት ጋር በመሆን የሐምሌ ወር አፈጻጸሙን በዙም ሚቲንግ ገምግሟል።

መምሪያው በ90 ቀናት ውስጥ ለማከናወን ያቀዳቸውን መደበኛ ተግባራትና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች የሐምሌ ወር አፈጻጸምን ገምግሟል።

በግምገማው የሐምሌ ወር ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ቀርበው፣ የተገኙ ጥንካሬዎችና የታዩ እጥረቶች በመለየት ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በግምገማው ወቅት በቀጣይ በትራንስፖርት ዘርፍ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ማጠናከር፣ መደበኛ ቁጥጥርን በማጠናከር ሕገወጥነትን መከላከል፣ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተመላክቷል።

የመናኸሪያ ስምሪትንና አገልግሎት አሰጣጥን እንዲሁም መሠረተ ልማትን ማሻሻልና ማዘመን፣ የድንገተኛ ተሽከርካሪ ምርመራ አገልግሎትን ማጠናከር እና ሁሉአቀፍ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ከመንገድ ዘርፍ አንጻርም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ከወዲሁ መጀመር፣ በሁሉም ዘርፍ ሕዝቡን ባለቤትና ተሳታፊ በማድረግ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ጠበቅ ያለ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

መድረኩን የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ የመሩ ሲሆን፣ በመድረኩ የዞን ማኔጅመንት አባላት፣ የወረዳና ከተማ ኃላፊዎችና የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የወረዳና ከተማ ትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።

‎የሽንፋ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ መተማ ወረዳን ከቋራ በማገናኘት የህዝብ እንቅስቃሴንና የንግድ ትስስርን አጠናክሮልናል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ፤‎‎ተንጠልጣይ ድልድዩ ለማህበረሰቡ እ...
09/08/2026

‎የሽንፋ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ መተማ ወረዳን ከቋራ በማገናኘት የህዝብ እንቅስቃሴንና የንግድ ትስስርን አጠናክሮልናል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ፤

‎ተንጠልጣይ ድልድዩ ለማህበረሰቡ እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ለመመልከት በቦታው የተገኙት የዞን እና የወረዳ አመራሮች፤ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ድልድዩን በአግባቡ እንክብካቤ በማድረግ ለረዥም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ የማድረግ ሃላፊነት ወስደው በጥሩ ሁኔታ ተንጠልጣይ ድልድዩን መያዝ አለባቸው ብለዋል።

‎አቶ ተስፋ ሃይሌ የሽንፋ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ የሽንፋ ወንዝ ተንጠልጣይ ድልድይ ከመሰራቱ በፊት በክረምት ወቅት ጀልባ በተባለ ባህላዊ መሸጋገሪያ ዘዴ ማህበረሰቡ ሲጠቀም የነበረና በዚህም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲደርስ የነበር መሆኑን አስታው አሁን ላይ ይህ ድልድይ የነበረውን ችግር ከመቀየር ባለፈ የሽንፋ ከተማና ከቋራ ወረዳ ለሽንፋ አዋሳኝ ቀበሌ ኗሪዎች የገቢያ ትስስራችን በጣም እየጠነከረ በፀጥታ ችግርም ሁኖ መንግስት ማልማት እንደሚችል ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።

‎ተንጠልጣይ ድልድዩ በርካታ ቀበሌዎችን በልማት፣ንግድና ማህበራዊ ትስስር ተገናኝተን አዲስ የስራ ዕድል ተፈጥሮልናል ብለዋል።

‎አቶ ታደሰ ቸኮል ሌላኛው የሽንፋ ከተማ ነዋሪ በበኩላቸው፤ የተገነባው ዘመናዊ ድልድይ ችግራችን በመቅረፍ የህዝቡን የጉዞ ፣ የንግድ፣ የጤናና የትምህርት ተደራሽነት በእጅጉ ተጠቃሚ መሆን ችለናል ሲሉ ሃሳባቸውን ገልጸዋል።

‎የአካባቢችኝ ቀጠናን ትስስርራችን አጠናክሮልናል ‎ቀበሌዎችን ከቀበሌ ማገናኘት በመቻልችን የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚና የባህል ግንኙነታችን ተጠናክሯል።

‎በንግድና በኢኮኖሚ ተጠናክረን የግብርና ምርቶች፣ የንግድ ዕቃዎች እና ሌሎች ሸቀጦች በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲደርሱ ለማድረግ ትልቅ አቅም አግኝተናል ብለዋል።

መረጃው የ‎መተማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው።

በኢትዮጵያ ከቦሌ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል በባሕር ዳር ተመረቀ!****ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን የደጃዝማች በላይ ዘለቀ...
06/08/2026

በኢትዮጵያ ከቦሌ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል በባሕር ዳር ተመረቀ!
****
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ግዙፍ ተርሚናል መርቀው ከፍተዋል።

የዜናው ዋና ዋና ነጥቦች ፦

• ትልቅ የመሰረተ ልማት እመርታ፡ አዲሱ ተርሚናል ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ በኢትዮጵያ ሁለተኛው ግዙፍ ተርሚናል ነው።

• ችግርን ወደ መልካም አጋጣሚ፡ በግጭት ምክንያት ጉዳት ደርሶበት የነበረውን አሮጌ ተርሚናል መነሻ በማድረግ፣ ለትውልድ የሚሻገር የተሻለና ያማረ ግዙፍ ፕሮጀክት ዕውን ማድረግ ተችሏል።

• የከተማዋ መነቃቃት፡ ባሕር ዳር በቱሪዝም፣ በኢንዱስትሪ፣ በኮሪደር ልማትና በግዙፉ የዓባይ ድልድይ አማካኝነት የልማትና የብልጽግና ምሳሌ መሆኗ ተገልጻል።

• የቴክኖሎጂ ውጤት፡ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍትህን ለማረጋገጥ የጀመረው የቨርቹዋል (በቴክኖሎጂ የተደገፈ) ችሎት አሠራር በምሳሌነት ተ አንስቶ አድናቆት ተችሮታል።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የከአስተላለፉ 2 ቁልፍ መልዕክቶች፡

1. ገቢን ማሳደግ ፦

ባሕር ዳር ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ያሏት ቢሆንም፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በገቢ አሰባሰብ 7ኛ ደረጃ ላይ መገኘቷ የተሰሩትን ፕሮጀክቶች እንኳን ለመጠገን አቅም የሚያሳጣ በመሆኑ፣ ነዋሪውና አመራሩ የከተማዋን ገቢ ለማሳደግ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ ይገባል።

2. ሰላምን ማስቀደም ፦

"ቀኙ የሰራውን ግራ እንዳያፈርሰው..." ልማትን ለማስቀጠል ሰላም ወሳኝ ነው። አለመግባባቶች ቢኖሩ እንኳ በጨዋነት እና በንግግር የማስወገድ ባህል ሊዳብር ይገባል። አሁን ላይ ክልሉ ራሱን በራሱ በተሟላ ሁኔታ እያስተዳደረ በመሆኑ ሕዝቡ በጋራ በመቆም ከተማዋንና ክልሉን እንዲያለማ ጥሪ ቀርቧል።

06/08/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ምረቃ ላይ ያስተላለፉት ሙሉ መልዕክት

Address

Amhara
Bahir Dar
6000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara RoadTransport and Logistics Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara RoadTransport and Logistics Bureau:

Shortcuts

Share