Gesha Woreda Communication

Gesha Woreda Communication ካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

‎በጌሻ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግሥት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ መካሄድ ተጀመረ።‎ጌሻ፦ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ...
02/09/2026

‎በጌሻ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግሥት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ መካሄድ ተጀመረ።

ጌሻ፦ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) በካፋ ዞን በጌሻ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈፃፀም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ በጌሻ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል።

‎የምዘና መድረክን የመሩት የካፋ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፍ አቶ አብረሃም አባቴ እንደተናገሩት የመድረኩ ዋና ዓላማ በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማጠናከር ጉድለቶችን በማረም ለቀጣይ ተልዕኮዎች አመራሩን ይበልጥ ለማዘጋጀት እንደሆነ ነው ብለዋል።

አያይዘውም አቶ አብረሃም በ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ የፓርቲና የመንግሥት ተግባራት አፈጻጸም በጥልቀት በመገምገም አመራሩ ጥንካሬዎቹን አጠናክሮ እንዲቀጥልና የታዩ ክፍተቶችን በዝርዝር በመፈተሽ ቀጣይ ለላቀ ስኬት እንዲዘጋጅ ለማድረግ ያለመ መሆኑንም ነው የገለፁት።

የካፋ ዞን የግብርና መምሪያ ም/ኃላፍና የቡና ሻይና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሞገስ ተክሌ በበኩላቸው ምዘናው በአመራሩ መካከል የተግባር እና የአስተሳሰብ አንድነት ወጥነት በማጠናከር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማስቀጠል ትልቅ አቅም እንደሚኖረው ትልቅ ተስፋ ሰጭ መድረክ ነው ብለዋል።

‎ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው የምዘና መድረክ ላይ የወረዳው የመንግሥት ረዳት ተጠሪና አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አጥናፉ አሰፋ አማካኝነት የፓርቲና የመንግሥት የሥራዎች አፈጻጸም ሪፖርት ሰነድ እየቀረበ ይገኛል።

የካፋ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፍ አቶ አብረሃም አባቴ፣ የካፋ ዞን የግብርና መምሪያ ም/ኃላፍና የቡና ሻይና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሞገስ ተክሌ መድረኩን እየመሩ ስሆን በመድረኩም የወረዳው አስተባባሪ አካላት እና አጠቃላይ አመራር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

  የጠለፋ ወንጀል የፈፀሙት ግለሰቦች በፅኑ እስራት መቀጣታቸው ተገለፀ። በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የጠለፋ ወንጀል የፈፀሙት ግለሰቦች በፅኑ እስራት መቀጣታቸው ተገለፀ። የጌሻ ወረዳ ፖሊስ ከህብረ...
31/08/2026


የጠለፋ ወንጀል የፈፀሙት ግለሰቦች በፅኑ እስራት መቀጣታቸው ተገለፀ።

በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የጠለፋ ወንጀል የፈፀሙት ግለሰቦች በፅኑ እስራት መቀጣታቸው ተገለፀ።

የጌሻ ወረዳ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሠረት ባደረገው ክትትል ተጠሪጣሪውን ቁጥጥር ስር በማዋል የሰውና የሰነድ ማስረጃ አደራጅተው ለወረዳው ዓቃቤ ህግ መረጃ ማስተላለፉ ይታወቃል።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሰኔ 29/2016 ዓ.ም ዕለተ ቅዳሜ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጋወቲ ቀበሌ በአሁኑ ሰዓት ለግዜው ለህግ እጃቸውን ያልሰጡት 1ኛ ተከሳሽ ሙሉቀን አሻግሬ የ16 ዓመቷን ተበዳይ ልዩወርቅ ማሞን አፍ አፍኖ ሲይዝ 2ኛ ተከሳሽ ማሙሽ ዓለሙ ደግሞ ከጮህሽ እንገልሻለን በማለት ማስፈራሪያ በማድረስ ሁለቱን እግሮቿን በመያዝ በግዳጅ ወደ ሌላ ቦታ በማዛወር ተከሳሾቹ ተበዳይን በኃይል ጠልፈው ማሙሽ ዓለሙ በተባለው ግለሰብ ባጃጅ ውስጥ በማስገባት ከቦታው ይሰውሩታል።

