Bonga Town Communications

Bonga Town Communications Here we provide updated governmental and public news and information to any concerned body.

ባለፉት ለውጥ ዓመታት በኢኮኖሚ ፣ በማህበራዊ ፣ በአስተዳደር እንዲሁም በፖለቲካ ዘርፍ የሚጨበጥ እና የሚታይ ዘርፈ ብዙ አዳዲስ ነገሮች ተመዝግቧል።አቶ ጋዎ አባመጫቦንጋ፦ነሐሴ ፣27/2018 ...
02/09/2026

ባለፉት ለውጥ ዓመታት በኢኮኖሚ ፣ በማህበራዊ ፣ በአስተዳደር እንዲሁም በፖለቲካ ዘርፍ የሚጨበጥ እና የሚታይ ዘርፈ ብዙ አዳዲስ ነገሮች ተመዝግቧል።አቶ ጋዎ አባመጫ

ቦንጋ፦ነሐሴ ፣27/2018 ዓ.ም (የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ /ቤት)

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም ማጠቃለያ ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

የማጠቃለያ ግምገማ መድረኩን የመሩት የካፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጋዎ አባመጫ ባለፈው በጀት ዓመት የታዩ ጉድለቶችን በማረም ህዝብ የሰጣቸውን አደራዎች ውጤታማ ተግባር በመፈፀም ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣት ያስፈልጋል ብለዋል።

የ2018 ዓ.ም አፈፃፀም ችግሮችን ለይተው መፍትሔ በመስጠት ጥንካሬዎችን በማስቀጠል መሻገር እና ማሻገር የሚችል አመራር መገንባት የመድረኩ ዋና ዓላማ መሆኑን አስረድተዋል።

ባለፉት ለውጥ ዓመታት በኢኮኖሚ ፣ በማህበራዊ ፣ በአስተዳደር ዘርፍ እንዲሁም በፖለቲካ የሚጨበጥ እና የሚታይ ዘርፈ ብዙ አዳዲስ ነገሮች አዳዲስ ነገሮች የታዩበት እና የተመዘገቡ መሆናቸውን ነው የተናገሩት አቶ ጋዎ አባመጫ ።

ሁለት የምርጫ መንትያ ግቦችን በማሳካት ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫን ዴሞክራሲያዊ እና በህዝብ ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ ስኬታማ መሆን ተችሏል ብለዋል።

የግምገማ እና የምዘና መድረኩ በተዋረድ ከክልል ጀምሮ እየተካሄደ መምጣቱን ያስታወሱት አቶ ጋዎ አመራር በተግባር እና በአመለካከት አንድ ሆነው በመንግሥት እና በፓርቲ የሚሰጡ ተልዕኮዎችን ስኬታማ እንዲሆን የአመራር ማጥራትና ለተግባር ማዘጋጀት ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።

የምዘና እና ግምገማ መድረኩን የካፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጋዎ አባመጫ እና የዞኑ ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ መቅደስ ማሞ እየመሩት ይገኛሉ።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ ?Bonga Town Government Communication Affairs OfficeCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

በቲክቶክ 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uW0x6Jb0CL&_r=1

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

በቦንጋ ከተማ አስተዳደር የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ ማሽቃሮ በዓል ለማክበር ቅድመ ዝግጅት ስራ በሰፊ እየተሰራ ነው። የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊና የ...
01/09/2026

በቦንጋ ከተማ አስተዳደር የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ ማሽቃሮ በዓል ለማክበር ቅድመ ዝግጅት ስራ በሰፊ እየተሰራ ነው።

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊና የማሽቃሮ ባሮ የቦታ ዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ፀጋዬ ሞላ በበኩላቸው የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ "ማሽቃሬ ባሮ " ለማክበር በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን በማሳተፍ ከተማዋን የማስዋብ ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በዚህም የአስፓልት ማፀዳት ፣ አደባባዮችን እና ቀለም የሚያስፈልጉ ቦታዎች ላይ የመቀባት ስራን እያከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

