Bonga Town Communications

Bonga Town Communications Here we provide updated governmental and public news and information to any concerned body.

01/06/2026
እስካሁን ባለው የምርጫው ሂደት ያልተገባ የሰብዓዊ መብት አያያዝ አለመመልከቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ።ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ እያካሄደች ትገኛለች። በምርጫው ሂደ...
01/06/2026

እስካሁን ባለው የምርጫው ሂደት ያልተገባ የሰብዓዊ መብት አያያዝ አለመመልከቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ።

ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ እያካሄደች ትገኛለች።

በምርጫው ሂደት የመራጮች የሰብዓዊ መብት አያያዝን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሀገሪቱ የተለያዩ ከተሞች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ መታዘብ ቅኝት እያደረገ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ የተመራው የኮሚሽኑ ቡድን በአርባምንጭና በጅማ ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ መታዘብ አድርጓል።

በምርጫ መታዘቡ ላይ ኤንቢሲ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፥ ኮሚሽኑ ባደረገው ቅኝት፥
መራጮች ለመምረጥ አስቻይ የምርጫ ጣቢያዎች የተመቻቹበት ፣ ወንዶች፣ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች በተመቻቸ የምርጫ ጣቢያዎች እየመረጡ የሚገኙበት ሁኔታ መኖሩንን ገልጸዋል።

የምርጫው መስፈርቶችን ያሟላ የምርጫ ሂደትን መታዘቡንም ተናግዋል።

ኮምሽኑ በትዝብቱ የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊና ምንም መስተጓጎሎች ያልታዩበትና የጠቀሱት ኮሚሽነሩ፥ እስካሁን ባለው የምርጫው ሂደት ያልተገባ የሰብዓዊ መብት አያያዝ አለመመልከቱን አብራርተዋል።

የምርጫው ታዛቢዎች እና መራጩ ዜጋ በሰዓቱ በምርጫ ጣቢያው በመገኘት ምርጫውን ከ ጥዋቱ 12:00 ጀምሮ እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ፥ ምርጫው ህብረተሰቡ ለቀጣይ አምስት አመታት የሚመራውን አካል በድምጹ የሚያረጋግጥበት በመሆኑ እንደሀገር ለመምረጥ የተመዘገበው ከ 54 ሚሊየን በላይ ህዝብ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በመምረጥ ህገመንግስታዊ መብቱን እንዲጠቀም ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ኮሚሽኑ ከትግራይ ክልል በስተቀር ምርጫው በሚካሄድባቸው በሁሉም አካባቢዎች በአጠቃላይ በ175 የምርጫ ክልሎችና ከ 2700 በላይ የምርጫ ጣቢያዎች የመታዘብ ስራውን እያከናወነ እንደሚገኝም ዋና ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

በምርጫ ሂደቱ ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ በመከታተልና በድህረ ምርጫ የሚኖረውንም ሂደት በአግባቡ በመምራት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

በምርጫ ሂደቱ ቅሬታዎችን ለማስተናገጃ በተዘጋጀው የቅሬታ መከታተያ ስርዓትም የምርጫውን ሂደት እየተከታተለ መሆኑንም አመላክተዋል።

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ ድምፅ ሰጡየቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ በዛሬው ዕለት በተካሄደው ምር...
01/06/2026

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ ድምፅ ሰጡ

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ በዛሬው ዕለት በተካሄደው ምርጫ ተገኝተው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

​ኃላፊው ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ በሰጡት መግለጫ፤ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች በማለዳ ተነስተው በነቂስ በመውጣት መምረጣቸው የከተማዋንና የሀገሪቱን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ያለውን ከፍተኛ ፍላጎትና ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

​አቶ ፍሬው አክለውም፤ የምርጫው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ስነ-ስርዓትን የተከተለ እንዲሆነ ገልፀዋል።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ 👉 https://www.facebook.com/BTGCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

የእውነተኛ  ቁርጠኝነት ማሳያ!አሊ መሀመድ ሀሙድ የአፋር ክልል፣ ዞን አምስት፣ ሰሙሮቢ ወረዳ ነዋሪ ናቸው። በሀሞና ሀማር ጌራ ቀበሌ ኮማሚ ምርጫ ጣቢያ ድምፃቸውን በአፋቸው ሰጥተዋል። ግለሰቡ...
01/06/2026

የእውነተኛ ቁርጠኝነት ማሳያ!

