01/06/2026
በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ቢጣ-ጌሻ የምርጫ ክልል ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው።
በምርጫ ክልሉ በጌሻ ወረዳ 43 የምርጫ ጣቢያዎች ህዝቡ በማለዳው የመራጭነት ካርዱን በመያዝ የቀጣይ መንግስቱን እየመረጠ ይገኛል።
ከምርጫው አስቀድሞም ከሌሊቱ 11:00 ጀምሮ በየሉም ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊዎች ፣ ታዛቢዎች ፣የተወዳዳሪ ፓርቲ ተወካዮች በተገኙበት የምርጫ ቁሳቁስ ቆጠራ የተደረገ ሲሆን መራጮች ድምጻቸውን የሚጥሉት ኮሮጆ ባዶ መሆኑ የመፈተሽና መልሶ የማሸግ ስራም ተከናውኗል።
የምርጫ ታዛቢዎቹ ፣ የተወዳዳሪ ዕጩ ተወካዮችና የምርጫ አስተባባሪዎች የመተማመኛ ቃለ ጉባኤ በመፈረምም ወደ መራጮች የድምጽ መስጠት ስራ ተጀምረዋል።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp
🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።