በዚህም ተበዳይ ልዩወርቅን በባጃጅ በመጫን ወደ ሸካ ዞን ማሻ ወረዳ ነጨ ገሮ ቀበሌ በመውሰድ ለ3ኛ ተከሳሽ ለዘላለም ዘለቀ አሳልፎ መስጠታቸው ነው የተገለጸው።

የዓቃቤ ህግ ክስ እና የፍርድ ቤቱ ውሳኔ
የጌሻ ወረዳ ዓቃቤ ህግ የፖሊስን የምርመራ መዝገብ ከተቀበለ በኋላ ተከሳሽ ዘላለም ዘለቀ የክስ መዝገብ አዘጋጅቶ ለወረዳው ፍርድ ቤት አቅርቧል።

ጉዳዩን ሲያከራክር የቆየው የጌሻ ወረዳ ፍርድ ቤት የቀረቡትን የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች በዝርዝር መርምሮ በማረጋገጥ ተከሳሹ ጥፋተኛ መሆኑን ወስኗል።

በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘላለም ዘለቀ የኢፌዴሪ ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 587(1) እና 620(1&2) "ሀ" ስር የተደነገገውን በመተላለፍ በመሆኑ ወንጀለኛው በ10 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

ህገወጥ የጦር መሳርያ ይዞ በገበያ ዉስጥ ስንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ ከኔ መሳርያ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ። በቀን 23/12/2018 ዓ.ም  ህገወጥ የጦር መሳርያ ይዞ በጌሻ ወረዳ የሽት ቀ...
30/08/2026

ህገወጥ የጦር መሳርያ ይዞ በገበያ ዉስጥ ስንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ ከኔ መሳርያ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ።

በቀን 23/12/2018 ዓ.ም ህገወጥ የጦር መሳርያ ይዞ በጌሻ ወረዳ የሽት ቀበሌ በገበያ ዉስጥ ስንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ ከኔ መሳርያ በቁጥጥር ስር ዉሏል።

ነዋሪነቱ ሳይለም ወረዳ ተችብ የሆነው ግለሰብ ወጣት ስንታየው ታደሰ በቀን 23/12/2018 ዓ.ም ህገወጥ የጦር መሳርያ ይዞ በየሽት ቀበሌ በገበያ ዉስጥ ስንቀሳቀስ የነበረ ስሆን ከነመሳሪያዉ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የጌሻ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር ሀብታሙ አለማየሁ ተናግረዋል።

አያይዘውም ረ/ኢንስፔክተር ሀብታሙ እንደገለፁት አንድ ህገ ወጥ ሽጉጥ ከመሰል ሶስት ፍሬ ጥይት ጋር በቀበሌ ኦፊሴር ፖሊስ ድንገተኛ ፍተሻ ተይዞ ከኔ ተጠርጣሪ ለህግ የቀረበ መሆኑ ተረጋግጠዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

በጌሻ ወረዳ የእስካሁኑ የመደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም ከ50% በላይ መድረሱ ተገለፀ።  በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም የዞኑ ደጋፊ ...
29/08/2026

በጌሻ ወረዳ የእስካሁኑ የመደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም ከ50% በላይ መድረሱ ተገለፀ።

በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም የዞኑ ደጋፊ ባለሙያ በተገኘበት ተገምግሞ ለቀጣይ አቅጣጫ የተቀመጠ ስሆን የእስካሁን የመደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም ከ50% በላይ መድረሱ ተገልጸዋል።

የጌሻ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አስራት ከተማ በመድረኩ ላይ እንዳነሱት በወረዳው እስካሁን በተጨባጭ ያለዉን የተማሪዎች ምዝገባ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ ለቀጣይ በቀረዉ ዉስን ጊዜ ዉስጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመሥራት ምዝገባውን ማሳካትና አስፈላጊውን ሪፖርት ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

አያይዘዉም የተማሪዎች ምዝገባ ከተጀመረ ጀምሮ በሚመለከታቸው አካላት የሚደረግ ድጋፍና ክትትል የሚመሰገን መሆኑን አንስቶ ለቀጣይም ከዝህ በተሻለ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ምዝገባው እንዲሳካ በተቀናጀ መልኩ እርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ከዝህም ጋር ተያይዞ ዘንድሮ በጌሻ ደካ ት/ት ለትዉልድ ፕሮጀክት 20 ተማሪዎችን ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስገባት መቻሉ በየደረጃ ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅትና አደረጃጀቶችን በማጠናከር ከተሰራ ዉጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ማሳያ በመሆኑ ለዚህ ተግባር ተገቢው ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አቶ አስራት አሳስበዋል።

