Gesha Woreda Communication

Gesha Woreda Communication ካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
(1)

በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ቢጣ-ጌሻ የምርጫ ክልል ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው። በምርጫ ክልሉ በጌሻ ወረዳ 43 የምርጫ ጣቢያዎች ህዝቡ በማለዳው የመራጭነት ካርዱን በመያዝ የቀጣይ መንግስቱን እየመረ...
01/06/2026

በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ቢጣ-ጌሻ የምርጫ ክልል ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው።

በምርጫ ክልሉ በጌሻ ወረዳ 43 የምርጫ ጣቢያዎች ህዝቡ በማለዳው የመራጭነት ካርዱን በመያዝ የቀጣይ መንግስቱን እየመረጠ ይገኛል።

ከምርጫው አስቀድሞም ከሌሊቱ 11:00 ጀምሮ በየሉም ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ጣቢያ ኃላፊዎች ፣ ታዛቢዎች ፣የተወዳዳሪ ፓርቲ ተወካዮች በተገኙበት የምርጫ ቁሳቁስ ቆጠራ የተደረገ ሲሆን መራጮች ድምጻቸውን የሚጥሉት ኮሮጆ ባዶ መሆኑ የመፈተሽና መልሶ የማሸግ ስራም ተከናውኗል።

የምርጫ ታዛቢዎቹ ፣ የተወዳዳሪ ዕጩ ተወካዮችና የምርጫ አስተባባሪዎች የመተማመኛ ቃለ ጉባኤ በመፈረምም ወደ መራጮች የድምጽ መስጠት ስራ ተጀምረዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

"ኢትዮጵያ ትመርጣለች!"ግንቦት 24 ለሚካሄደው ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶች በተገቢው መንገድ እየተሰራጩ መሆናቸውን የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል አስተባባሪ ገለጹ።የምርጫ ክልሉ አስተባባሪ አቶ ኢዮብ አ...
31/05/2026

"ኢትዮጵያ ትመርጣለች!"

ግንቦት 24 ለሚካሄደው ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶች በተገቢው መንገድ እየተሰራጩ መሆናቸውን የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል አስተባባሪ ገለጹ።

የምርጫ ክልሉ አስተባባሪ አቶ ኢዮብ አሰፋ በምርጫ ክልሉ በአጠቃላይ 110 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በቢጣ፤ ጌሻና ከፍል ሳይለም ወረዳዎችን እንደሚያጠቃልል ገልጸዋል።

በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁሶች የማሰራጨት ስራ በስኬት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

በደካ ከተማ አስተዳደር የአደባባይ ምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ብንያም ብርሃኑ እና የጤና ጣቢያ ሰፈር ምርጫ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሀይሌ ለምርጫ ማስፈጸሚያ የተላኩ ቁሳቁሶችን መረከባቸውን ተናግረዋል።

ቁሳቁሶቹ ደህንነቱ በተጠበቀ ቦታ ላይ መቀመጡን የጠቆሙቶ የጣቢያዎቹ ኃላፊዎቹ ለድምፅ መስጫው ዕለት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን ገልፀዋል:- ሲል ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4 ዘግበዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

በየትኛውም የምርጫ ጣቢያ 200 ሜትር ርቀት ውስጥ ሆኖ ለመዘገብ ባጅ የተሰጣቸው የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚከተሉትን ግዴታዎች ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡-👉 የሀገሪቱን እና የአካባቢውን ባህ...
29/05/2026

በየትኛውም የምርጫ ጣቢያ 200 ሜትር ርቀት ውስጥ ሆኖ ለመዘገብ ባጅ የተሰጣቸው የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚከተሉትን ግዴታዎች ማክበር ይጠበቅባቸዋል፡-

👉 የሀገሪቱን እና የአካባቢውን ባህልና ልምድ ማክበር፤

👉 በቦርዱ የተሰጠውን የመታወቂያ ባጅ በሚታይ መልኩ በመያዝ መንቀሳቀስ፤

👉 የመራጭ ምዝገባ መረጃዎችን በሰነድ ላይ ሲሰፍሩ ወይም መራጩ በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የምርጫ ምልክት ሲያደርግ አለመቅረጽ ወይም ፎቶግራፍ አለማንሣት፤