አሊ መሀመድ ሀሙድ የአፋር ክልል፣ ዞን አምስት፣ ሰሙሮቢ ወረዳ ነዋሪ ናቸው። በሀሞና ሀማር ጌራ ቀበሌ ኮማሚ ምርጫ ጣቢያ ድምፃቸውን በአፋቸው ሰጥተዋል። ግለሰቡ እጆቹን መጠቀም አለመቻሉ ሳይበግረው፣ በከፍተኛ ጥረት ጎንበስ ብሎ በአፉ የድምፅ መስጫ ወረቀቱን በምርጫ ሳጥኑ ውስጥ ሲያስገባ ይታያል። በአጠገቡ የቆመው የምርጫ አስፈጻሚም ይህንን ታላቅ የዜግነት ግዴታ የመወጣት የጽናት ታሪክ በአክብሮትና በትዕግስት ይመለከታል።

ይህ አንድ ምስል ተራ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን እጅግ ጥልቅ የሆነ የዜግነት ቁርጠኝነትን ያመላክታል። የአካል ጉዳተኝነትም ሆነ ማንኛውም ዓይነት ፈተና የራሱን አሻራ ከማሳረፍና የዜግነት መብቱን ከመጠቀም ሊያግደው አልቻለም።

የግለሰቡ ድምፅ ትልቅ ዋጋ እንዳለው ጠንቅቆ ያውቃል፤ ምርጫው እንዲቆጠርለትና ድምጹ እንዲሰማ ማንኛውንም መሰናክል ለመሻገር ቆርጦ ተነስቷል።
በማኅበረሰባችን ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆንና የወደፊት ዕድላችንን በራሳችን መወሰን በቀላሉ የሚታይ ሳይሆን፣ በብዙ ቁርጠኝነት የሚገኝ ትልቅ ዕድል መሆኑን የሚያረጋግጥ የዘመናችን ቆራጥ ግለሰብ ነው።

ኢትዮጵያ የራሷን የዴሞክራሲ ባህል እየገነባች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ ዕለት ዜጎቿ አካል ሀዘን፣ ጉዳተኝነት፣ ህመምና ሌሎች አስቸጋሪ ሁኔታ ሳይበግራቸው አሻራቸውን እያኖሩ ለዴሞክራሲ ስርዓት መገንባት ያላቸውን መሻት እያስመሰከሩ ይገኛሉ።

ምርጫው ለአንድ ሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ዜጎች በተሰጣቸው ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅሞ የሚጠቅማቸውን መንግስት መምረጥ አለባቸው፦ አቶ ታከለ ታምሩ! የአዲያ-ካካ ምርጫ ክልል የ...
01/06/2026

ምርጫው ለአንድ ሀገር የሚኖረው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ዜጎች በተሰጣቸው ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅሞ የሚጠቅማቸውን መንግስት መምረጥ አለባቸው፦ አቶ ታከለ ታምሩ!

የአዲያ-ካካ ምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እጩ ተወካይ አቶ ታከለ ታምሩ ምርጫ ለአንድ ሀገር የሚኖረው ሁለንተናዊ ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ዜጎች የተሰጣቸውን ህገመንግስታዊ መብት ተጠቅሞ ነገ የሚመራቸውን መንግስት መምረጥ እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እጩ ተወካይ የተከበሩ አቶ ታከለ ታምሩ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ላይ ተገኝተው ድምፅ በሰጡበት ወቅት እንዳሉት ምርጫ በመንግስት ምስረታ ላይ የሚኖረው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ዜጎች በተሰጣቸው ዲሞክራሲያዊ መብት መሰረት የሚበጃቸውን መንግስት መምረጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በምርጫ ክልሉ በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ላይ እየተከናወነ እንዳለ ያነሱት አቶ ታከለ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ መራጩ ህዝብ ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆም የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ ግዴታ እንዲወጡ ጠይቀዋል።

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩት የፓን አፍሪካ ፓርላማ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ ( ዶ/ር  ) በሚወዳደሩበት ምርጫ ...
01/06/2026

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩት የፓን አፍሪካ ፓርላማ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ ( ዶ/ር ) በሚወዳደሩበት ምርጫ ክልል በመገኘት ድምፅ ሰጡ::

ዶክተር አሸብር ምርጫው በእስካሁን ሂደቱ ሰላማዊ መሆኑን ተናግረው ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ እየሰጠ በመሆኑ በውጤቱ ስኬታማ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል ::

ዶክተር አሸብር አክለው ማንም ቢያሸንፍ ትልቁ ነገር ኢትዮጵያ ማሸነፏ ነው ብለው ሂደቱ ሕዝቡን የሚጠቅም እና ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርግ መሆን እንዳለበት አንስተዋል::