የካፋ ዞን ት/ት መምርያ ባለሙያ አቶ ስንታየሁ ተስፋዬ በበኩላቸው የተማሪዎች ምዝገባ በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመሥራት በተቀመጠው የምዝገባ መርሃ ግብር ግዜ ገደብ መሠረት ለማጠናቀቅ እርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

አያይዘውም አቶ ስንታየሁ በተማሪዎች ምዝገባ ሂደት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች ላይ በጋራ የተወሰዱ ያሉ መፍትሔዎች መኖራቸዉና በሪፖርቱ መካተቱንም በጠንካራ ጎን አንስቶ ለቀጣይ በወረዳ አመራሮችን ጨምሮ በሌሎችም ባለድርሻ አካላት በተሻለ እየተደገፈ በተቀመጠው ግዜ ምዝገባ እንዲጠናቀቅ ተጠናክሮ ልቀጥል ይገባል ስሉ ተናግረዋል።

አክለውም በምዝገባው ጎን ለጎን የት/ት ቤቱን ከባቢ ምቹና ማራኪ ለማድረግ ለአብነት የመማርያ ክፍል ከወንበር ጥገና ጀምሮ ለተማሪዎች ምቹ የማድረግ ስራ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በዲጂታል የታገዘ ትምህርት ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ የማታ ትምህርት ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ትኩረት የሚሻ ስራ መሆኑን አሳስበዋል።

በአጠቃላይ በመድረኩ ላይ የወረዳ ት/ት ጽ/ቤት ባለሙያዎችና ሱፐርቫይዜሮች የተሳተፉ ስሆን በሪፖርቱ በቀረበው የምዝገባ አፈጻጸም ላይ በጉድለት የተገመገመዉን ለማሻሻልና በጠንካራ የተነሱትን ተጠናክሮ በቀጣይ ተግባራዊ የማስፈጸሚያ ስልቶችን በመንደፍና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ የተማሪዎች ምዝገባን ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራ የጋራ አቅጣጫ ተይዘዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

በ2018 ዓ/ም ያመለጡንን ዕድሎች በመፈተሽ በ2019 ዓ/ም ለህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር  ጥያቄ ፈጣን ምላሽ መስጠት አለብን÷ ዶ/ር ኢንጂነር አስራት ገ/ማሪያም::በደቡብ ምዕራብ ኢት...
29/08/2026

በ2018 ዓ/ም ያመለጡንን ዕድሎች በመፈተሽ በ2019
ዓ/ም ለህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ፈጣን ምላሽ መስጠት አለብን÷ ዶ/ር ኢንጂነር አስራት ገ/ማሪያም::

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የካፋ ዞን የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ በቦንጋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የክልሉ ደን አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኢንጂነር አስራት ገ/መሪያም እንደተናገሩት በ2018 ዓ/ም ያመለጡንን ዕድሎች በመፈተሽ በ2019 ዓ/ም ለህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት አለብን ብለዋል::

በ2018 ዓ/ም በፓርቲና በመንግስት ኢንሸቲቮች በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውንና ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል::

ባሳለፍነው ዓመት የተካሄደውን ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫን ዴሞክራሲያዊ እና በህዝብ ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ እንደሀገር እና እንደዞን ስኬታማ መሆን መቻሉንም ተናግረዋል::

እንደ ዶ/ር ኢንጂነር አስራት ገ/ማሪያም ገለፃ የመድረኩ ዋነኛው ዓላማ በ2018 ዓ/ም በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ጠንካራ አፈፃፀሞችን የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠልና ድክመቶችን በማረም ያመለጡንን ዕድሎች ፈትሾ ህዝባችንን በሁሉም መስኮች ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል::