"ለማሽቃሬ ባሮ" የከተማዋ ነዎረዎች በመተባበርና በጋራ በመሆን አካባቢያቸውን በማሳመር በዓሉን በድምቀት ለማክበር ከወዲህ የቅድመ ዝግጅት ስራ ማጠናቀቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ንግድ ቤቶች በዓሉን አስመልክቶ በንግድ ቦታቸው የካፋን ባህል የሚገልፁ አልባሳት ከመጠቀም ጀምሮ ባህላዊ የምግብና የመጣጥ አቅርቦትም ላይ መዘጋጀት እንዳለባቸውም አክለዋል።

በስራ ላይ ያነጋገርናቸው ወጣት ካሰች ኬሮ እና እንዳሻው ካሳሁን በበኩላቸው "ማሽቃሮ" በዓል የማንነት መግለጫ በመሆኑ ለበዓሉ ቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ መሳተፍ የሁሉም ነው ብለዋል።

የበዓል ዝግጅት ስራ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀው ለሎች ወጣቶችም በበጎ ስራ በመሳተፍ በዓሉን በጋራ በመሆን በሰላም ተከብሮ እንዲውል የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በተጨማሪ የቦንጋ ከተማ ዘርፍ ምክር ቤት በጎ ፍቃደኛ ወጣት አስማማው አብረሃም የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ ማሽቃሬ ባሮን ሁሉም በተነሳሽነት በጋራ በመሆን ወደ ከተማዋን ለሚመጡ እንግዶች ውብና ማራኪ የማድረግ ስራ እንዲያጠናክሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወጣት አስማማው አክለውም የከተማዋ ነዋሪዎች ሁሉ በዓሉን በሰላም ለማክበር የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ ?Bonga Town Government Communication Affairs OfficeCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

በቲክቶክ 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uW0x6Jb0CL&_r=1

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

"የ21ኛው ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኅብረ-ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና ለኢኮኖሚ ዕድገታችን ጉልህ አበርክቶ ይኖረዋል" — አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገርየኢ...
01/09/2026

"የ21ኛው ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኅብረ-ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር ለዘላቂ ሰላም እና ለኢኮኖሚ ዕድገታችን ጉልህ አበርክቶ ይኖረዋል" — አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የበዓሉ አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አገኘሁ ተሻገር በ21ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ላቅ ያለ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤት እንዲመዘገብ ከወዲሁ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገለጹ።

አፈ ጉባኤው እንዳመለከቱት በዓሉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ባህልና ልምዳቸውን በመለዋወጥ ኅብረ-ብሔራዊና ዲሞክራሲያዊ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ እንዲሁም ለሀገራችን ዘላቂ ሰላምና ዘርፈ-ብዙ የኢኮኖሚ እድገት በጋራ እንዲቆሙ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

በዓሉ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ተጠናቅቆ አዲስ መንግሥት በተመሰረተበት፣ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት መሠረት በተጣለበት እንዲሁም የዲሞክራሲ ባህልን የሚያጎለብቱ በርካታ አገራዊ ሁነቶች በተከናወኑበት ማግሥት የሚከበር በመሆኑ የተለየ ትርጉምና ገጽታ ይኖረዋል።

የገዳ ሥርዓትን ጨምሮ የበርካታ ታሪካዊና ባህላዊ ሀብቶች ባለቤት በሆነችው ታሪካዊቷ የጅማ ከተማ በሚካሄደው በዚህ በዓል፣ የሕዝቦች ወንድማማችነትና አብሮነት ከፍ ብሎ እንደሚንፀባረቅ ተጠቅሷል።

በዚሁ የምክክር መድረክ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የመንግሥታት ግንኙነት፣ የዲሞክራሲያዊ አንድነትና የሕገመንግሥት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ወ/ሮ ባንቺይርጋ መለሰ የበዓሉን ረቂቅ መሪ ዕቅድ አቅርበው ጥልቅ ውይይት እንደተደረገበት ከምክር ቤቴ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

የባህል ልብሳችን መድመቂያችን ነው ፤ ማሽቃሮ የካፋ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ነው። የማሽቃሮ በዓል ዘንድሮም በድምቀት ይከበራል ፤ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ወጪ ያላችሁ የካፋ ልጆች ፣ የ...
01/09/2026