በርካታ ታላላቅ ድሎችን ባስመዘገብንበት ማግስት መሆኑ የዘንድሮን ምርጫ ልዩ ያደርገዋል ያሉት ዶክተር አሸብር ኢትዮጵያ ገናና ስም ይዛ ጠንክራ በታየችበት ሰዓት የሚካሄድ ምርጫ መሆኑ ይበልጥ ልዩ ያደርገዋል ነው ያሉት።
#ካፋ ቲቪ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሕይወት አሰግድ በሚወዳደሩበት ምርጫ ክልል ድምፅ ሰጡ።ምርጫው እስካሁን ከነበሩት የምርጫ ሂደቶች በተሻለ እየተካሄደ መሆኑን ተ...
01/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሕይወት አሰግድ በሚወዳደሩበት ምርጫ ክልል ድምፅ ሰጡ።

ምርጫው እስካሁን ከነበሩት የምርጫ ሂደቶች በተሻለ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ ምርጫ ሴቶች በነቂስ ወጥተው ይበጀናል የሚሉትን ለመምረጥ የተዘጋጁበት ሁነት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

መራጩ ህዝብ በጊዜ ወጥቶ በመምረጥ ሀገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ድምጽ ሰጡበ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ብልጽግና ፓርቲን ...
01/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ድምጽ ሰጡ

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ብልጽግና ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩት አቶ ማስረሻ በላቸው በምርጫ ክልላቸው ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ማስረሻ ድምፃቸውን የሰጡት በቢጣ ወረዳ ቢጣ-ገነት ከተማ ምርጫ ጣቢያ "ለ" በመገኘት ነው፡፡

በክልሉ ምርጫው ፍፁም ነፃ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ዜጎች ይበጀናል የሚሉትን ፓርቲ በነቂስ ወጥተው እንዲመርጡም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ምርጫ የህዝብ የበላይነት የሚረጋገጥበትና ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ውጤቱ ይፋ እስኪሆን ድረስ ዜጎች ሰላማቸውን ጠብቀው የድምጽ መስጠት መርሃ-ግብሩ እንዲጠናቀቅ ጠይቀዋል፡፡

በሌላ በኩል የቦንጋ ከተማ ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ(ዶ/ር)፣ በምርጫ ክልሉ ብልጽግና ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩ ሲሆን በምርጫ ጣቢያቸው ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል፡፡

ዜጎች በሌሊት በመውጣት የሚበጃቸውን እየመረጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ .4

የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ደመላሽ ንጉሤ በሚወዳደሩበት ዋቻ ምርጫ ክልል ተገኝተው ድምፅ ሰጡ፤ምርጫውን በሰላም አጠናቆ ውጤቱን ለመቀበል መዘጋጀት እንደሚገባም አቶ ደመላሽ ተናግረዋል፡...
01/06/2026

የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ደመላሽ ንጉሤ በሚወዳደሩበት ዋቻ ምርጫ ክልል ተገኝተው ድምፅ ሰጡ፤

ምርጫውን በሰላም አጠናቆ ውጤቱን ለመቀበል መዘጋጀት እንደሚገባም አቶ ደመላሽ ተናግረዋል፡፡

በዚህ ምርጫ ክልል 6 የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው እየተፎካከሩ ነው።

አቶ ደመላሽ የሚወዳደሩበት በምርጫ ጣቢያ እስካሁን ባለው ሂደቱ ሰላማዊ ፣ ነፃ እና ታአማኒ ሆኖ በመካሄድ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል።

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ ድምፃቸውን ለመስጠት በምርጫ ጣቢያ ተገኝተዋል።​አቶ ፍሬው አበበ በማለዳው በምርጫ ጣቢያው የተገኙ ሲሆን፥ እንደማን...
01/06/2026

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ ድምፃቸውን ለመስጠት በምርጫ ጣቢያ ተገኝተዋል።

​አቶ ፍሬው አበበ በማለዳው በምርጫ ጣቢያው የተገኙ ሲሆን፥ እንደማንኛውም ዜጋ ሰልፍ በመያዝ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ተራቸውን እየጠበቁ ይገኛሉ።

በቦንጋ ከተማ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች ጠዋት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ድምፅ ለመስጠት በነቂስ ወጥቶ በሰላማዊ ሁኔታ ሰልፍ ይዞ እየተጠባበቀ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

የከተማው አስተዳደር የምርጫው ሂደት በሰላም፣ በዲሞክራሲያዊና በነፃነት እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት በሙሉ መደረጉንና ሂደቱም በሰላም እየተከናወነ መሆኑን አስታውቋል።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ 👉 https://www.facebook.com/BTGCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

Address

Bonga Town
Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bonga Town Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share