ዶ/ር አንጂነር አስራት ገ/ማሪያም አክለው የተቀመጡ ተልዕኮዎችን በአግባቡ በመፈጸም የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የከተማና የገጠር ልማቶች መከናወናቸውን እና ከአፈጻጸም አኳያ መሻሻሎች መታየታቸውን ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአስፈፃሚ ተቋማት እና በአመራሩ መካከል የሚታየውን የተግባር አፈጻጸም ልዩነት በማጥበብ የአመለካከት ክፍተቶችን ማስተካከል እንደሚያስፈልግ የተናገሩት ዶ/ር አስራት በሂደቱ የአመራር ቁመና በብልፅግና ፓርቲ መሠረታዊ መርሆችና ዕሴቶች ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።

መድረኩ በየደረጃው የሚገኘውን አመራር በመገምገምና በመመዘን የአመለካከትና የተግባር አንድነት በማምጣት በቀጣይ የሕዝብ ተጠቃሚነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ መሆኑንም ተናግረዋል።

ለዚህም አመራሩን በማጥራት ለቀጣይ ተልዕኮ ከማዘጋጀት ባሻገር፣ የውስጠ ፓርቲ ጤንነትና የዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መርህን በማረጋገጥ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳካት የሚያዘጋጅ መሆኑም ተጠቁሟል።

አመራሩ የፓርቲና የመንግሥት ተግባራትን በጥራትና በውጤታማነት እንዲያከናውኑ ማብቃት እንደምያስፈልግ አጽንኦት ተሰጥቷል።

መድረኩን የክልሉ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸውና የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አስራት አሰፋ በጋራ እየመሩ ሲሆን በመድረኩ የዞን አጠቃላይ አመራር እንዲሁም የሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ሥራ አስተባባሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ:- ሲል የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

በጌሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት  የ2018 ዓ.ም አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም እቅድ ዝግጅት ዙርያ ግምገማ ተካሄደ። በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም አፈፃፀምና የ...
28/08/2026

በጌሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም እቅድ ዝግጅት ዙርያ ግምገማ ተካሄደ።

በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት የእቅድ ዙርያ የዞኑ ደጋፊ ባለሙያ በተገኘበት ግምገማ ተካሄደ።

የካፋ ዞን የሶሽዮ ኢኮኖሚና ፊዚካል ጂኦግራፍ መረጃ ጥናትና ትንተና ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ቶማስ ወልደ በወረዳው ሴክተር ልማት ዕቅድ ሶሺዮ ኢኮኖሚ ስነ ህዝብ የስራ አፈፃፀም ካፒታል ፕሮጀክትን ጨምሮ አጠቃላይ የሴክተር ስራ አፈፃፀም ገምግመዋል።

በግምገማው አቶ ቶማስ እንዳነሱት በሴክቴሮች በሪፎርም ስራዎች እቅድ ዝግጅት ዙርያ ግንዛቤ ከማስጨበጥ ጀምሮ ዕቅድ በመሰብሰብና የወረዳ እቅድ መዘጋጀቱን ሪፖርቶች ተሰብስበው ግብረመልስ መሰጠቱንና የካፒታል ፕሮጀክቶች ድጋፍና ክትትል መደረጉን እንደ ጠንካራ ጎን በማንሳት ለቀጣይ ተጠናክሮ ልቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።

አክለውም የሶሽዮ ኢኮኖሚ መረጃን በየሩብ ዓመቱ መሰብሰብና የ2018 ዓ.ም የማጠቃለያ መረጃ በወረዳ ደረጃ መገምገሙ እንደ ጠንካራ ጎን የተነሳ ስሆን ለቀጣይ በየደረጃ ከሚገኙት ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ትክክለኛ መረጃ መሰብሰብ ማደራጀትና ለሚመለከተው ሪፖርት የማድረግ ስራ ተኩረት የሚሻ መሆኑን ገልፀዋል።

የጌሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰድቅ አብዱ እንደተናገሩት የተቋማትን ስራ መከታተል ግብረመልስ መስጠት የሴክተሮችን አፈፃፀም መገምገምና ደረጃ መስጠት የጽ/ቤቱ ሀላፊነት መሆኑን ገልጸው ለቀጣይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በመቀጠልም አቶ ሙሰድቅ ጽ/ቤቱ የ2018ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም መነሻ በማድረግ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለቀጣይ የ2019ዓ.ም የዕቅድ አካል ተደርጎ በየደረጃ ከሚገኘው ባለድርሻ አካላት ጋር በመፍታት ከላይ የተነሱ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በመጨረሻም የሴክተሩ ኃላፊና ባለሙያዎች በተገኙበት የ2018ዓ.ም ስራ አፈፃፀም ተገምግሞ በጉድለት የተነሱትን ለማሻሻልና በጥንካሬ የተገመገመዉን አጠናክሮ ለማስቀጠል በ2019 ዓ.ም የእቅድ ዝግጅትና በቀጣይ በሚወሰዱ መፍትሔዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጎ ለቀጣይ የጋራ አቅጣጫ ተይዘዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