የባህል ልብሳችን መድመቂያችን ነው ፤ ማሽቃሮ የካፋ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ነው።

የማሽቃሮ በዓል ዘንድሮም በድምቀት ይከበራል ፤ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ወጪ ያላችሁ የካፋ ልጆች ፣ የካፋ ተወላጆች እንዲሁም የካፋ ወዳጆች በልዩ ድምቀት የሚረከበውን የማሽቃሬ ባሮ ዕለት ቦንጋ በመገኘት እንድትታደሙ መልዕክታችን ነው።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ ?Bonga Town Government Communication Affairs OfficeCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

በቲክቶክ 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uW0x6Jb0CL&_r=1

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የካፋ ዞን የአመራር ግምገማ እና ምዘና መድረክ ተጠናቋል።በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ተገኝቶ ሀሳብ የሰጡት የክልሉ ደን፣ አከባቢ ጥበቃና የአየር ንብ...
31/08/2026

ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የካፋ ዞን የአመራር ግምገማ እና ምዘና መድረክ ተጠናቋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ተገኝቶ ሀሳብ የሰጡት የክልሉ ደን፣ አከባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ሀላፊ ኢንጅነር አስራት ገ/ማርያም (ዶ/ር) በዚህ በሦስት ቀን ቆይታ ጊዜ ውስጥ ለቀጣይ ተልዕኮ ለአመራር ስምሪት ለመስጠት የሚያስችል ከፍተኛ ግብዓት የተሰበሰበት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል ።

ዞኑን የተሻለ ደረጃ ላይ ማድረስ የሚችልና ለዚህ አከባቢ የሚመጥን የአመራር ስምሪት መስጠትና ለተልዕኮ ዝግጁ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል ።

በግምገማ ወቅት በጉድለት የተገመገሙ ነጥቦችን በመለየት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን መስራት እንደሚያስፈልግና በማዴያ አከባቢ የሚታየው የመልካም አስተዳደር ችግር መታረም እንዳለበትም አክለዋል ።

ከማህበራዊ ሚዲያ አኳያ አመራሩ ፌክ አካውንትን በመታገል ራሱን ነጻ ማውጣት እንዳለበት እንጂነር አስራት ገ/ማርያም (ዶ/ር) ተናግረዋል ።

በአጠቃላይ በጉድለት የተነሱ ነጥቦችን ሁሉም ተቋማቶች ከሰራተኞቻቸው ጋር የጋራ በማድረግ ጉድለቶችን የዕቅድ አካል በማድረግ መስራት እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።

በማጠቃለያው መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ወሃ፣ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸውና በድክመት የተገመገሙ ተቋማት መታረም እንዳለባቸው የተገመገመ መሆኑን ተናግረዋል ።

በግምገማ ወቅት ጎልቶ የወጡ ነጥቦች መለየታቸውን ጠቅሰው በተመሳሳይ ውድቀት ተከታታይ የተገመገሙና ከችግራቸው መውጣት ያልቻሉ ተቋማት ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ተናግረዋል ።

ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን አካባቢ የግንባታ ፍቃድ አሰጣጥ ላይ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበትና በማደያዎች ላይ ነዳጅ በአግባቡ ከመጠቀም አንጻር የሚታየው ችግር መታረም እንዳለበት ተናግረዋል ።

ህገወጥነትን በማስወገድ ኑሮ ውድነትን ከማረጋጋት አኳያ የሚታየው ችግር መታረም እንዳለበት ኢንጂነር በየነ አክለዋል ።

ከመንገድና ትራንስፖርት አንጻር የህዝብ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የሆነው ትርፍና ታርፍ ላይ የሚታየው ችግር መስተካከል እንዳለበት አክለዋል ።

በየተቋሙ የተነሱ ጉድለቶችን በመወያየትና በማቀድ ጉድለቶችን ማረም እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል ።

የመድረኩ ተሳታፊ አመራሮች በበኩላቸው፤ በየደረጃው የሚነሱ የህዝብ መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በህዝብ ፍላጐት መሠረት የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት አቅደው መፍታት እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል ።

በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በትኩረት መሰራት እንዳለበትና ስራ የማማረጥ ባህልን ለመቅረፍ ለወጣቶች የስዕብና ግንባታ ስራ መሰራት እንዳለበት ተነስቷል ።

ጠንካራ የፓርቲና የመንግሥት ተቋማት በመገንባት በበጀት ዓመቱ የታቀዱ የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን በተሻለ ለመፈጸም ቁርጠኛ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።

የሚዲያ ተቋማትን አጠናክሮ ከመምራት አንጻር ያለው ጉድለትና ትክክለኛ መረጃን ለህዝብ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ የሚታየው ክፍተቶች መስተካከል እንዳለባቸውም አንስተዋል ።

ተሳታፊዎቹ አክለውም መድረኩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ጉድለቶችን ፈጥኖ ለማረምና የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም በጥልቀት በመፈተሽ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ትልቅ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል ።
Kaffa Zone Prosperity Party ዘግቧል

ተቋማት የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ተግባራዊነት ላይ ትኩረት ሰጥተው በመስራት ውጤታማ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀየካፋ ዞን ፕላን መምሪያ በቦንጋ ከተማ ፕላን ጽ/ቤት ድጋፍ እና ክትትል አድር...
31/08/2026

ተቋማት የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ተግባራዊነት ላይ ትኩረት ሰጥተው በመስራት ውጤታማ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ

የካፋ ዞን ፕላን መምሪያ በቦንጋ ከተማ ፕላን ጽ/ቤት ድጋፍ እና ክትትል አድርጓል።

የከፋ ዞን ፕላን እና ልማት መምሪያ በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ፕላን ጽ/ቤት ተገኝተው የድጋፍና ክትትል ተግባር ያከናወኑ እና የቡድኑ መሪና የመምሪያው ባለሙያ አቶ ሀብታሙ መንገሻ የድጋፉ ዋነኛ ዓላማ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን መገምገም እና የ2019 እቅድ ዝግጅት በዞኑ አቅጣጫ መሰረት መዘጋጀቱን ማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሀብታሙ አክለውም በ2018 አፈጻጸም እና በ2019 እቅድ ዝግጅት ላይ አዎንታዊ እንቅስቃሴዎች መታየቱን ገልፀው በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ክፍተቶች በ2019 መታረም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ተቋማት የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ተግባራዊነት ላይ ትኩረት ሰጥተው በመስራት ውጤታማ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ድጋፍና ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም የጠቆሙት አቶ ሀብታሙ ጽ/ቤቱ በተለያዩ ጽ/ቤቶች መደረግ ያለበትን የስራ ክትትልና ድጋፍ ማጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል።

የቦንጋ ከተማ ፕላን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የማታወርቅ ደምሴ ጽ/ቤቱ ተቋማት ባቀዱት እቅድ መሰረት ስራቸውን እየሰሩ መሆኑን መገምገም ፣ አቅጣጫ ማስቀመጥ ፣ ካፒታል ፕሮጀክቶችን መከታተልና መደገፍ ኃላፊነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

በተያያዘም በከተማ አስተዳደሩ ስር ያሉ ተቋማት የሚያቅዷቸውን እቅዶች ከፕላን ጽ/ቤቱ ጋር አስተጋብረው መተግበር እንዳለባቸው አብራርተዋል።

በመጨረሻም አቶ ሀብታሙም በበኩላቸው በካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ በጊዜ ገደብና በጥራት ተሰርተው እንዲጠናቀቅ ጥብቅ ክትትል ማድረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ ?Bonga Town Government Communication Affairs OfficeCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