👉 ግለሰቡ በግልጽ እየተቃወመው መራጮችን እና ሌላ ማንኛውንም ሰው ፎቶ ወይም በተንቀሳቃሽ ምስል አለመቅረጽ እና ቃለ-መጠይቅ አለማድረግ፤

👉 የመራጮች ግላዊ ማንነትን በሚነካ አኳኃን መዝገብ፣ የመራጮችን ምዝገባ መታወቂያ ወይም ማንኛውንም ተመሳሳይ ሰነድ በፊልም አለመቅረጽ፣ ፎቶግራፍ አለማንሳት ወይም ኮፒ አለማድረግ፤

👉 የሕዝብን ሰብዓዊ መብትና መሠረታዊ ነፃነቶች ማክበር፤

👉 የቦርዱን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፀጥታና የደኅንነት እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት አካላትን ሚና እና ሥልጣን ማክበር፣

👉 ለምርጫ አስፈጻሚዎች ስለ ኃላፊነታቸው ምክር ወይም መመሪያ አለመስጠት፣

👉 መራጩ ድምፁን ለማን እንደሰጠ አለመጠየቅ፣

👉 የሕግ ጉዳዮችን በራስ አለመተርጎም እና የምርጫ ሂደትን የሚመለከት ሕጋዊ ያልሆነ መረጃ ወይም መመሪያ አለማስተላለፍ፣

👉 ለድምፅ መስጫ የተከለለ ቦታ ካሜራም ሆነ ሌላ የድምፅ ወይም የምስል መቅጃ መሣሪያ አለመጠቀም፣

👉 ከአድሎና ከወገንተኝነት በፀዳ አኳኋን ተግባራትን ማከናወን ይጠቀሳሉ።

የጌሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ አንድሰው ዓለማየሁ ለዓረፋ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ‎‎የጌሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፍና የመንግስት ዋና...
27/05/2026

የጌሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ አንድሰው ዓለማየሁ ለዓረፋ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

‎የጌሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፍና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አንድሰው ዓለማየሁ ለ1447ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎አቶ አንድሰው በመልዕክታቸው ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለዓረፋ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ብለዋል።

‎የዓረፋ በዓል በህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ የመተጋገዝ የአብሮነት እና የመታዘዝ በዓል ሆኖ ትልቅ ስፍራ እንደሚሰጥ የገለጹት አስተዳዳሪው በወረዳችን የሚገኙ የሙስሊም ማህበረሰብ ይህን ሲያከናውን መቆየቱንም አንስተዋል።

‎በዚህ በዓልም የተለመደውን የመተባበር እና የመደጋገፍ እሴት በማጠናከር አንድነትን ማጉላት አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

‎አሁን ሀገራችን 7ኛውን ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ ለማካሄድ በዋዜማው ስለሚትገኝ በወረዳችን የሚትገኙ የሙስሊሙ ማህበረሰብ በጸሎት እና በዱአ ፈጣሪ ፊት በመቅረብ ኃይማኖታዊ ኃላፊነታቸውን እንድትወጡ ሲሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

‎በድምፅ አሰጣጥ ሂደትም ካርድ የወሰዱ ሁሉ የአንድ ሰው ድምፅ ዋጋ ስላላት ሁሉም በነቅስ ወጥቶ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

‎የዓረፋ በዓል የፍቅር ፣ የሰላም ፣ የመቻቻል፣ የአንድነት ፣ የአብሮነት እንዲሆን እመኛለሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለ1ሺህ 4መቶ 47ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢድ አል አደሃ /አረፋ/ በዓልን አስመልክቶ አቶ ካሳሁን ገብሬ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ። ለ1ሺህ 447ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢድ አል ...
27/05/2026

ለ1ሺህ 4መቶ 47ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢድ አል አደሃ /አረፋ/ በዓልን አስመልክቶ አቶ ካሳሁን ገብሬ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ለ1ሺህ 447ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢድ አል አደሃ /አረፋ/ በዓልን አስመልክቶ የጌሻ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ካሳሁን ገብሬ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አስተዳዳሪው ባስተላለፉት መልዕክት የዒድ አል-አድሃ በዓል የእስልምና እምነት ተከታዮች ፍጹም ታዛዥነታቸውን መስዋዕትነታቸውን እና ለፈጣሪ ያላቸውን ፍቅር ያረጋገጡበት ታላቅ ዕለት ነው።