'አፈሳ'' አለ በማለት የሚሠራጨው መረጃ ፍፁም ከእዉነት የራቀና ተቀባይነት የለለው መሆኑን የጌሻ ወረዳ ሠላም ፀጥታና ሚልሻ ጽ/ቤት ገለፀ። የጌሻ ወረዳ ሠላም ጸጥታና ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ አ...
27/08/2026

'አፈሳ'' አለ በማለት የሚሠራጨው መረጃ ፍፁም ከእዉነት የራቀና ተቀባይነት የለለው መሆኑን የጌሻ ወረዳ ሠላም ፀጥታና ሚልሻ ጽ/ቤት ገለፀ።

የጌሻ ወረዳ ሠላም ጸጥታና ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደረጀ ደምሴ በአሁኑ ወቅት በወረዳው በየትኛውም ሥፍራ ምንም አይነት የአፈሳ ተግባር እንደሌለ ገልፀዋል።

አክለውም በሀገር መከላከያ ሠራዊት የምልመላ መሥፈርቶችን ያሟሉትንና በራስ ፍቃድ ለመሄድ ዝግጁ የሆኑትን ብቻ ምልመላ እያካሄደ መሆኑን ገልፀው በአሁኑ ወቅት የተዛባ መረጃን በማሠራጨት የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ምልመላን ለማደናቀፍ የሚደረግ እንቅስቃሴ እንደሆነ ተናግረዋል።

በወረዳችን ውስጥ ''አፈሳ'' አለ በማለት ህበረተሰቡን ከየትኛውም የልማት እንቅስቃሴ ወደ ኋላ ለማስቀረት የምናፈሰው ሀሰተኛ መረጃ መሆኑን የጠቆሙት ሀላፊው እንደዝህ ዓይነት ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላትም ሆኑ ቡድኖች በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን ተገንዝበው ከእንድህ አይነት ተግባር እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

በመጨረሻም አቶ ደረጀ ወጣቱና መላው የማህበረሰብ ክፍሎች ከእንደዝህ አይነት የተዛባ መረጃ ራሱንና ቤተሰቡን በመጠበቅ እንደ ወትሮ ሁሉ ለልማትና መሰል ጉዳዮች በነጻነት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

አቶ ነብዩ ደስታ ለጌሻ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የፕረንተር ማሽንን ድጋፍ አደረጉ። በወረዳው ኢንቨትመንት ስራዎች የተሰማሩት ባለሀብቱ አቶ ነብዩ ደስታ በግምት ከሰማኒያ ሺ ብር በላይ የሚያወጣ የ...
27/08/2026

አቶ ነብዩ ደስታ ለጌሻ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የፕረንተር ማሽንን ድጋፍ አደረጉ።

በወረዳው ኢንቨትመንት ስራዎች የተሰማሩት ባለሀብቱ አቶ ነብዩ ደስታ በግምት ከሰማኒያ ሺ ብር በላይ የሚያወጣ የፕሪንተር ማሽንን ለጌሻ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ድጋፍ አደረጉ።

አቶ ነብዩ ደስታ በግምት ከሰማኒያ ሺ ብር በላይ የሚያወጣ ፕሪንተር ማሽን በስፍራዉ ተገኝተዉ ለጌሻ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ረ/ኢ ሀብታሙ ዓለማየሁ አስረክበዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የጌሻ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር ሀብታሙ አለማየሁ እንደተናገሩት ማሽኑ የተቋሙን ስራ ጫና የሚያቃልልና ለህብረተሰቡ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ተናግሮ ድጋፉን ላበረከቱት ባለሀብት ምስጋና አቅርበዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