በቲክቶክ 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uW0x6Jb0CL&_r=1

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

31/08/2026

የቦንጋ ከተማ ኮሪደር ልማት ለከተማዋ ሁሉን አቀፍ መሻሻል የጎላ አስተዋጸኦን እያበረከተ ይገኛል።

በልማት ሥራውም የኅብረተሰቡ ተሳትፎ እየጎጎለበተ መጥቷል።

የከተማ አስተዳደሩም ለውጡን ይበልጥ ለማስፋፋት የተቀናጀ ጥረት እያደረገ ስለመሆኑም አመላክቷል።

የካፋ ሰርከስና ጅምናስቲክ ማሰልጠኛ በቦንጋ ከተማ ሻቴራሻ ጌሮ አዳራሽ የሰርከስ ፌስቲቫል አካሄደ ቦንጋ፦ነሐሴ ፣24/2018 ዓ.ም (የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ...
30/08/2026

የካፋ ሰርከስና ጅምናስቲክ ማሰልጠኛ በቦንጋ ከተማ ሻቴራሻ ጌሮ አዳራሽ የሰርከስ ፌስቲቫል አካሄደ

ቦንጋ፦ነሐሴ ፣24/2018 ዓ.ም (የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ /ቤት)

​የካፋ ሰርከስ ማሰልጠኛ ተቋሙ ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 18 ዓመታት በዘርፉ አሰልጥኖ ሲያስመርቅ ቆይቷል።

በፌስቲቫሉ የተገኙት የካፋ ዞን ባህል ቱርዝም መምሪያ ተወካይ አቶ አብይ ዘውዴ ካፋ ሰርከስ ማሰልጠኛ ለ18 ተካታታይ ዓመታት በከተማው ሰፊ እየሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

ወጣቶች በሁሉም ስፖርት ዘርፎች መሳተፊ እንዳለባቸውና ስፖርት የፍቅርና የአንድነት መሰረት መሆኑን በማወቅ ከተለያዩ አልባሌ ቦታዎች ባለመዋል ስፖርትን በማዞተር ጤንነታቸውን በመጠበቅ እራሳቸውን ማብቃት እንዳለባቸው ገልጽዋል።

ልጆችን በመመልመል ወደ ስፖርት አካዳሚ እንዲቀላቀሉ ዞኑ ሰፊ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ በማብራራት ህብረተሰቡም የአደባባይ የጋራ ስፖርቶችን በመስራት ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች እራሱን መከላከል አለበት ብለዋል።

በፌስቲቫሉ ያገኘናቸው አቶ ደነቀ አባድጋ እና አቶ ሱለማን በርታ በበኩላቸው ወጣቶች ከቀለም ትምህርት ባሻገር በስፖርቱ እራሳቸውን በማጎልበት ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው መክረዋል።

ወጣቶች ከዕለት ተዕለት ተግባራቸው ጎን ለጎን ስፖርት መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

በስነምግባር የታነጹ በስፖርት የተደገፉ ልጆችን ማፊራት ተገቢ በመሆኑ ለስፖርት የሚያስፈልገውን ድጋፍ በማድረግ ስፖርት ቤቶችን መደገፍና ማስፋፋት ያስፈልጋል ብለዋል ።

ሰርከስና ጅምናስቲክ ትርዕት ካሳዩት ውስጥ ወጣት ምናየው አንበሴ እና ሬድኤት ሙርሰፋ በበኩላቸው በማሳዩት ትርዒት ደስተኛ መሆናቸውን በመግለፅ ስፖርቱን መከታተላቸው ከአልባሌ ቦታ ታድጎናል ብለዋል።

ወጣቶቹ ስፖርቱን በመከታተል ሀገራቸውን በስፖርት ዘርፍ ፊት የወጣ ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል ።

የካፋ ሰርከስና ጅምናስትክ አሰልጣኝ እንዳልካቸው ጌታቸው (ሩዝ)በሰጠው አስተያየት ስፖርት ጤንነታችንን የሚንጠብቅበት ዋነኛውና እና የመጀመሪያ ህክምና መሆኑን አስረድተዋል።

የስፖርት ዘርፍ በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ነገሮች እየተደገፈ እንዳለ ጠቁመው ስፖርት ቤቱን ለማሰራት ድጋፍ ያደረጉትን አካላት በማመስገን ሌሎቹም የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

የተለያዩ የሰርከስና ጅምናስትክ ትርዕቶችን በማሳየት በስፖርቱ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የተለያዩ ስፖርት አስልጣኞችና ለሌሎች አካላት የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።