በየዓመቱ የሚከበረው የአረፋ በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ትርጉም ያለው ሃይማኖታዊ በዓል ሲሆን በህዝቦች መካከል ወንድማማችነትን መተሳሰብንና መደጋገፍን በተግባር በማሳየት ረገድ የጎላ ድርሻ እያበረከተ የቆየ በዓልም ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ ታላቅ በዓል የፍቅር፣ የአንድነት እና የሰላም እሴቶችን የሚያጎለብት ሃይማኖታዊ በዓል ነው።

ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳትና አብሮ በማሳለፍ እንዲሁም የተለመደ የመተዛዘንና የመረዳዳት እሴቶቹን በማጉላት ሊሆን ይገባል ሲሉ አቶ ካሳሁን አስገንዝበዋል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

በቦንጋ ከተማ የብልጽግና ፓርቲን የሚደግፍ ታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ይገኛል።ክልላዊ፣ የብልጽግና ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ ለመደገፍ የተዘጋጀ ደማቅ ሕዝባዊ ሰልፍ በተለያዩ ባህላዊና ዘ...
26/05/2026

በቦንጋ ከተማ የብልጽግና ፓርቲን የሚደግፍ ታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ክልላዊ፣ የብልጽግና ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ ለመደገፍ የተዘጋጀ ደማቅ ሕዝባዊ ሰልፍ በተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ ትርኢቶች፣ የፈረስ ጉግስና የኪነ-ጥበብ ኩነቶች ታጅቦ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

የከተማዋና የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ከተለያዩ የክልሉ አከባቢዎች የተገኙ አባልና ደጋፊዎች ከማለዳው ጀምሮ በነቂስ በመውጣት፣ የለውጡ መንግሥት ያስመዘገባቸውን ሁለንተናዊ ድሎች እውቅና በመስጠትና አጋርነታቸውን በተግባር እያሳዩ ይገኛል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡት የልማት ድሎች የዚሁ ሕዝባዊ ድጋፍ መሠረት መሆናቸው በሰልፉ ላይ በተለያዩ መርህ ቃሎች ተንጸባርቋል።

እነዚህ የተገኙ ስኬቶች የክልሉን ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጣቸውም በላይ፣ ለቀጣይ የብልጽግና ጉዞ ጠንካራ መሠረት የሚጥሉ እንደኾነም እንዲሁ ተገልጿል።

ሕዝቡ በአንድ ድምፅ እንደገለጸው፣ የተጀመረውን የልማትና የሰላም ጉዞ ለማስቀጠል፣ የአካባቢውን ዕምቅ ሀብት ወደ ደጨባጭ ልማት ለመቀየርና የክልሉን ሁለንተናዊ ከፍታ ለማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲን ማስቀጠል ተገቢ እንደኾነም ተገንዝቧል።

በመሆኑም በመጪው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲውን የብርሃን ጉዞ ለመደገፍና ድምፁን ለብልጽግና ለመስጠት ሕዝቡ ሙሉ በሙሉ ዝግጁና ቁርጠኛ መኾኑን በይፋ አውጇል።

በአጠቃላይ፣ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ፣ የብልጽግና ፓርቲ በሕዝብ ልብ ውስጥ ያለውን ጥልቅ መሠረትና ተቀባይነት በድጋሚ ያረጋገጠ ነው።

የፓርቲው አባልና ደጋፊ በነቂስ ወጥቶ የለውጡን ድሎች እውቅና መስጠቱና ለቀጣዩ ምርጫ ያለውን ዝግጁነት መግለጹ፣ ፓርቲው የጀመረውን ሕዝብን ተጠቃሚ የማድረግና አገርን የማበልጸግ ታላቅ ተልዕኮ በድል አድራጊነት ለማስቀጠል ተጨማሪ የሞራልና የፖለቲካ አቅም የፈጠረለት ታላቅ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል።

በዚህ ታላቅ የምርጫ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማንና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ሲል የዘገበው የደቡብ ምዕራብ ኮሙኒኬሽን ነው ።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ፣ነጻ ፣ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅና የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው ሂደት ሊኖራቸው በሚገባው ሚና ዙሪያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውይይት ...
25/05/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ፣ነጻ ፣ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅና የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው ሂደት ሊኖራቸው በሚገባው ሚና ዙሪያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውይይት አካሄደ።

በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ፣ነጻ ፣ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅና የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው ሂደት ሊኖራቸው በሚገባው ሚና ዙሪያ የዞኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጌሻ እና የደካ ከተማ አስ/ር የጋራ ምክር ቤት ውይይት አካሄደ።

በመድረኩ ላይ የፓርቲዎች ሚና፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ማስፋት እንዲሁም የምርጫን ውጤት በጸጋ የመቀበል ባህልን ማዳበር በሚቻልባቸው አቅጣጫዎች ላይ ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ሰፍ ውይይት ተካሂደዋል።

ምርጫውን በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ መስራት፤ ሁለተኛ ደግሞ የመጣውን ውጤት በጸጋ ተቀብሎ ችግሮች ቢኖሩ እንኳን በሰለጠነ ፖለቲካዊ አግባብ መፍታት እንሚገባም ነው በውይይቱ የተገለፀው፡፡

ገዢው ፓርቲም የምክር ቤቱ አባል በመሆኑ እንደ መንግስትና እንደ ፓርቲ የሚነሱ ጥያቄዎችንና ችግሮችን በጋራ እየገመገሙ ለመፍታት ጥረት ሲደረግ መቆየቱ የተገለፀ ስሆን መንግስትም የምርጫውን ምህዳር በማስፋትና ለፓርቲዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ጥሩ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነም ተገልፀዋል።

በጀግንነት መጠበቅ! በሰብዓዊነት ማገልገል!!
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ምርጫው 7 ቀናት ብቻ ቀርተውታል! ምልክታችን የመደመር ፣ የትብብር እና የአንድነት መገለጫ የሆነው የስንዴ ነዶ ነው !
25/05/2026

ምርጫው 7 ቀናት ብቻ ቀርተውታል!
ምልክታችን የመደመር ፣ የትብብር እና የአንድነት መገለጫ የሆነው የስንዴ ነዶ ነው !

ሰላም በለለበት ማንኛውም ሀገራዊ እድገት እውን ማድረግ ስለማይቻል በቅድሚያ ለሰላም ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል:- አቶ ካሳሁን ገብሬ። የካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በድድፋ ቀበሌ ከወንጀ...
24/05/2026

ሰላም በለለበት ማንኛውም ሀገራዊ እድገት እውን ማድረግ ስለማይቻል በቅድሚያ ለሰላም ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል:- አቶ ካሳሁን ገብሬ።

የካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በድድፋ ቀበሌ ከወንጀል ስጋት ነፃ ሆኖ የነጭ ባንዲራ መስቀል ፕሮግራም ተካሂደዋል።

በፕሮግራሙ የተገኙት የጌሻ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ካሳሁን ገብሬ እንደተናገሩት ሰላም በለለበት ማንኛውም ሀገራዊ እድገት እውን ማድረግ ስለማይቻል በቅድሚያ ለሰላም መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል።

አክለውም ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል አካባቢዉን ከወንጀል ስጋት ነፃ ለማድረግ የነቃ ተሳትፎ በማበርከት ሀገራዊ እድገቱን ማረጋገጥ ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል።

ሰላምና የሀገር እድገት የማይነጣጠሉ በመሆናቸዉ ሰላም ለሀገር እድገት ያለዉ አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ካሳሁን ማህበረሰቡ አካባቢዉን ከወንጀል ጽዱ ለማድረግ ከጸጥታ አካላት ጋር በንቃት መስራትና ወንጀል ጠል ትውልድ ማፍራት አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

የጌሻ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን ሀብታሙ ወርቁ በበኩላቸዉ ይህንን የልማት ስራ ለማስቀጠል ሰላም ትልቁን ቦታ የሚይዝ በመሆኑ በየደረጃ ያለው ማህበረሰብ ተቀናጅቶ መስራት አለበት ብለዋል።