የጌሻ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤትና አራቱ ማዘጋጃ ቤቶች የ2018 ዓ.ም ስራ አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ዙርያ የግምገማ መድረክ ተካሄደ። በግምገማ መድረኩ ላይ የመክፈቻ ...
26/08/2026

የጌሻ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤትና አራቱ ማዘጋጃ ቤቶች የ2018 ዓ.ም ስራ አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ዙርያ የግምገማ መድረክ ተካሄደ።

በግምገማ መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጌሻ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሻሮ ሀ/ማርያም እንዳነሱት በዋናነት በህዝብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት ሰጥተው የሚሰራ በመሆኑና የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይኖርብናል ብለዋል።

አያይዘውም በከተሞቻችን ላይ የተለያዩ መሠረተ ልማት ስራዎችን ለማሳለጥ በመንግስት አቅም ብቻ የሚሳካ እንዳልሆነ የተናገሩት አቶ ሻሮ በእጃችን ያለውን የህዝብ ጉልበት ፣ገንዘብና እውቀትን በአግባቡ በመጠቀም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተለያዩ መሰረተ ልማት ስራዎችን መስራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

የከተማ መሬት ዝግጅትና ፕላን ትግበራን በሚመለከት ልዩ ትኩረት ሰጥተው በመስራት ስታንዳርዱን የጠበቀ ከተማ መመስረት ይኖርብናል ያሉት ኃላፊ ከተማን ምቹና ማራኪ ለማድረግ ውበት የሚሰጡ ችግኞችን መትከልና የማዘጋጃ ቤት ገቢ አሰባሰብ ዙርያ ላይ ከምንም ጊዜ በላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥተው ይሰራል ነው ያሉት።

ከዝህ ጋር ተያይዞ የህብረተሰብን ጤንነት ከመጠበቅ አኳያ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው በመስራት ከተማውን ጽዱና ማራኪ ማድረግ ይገባል ስሉ ተናግረዋ።

መድረኩን በጋራ በመሆን የመሩት የጌሻ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ ፈቀደ ደምሴ በበኩላቸው እንዳነሱት ሁሉም ባለድርሻ አካላት መንግስት በዘረጋው አሰራር ስርዓትን ተከትሎ የኮሪደር ስራዎችን በቁርጠኝነት ማስፈፀምን ጨምሮ በመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ የሚታየዉን ክፍተቶችን በማረም ከተሞችን በሁሉም ተግባር ፊት የወጣ ተወዳዳሪ ዉብና ማራኪ ለዜጎች ምቹ የማድረግ ስራ ትኩረት የሚሻና ሊጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።

አክለውም አቶ ፈቀደ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከመቸዉም ጊዜ በላይ ባለድርሻ አካላት ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤትና ማዘጋጃ ቤቶች ሪፖርት ከማድረግ ጀምሮ የመረጃ መረብ ሊዘረጋና በቅንጅት መመራትና መተግበር እንደሚያስፈልግ አንስተው እያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት በዕቅዱ መሠረት መፈፀምና ተቋሙን ፊት ማዉጣት በዕቅድ አፈፃፀም መሰረት መገምገምና አስፈላጊውን ምዘና ማግኘት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች፣ የማዘጋጃ ቤት ባለሙያዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በመድረኩ ላይ የተሳተፉ ስሆን የግምገማው ሰነድ ቀርቦ የተነሱትን ጉድለቶች ለማረምና በጥንካሬ የተነሱትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ለቀጣይ የጋራ አቅጣጫ ተይዘው የ2019 ዓ.ም ዕቅድ የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

በጌሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የእስካሁን የመንግስትና ፓርቲ ስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሄደ። የግምገማ መድረኩን የመሩት የጌሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አ...
26/08/2026

በጌሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የእስካሁን የመንግስትና ፓርቲ ስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሄደ።

የግምገማ መድረኩን የመሩት የጌሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አንድሰዉ አለማየሁ እንደተናገሩት በየደረጃ ያሉ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችም ሆኑ ሌሎች ባለድርሻ አካላት የህዝባችንን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ወቅቱን በመገንዘብ የመንግስትና ፓርቲን አቅጣጫ በመከተል ለህዝባችን ተጠቃሚነት ቅድምያ በመስጠት እስከ ታችኛው መዋቅር አደረጃጀቶችን በማጠናከር በቅንጅት መስራት ጊዜ የማይሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