ቦንጋ ከተማን በጋራ እናልማ ❗️

✍ተጨማሪ መረጃዎቸን ✍
በቴሌግራም 👉 t.me/BongatownGCAO
በፌስቡክ ?Bonga Town Government Communication Affairs OfficeCA
በቲውተር 👉 https://twitter.com/BongaTown?t=1Hfq-1TmjDHkrNlWUiPA7g&s=09 ተወዳጅተው ይከታተሉን፡፡

በቲክቶክ 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uW0x6Jb0CL&_r=1

🙏ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን🙏

30/08/2026

ደጅ ጸድቶ ፣ ማዕድ ተዘርግቶ ዘመድ አዝማድና ጎረቤት ተሰብስቦ የሚበላበት እና የሚጠጣበት አውድማ ሁልጊዜም ፍቅርን ፣ አንድነትንና አብሮነትን ያጠናክራል።

የኢትዮጵያ የከተማና ገጠር አስደናቂ የልማት ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን ተምሳሌታዊ ተግባር ነው።የኢትዮጵያ የከተማና ገጠር አስደናቂ የልማት ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት...
30/08/2026

የኢትዮጵያ የከተማና ገጠር አስደናቂ የልማት ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን ተምሳሌታዊ ተግባር ነው።

የኢትዮጵያ የከተማና ገጠር አስደናቂ የልማት ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ተሞክሮ የሚሆን ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑን የአህጉር አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ገልጸዋል።

በአፍሪካ ሕብረት ልማት ኤጀንሲ የግብርናና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ዋና ፕሮግራም ባለሙያ ክሌመንት አድጆርሎሎ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በከተሞችና መሠረተ ልማት ግንባታ አስደናቂ ለውጥ አስመዝግባለች።

አዲስ አበባን ለመጀመሪያ ጊዜ ያዩት እ.ኤ.አ. በ1999 እንደነበር በማስታወስ፣ አሁን ከተማዋ በአስደናቂ የለውጥ ስኬት ውስጥ እየተጓዘች መሆኗን ገልጸዋል።

የመዲናዋ የልማት ስኬትና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በርካታ የበረራ መዳረሻዎች አዲስ አበባን የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል በማድረግ ለቱሪዝምና አገልግሎት ዘርፍ ወሳኝ የኢኮኖሚ አቅም መፍጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የከተማና ገጠር አስደናቂ የልማት ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ተሞክሮ የሚሆን ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑንም አንስተዋል።

በአጀንዳ 2063 የቀጣናዊ ስትራቴጂክ ትንተናና እውቀት ድጋፍ ሰጪ ሥርዓት ዲፓርትመንት ኃላፊ ፖል ጉቲጋ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ የከተማ ልማት ኢንቨስትመንት አስደናቂ ውጤት አምጥቷል ብለዋል።

የአፍሪካ ከተሞችን ሁለንተናዊ ለውጥ በውጤታማ አፈጻጸም መምራት ከተቻለ የአህጉሪቷን ዕድገትና ብልፅግና በማሳለጥ፣ የኢኮኖሚ መነቃቃትና አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ከተሞቿን በማስዋብ የፈጠረችው ጠንካራ የከተሜነትና ምቹ የኢንቨስትመንት አቅም ለአፍሪካ ሀገራት ከተሞች ጭምር በልምድና ተሞክሮነት የሚወሰድ አስደናቂ ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም ለከተማና ገጠር ውጤታማ ሽግግር በቀላል ዋጋ የማይተመን አካታች የልማት አቅጣጫ እንደሚሆን አንስተዋል።

በዑጋንዳ ግብርና፣ የእንስሳት ኢንዱስትሪና ዓሳ ሀብት ሚኒስቴር የምግብና የሥነ ምግብ ዋስትና ረዳት ኮሚሽነር አሌክስ ባምቦና በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ተሞክሮ ለሁላችንም የሚተርፍ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር፣ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም እየገነባች ለመሆኗ ማሳያ መሆናቸውንም ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧነው።

Address

Bonga Town
Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bonga Town Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share