በ2018 በጀት ዓመት አምስት ቀበሌዎችን ከወንጀል ጽዱ አድርጎ ለማስመረቅ ታቅዶ ሁለት ቀበሌዎችን ማስመረቅ ተችሏል ያሉት የወረዳዉ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን ሀብታሙ ከሁለቱ ውስጥ አንዱ ዛሬ የተመረቀዉ ድድፋ ቀበሌ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ቀበሌዉ ከወንጀል ስጋት ነጻ እንዲሆን የድርሻቸዉን ለተወጡ ቀበሌ መዋቅር፣ ለወረዳው መንግስት፣ፓትሮል ቅኝት፤ምሊሻ መዋቅር፣የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች እንድሁም ለማህበረሰቡ ምስጋናቸዉን አቅርበዉ ሌሎች ቀበሌዎችም ይህን ተሞክሮ በመውሰድ አካባቢያቸዉን ከወንጀል ስጋት ነጻ እንድያደረጉ ሳጅን ሀብታሙ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

በመርሃ ግብሩ የደ/ምዕ/ኢት/ክልል የመስኖ ኤጀንሲ ምክትል ቢሮ ኃላፍ አቶ አፈወርቅ ዓለሙ የጌሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሳሁን ገብሬ የካፋ ዞን ትራንስፖርት መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፍ አቶ በላይ ባደገ የካፋ ዞን ፕላን ኮምሽን መምሪያ ኃላፍ አቶ አስማማው አደሜ የወረዳ ም/አስተዳደርና ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ታከለ ዓለማየሁ እንድሁም የወረዳው አስተባባሪ አካላትና አመራር የካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፍተኛ መኮንኖች የወረዳ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን ሀብታሙ ወርቁን ጨምሮ የጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አመራርና አባላት የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት መሪዎች እና ሌሎች ተገኝተዋል።

በጀግንነት መጠበቅ! በሰብዓዊነት ማገልገል!!
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

በካፋ ዘን ጌሻ ወረዳ ለፖሊስ አመራርና አባላት የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ በምርጫ የጸጥታ አስከባሪዎች አሠራርና ሥነ-ምግባር መመሪያ ዙርያ ስልጠና ተሰጠ። ከካፋ ዞን ፖሊስ መምርያ ኮ...
19/05/2026

በካፋ ዘን ጌሻ ወረዳ ለፖሊስ አመራርና አባላት የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ በምርጫ የጸጥታ አስከባሪዎች አሠራርና ሥነ-ምግባር መመሪያ ዙርያ ስልጠና ተሰጠ።

ከካፋ ዞን ፖሊስ መምርያ ኮማንደር ታደለ ቦጋሌ እና ኮማንደር ክፍለ ተካ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ሰነዱን በማቅረብ ስልጠና የተሰጠ ስሆን ከጌሻ ወረዳ ጸጥታና ሚልሻ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደረጀ ደምሴ ጋር በመሆን ዉይይቱን መርተዋል።

የጌሻ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን ሀብታሙ ወርቁን ጨምሮ አጠቃላይ የወረዳው ፖሊስ አመራርና አባላት በመገኘት ስልጠናውን ወስደዋል።

ከፊታችን ያለዉ 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ተዓማኒ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን የጸጥታ አካላት ትልቅ ሀላፊነት የተጣለባቸዉ መሆኑ በሰነዱ ተገልፀዋል።

ከምርጫ በፊትና እንዲሁም በምርጫ ወቅት ከማንኛውም ብልሽትና ስርቆት አከባቢውን መረጃ በማደራጀትና በመጠበቅ በልዩ ትኩረት ሊሠራ እንደሚገባና ምርጫው ሰላማዊና የዜጎች ደህንነት የተጠበቀ ሆኖ እንዲጠናቀቅ፣ የፖሊስ አባላት ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃና ገለልተኛ በመሆን መሥራት እንደሚገባ ተጠቁመዋል።

በመጨረሻም ከፊታችን ያለዉ 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም ፀጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊዉን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ፖሊስ የአንበሳ ድርሻ ልወጣ እንደሚገባ እና አጠቃላይ በተነሳው አጀንዳ ላይ የጋራ አቅጣጫ ተይዘዋል።

በጀግንነት መጠበቅ! በሰብዓዊነት ማገልገል!!
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏🙏አብረዎን ስላሉ እናመሰግናለን🙏🙏
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

Address

Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gesha Woreda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gesha Woreda Communication:

Share