መድረኩ ትኩረት ያደረገውም በፓርቲውና በመንግስት በኩል በተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ላይ፣ በቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚገቡ አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት በቀጣይም ሁሉም አመራሮች የተቀናጀ አሰራርን በማጠናከር ከሌሎችም ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ወቅታዊና መደበኛ ተግባራትን በውጤታማነት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

በመቀጠልም በወረዳው ነባራዊ የፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ በህዝብና ባለድርሻ አካላት ቅንጅትና ከፍተኛ እርብርብ ተስፋ ሰጪ ጅምር ዉጤቶች እንዳሉና እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች መኖራቸዉን ጠቅሰዉ አሁንም አስፈላጊው ክትትል ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።

አያይዘዉም አቶ አንድሰዉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የግብርና ስራን በቴክኖሎጂ ማዘመንና ማስፋፋት በትምህርት ዘርፍ ተማሪዎች በሙላት ትምህርት ቀርበዉ እንዲመዘገቡና በተቀመጠዉ ጊዜ ትምህርታቸዉን ጀምሮ እንዲከታተሉ አስፈላጊዉን ድጋፍና ክትትል ማድረግ በሌሎችም የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከመመለስ ጀምሮ ህዝባችን ቆጥሮ የሰጠንን ሀላፊነት በታማኝነትና በቁርጠኝነት መወጣት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የጌሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ፖ/ህ/ግ ሀላፊ ወ/ሮ ህብረት ተካ በበኩላቸው እንደተናገሩት የመንግስትና የፓርቲያችን ተግባራትን በውጤታማነት ለማስቀጠል እቅዶችን በባለቤትነት መምራት እንደሚያስፈልግ የጠቆሙ ሲሆን፣ አመራሩ ከልማዳዊ አሰራር በመውጣት ሁሉንም ተግባራት አስተሳስሮ በቅንጅት በመምራት ከመቼውም ጊዜ በላይ በንቃት መስራት እንዳለበት በማሳሰብ አመራሩ ወቅታዊና መደበኛ ተግባራትን በተገቢው በመምራት የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

አክለውም ወ/ሮ ህብረት ከፓርቲያችን ኢኒሼቲቭ ስራዎች አንዱ የሆነዉ ሰዉ ተኮር የበጎ አገልግሎት ስራ መርሐግብር በወረዳዉ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑን አንስቶ ይህ ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥልና በወረዳዉ በተለያዩ አከባቢዎች የሚገኙትን ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ልቀጥል ይገባል ብለዋል።

ከዝህ ጋር ተያይዞ በክረምት በጎ አገልግሎት ስራ መርሐግብር በየትምህርት ቤቱ የሚገኙትን አቅመ ደካማ ተማሪዎችን ለይቶ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ለአቅመ ደካማ ቤተሰቦች ቤት የማደስና መገንባት በጤና ጣቢያ ለሚገኙ ነፍሰ ጡር እናቶች ምግብ ማቅረብ ወጣቶችን ሴቶችን ሌሎችም በማስተባበር የወንዝ ድልድይ ስራ ሌሎችም አያሌ የድጋፍ ስራዎች በክረምት በጎ ስራ መርሐግብር እየተሰሩ መሆናቸዉን አንስተዉ ተግባሩ በተሻለ እንዲቀጥል በአፅንኦት ተናግረዋል።

በመድረኩ ላይም የወረዳው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በሙሉ በተገኙበት በነባራዊ ሁኔታ፣ በተግባር አፈጻጸም እና በቅንጅታዊ አሰራር ዙሪያ በጥልቀት የተገመገመ ስሆን በመጨረሻም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በጉድለት የተነሱትን ለማሻሻልና በጥንካሬ የተገመገሙትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ለቀጣይ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የየጋራ አቅጣጫ ተይዘዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064824279218
📌በቲክቶክ https://tiktok.com/
📌በቴሌግራም https://t.me/GW_communicationlink2025
📌በዋትስአፕ https://chat.whatsapp.com/FzBtziS1ViPKt6bnnEZ3lp

🙏ዘውትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዘገባው:-የጌሻ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

Address

Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gesha Woreda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gesha Woreda Communication:

Shortcuts

Share