Bita Woreda Communication

Bita Woreda Communication የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለተወጡ አካላት የቢጣ ወረዳ ምስጋና አቀረበ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡በካፋ ዞን ከሚገኙ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አንዱ የቢጣ ጌ...
02/06/2026

ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለተወጡ አካላት የቢጣ ወረዳ ምስጋና አቀረበ

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡

በካፋ ዞን ከሚገኙ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አንዱ የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ሲሆን በምርጫ ክልሉ ሰላማዊ የሆነ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ተከናውኖ ተጠናቋል፡፡

የቢጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ፣ በወረዳው ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡

ዜጎች ያሳዩት ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው ፣ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም መቻላቸውንም ነው ያብራሩት፡፡

ከምርጫ ማግስት ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች ወደሥራቸው የተመለሱ መሆናቸውን ተናግረው፣ ሌሎች ዜጎችም መደበኛ የዕለት ተዕለት ህይወታቸውን ማስቀጠላቸውን አብራርተዋል፡፡

በወረዳው ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን የተወጡ የፀጥታ አካላትንና ሁሉንም ነዋሪዎች አመስግነዋል፡፡

በቀጣይ የሚመለከተው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ የሚያደርገውን የምርጫ ውጤት በፀጋ መቀበል እንደሚገባም ነው የመከሩት፡፡

በቢጣ ወረዳ በቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት ይፋ እያደረጉ ሲሆን ህዝቡም ውጤቱን እየተመለከተው ይገኛል ።ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻ...
02/06/2026

በቢጣ ወረዳ በቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት ይፋ እያደረጉ ሲሆን ህዝቡም ውጤቱን እየተመለከተው ይገኛል ።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን

"ምርጫው በሰላም በመጠናቀቁ ደስታ ተሰምቶናል" : የቢጣ-ገነት ከተማ ነዋሪዎችበካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በቢጣ ወረዳ ቢጣ-ገነት ከተማ ያነጋገርናቸው ቄሲስ ማሞ ደያስ፣ ወይዘሮ አይናለም...
02/06/2026

"ምርጫው በሰላም በመጠናቀቁ ደስታ ተሰምቶናል" : የቢጣ-ገነት ከተማ ነዋሪዎች

በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በቢጣ ወረዳ ቢጣ-ገነት ከተማ ያነጋገርናቸው ቄሲስ ማሞ ደያስ፣ ወይዘሮ አይናለም ዘውዴ እና አቶ አየለ አለሙ፣ ምርጫው በሰላም በመጠናቀቁ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ ተመራጩ አካል ትኩረቱን ወደ ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና መሠረተ ልማት ገንባታ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

በተጨማሪም ለሀገር ሰላም ቅድሚያ ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ በጋራ ሀገርን መገንባት ከምንም በላይ ወሳኝ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡

የምርጫው ውጤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ እስኪሆን ድረስ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆኑ ዜጎች በትዕግስት እንዲጠባበቁ መክረዋል፡፡

ሁሉም ፓርቲዎች ይፋ የሚሆነውን ውጤት በፀጋ ለመቀበል ራሳቸውን እንዲያዘጋጁም ነው ያሳሰቡት፡፡

በቀጣይ ለኢትዮጵያ የሰላም፣ የዴሞክራሲ እና የአንደነት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል መራጮች ፍፁም ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ድምፃቸውን መስጠታቸውን ምርጫ ክልሉ አስታውቋል፡፡የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ እስራኤል አለማየሁ፣ በምርጫ ክልሉ በሚ...
02/06/2026

በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል መራጮች ፍፁም ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ድምፃቸውን መስጠታቸውን ምርጫ ክልሉ አስታውቋል፡፡

የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ እስራኤል አለማየሁ፣ በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 110 የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች ድምፃቸውን ሰጥተዋል ብለዋል፡፡

በሁሉም ጣቢያዎች ድምጽ የመስጠት ሂደቱ ተጠናቅቆ ወደ ድምጽ ቆጠራ መገባቱን ተናግረዋል፡፡

የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ፍፁም ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ እንደነበር ጠቁመው ዜጎች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን መጠቀማቸውን ነው የተናገሩት፡፡

በዚህም በምርጫ ክልሉ የተከሰተ ምንም አይነት ችግር ያለመኖሩን አስታውቀዋል፡፡

ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና የተወጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የፀጥታ አካላትን አመስግነዋል፡፡

ኢትዮጵያ መርጣለች!

"በካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ምርጫው በሰላም ተጠናቋል" :- የቢጣ ወረዳ ፖሊስ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው ዕለት ተካሂዶ ውሏል፡፡በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በቢጣ ማዕከል ዜጎች ሰላማዊ በሆነ...
02/06/2026

"በካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ምርጫው በሰላም ተጠናቋል" :- የቢጣ ወረዳ ፖሊስ

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው ዕለት ተካሂዶ ውሏል፡፡

በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በቢጣ ማዕከል ዜጎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ድምፃቸውን ሰጥተው ውለዋል፡፡

የቢጣ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር አየነሁ አበበ፣ በወረዳው ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ በሰላም ተጠናቋል ብለዋል፡፡

ፖሊስ ከቁሳቁስ ስርጭት ጀምሮ እስከ ድምጽ መስጠት የበኩሉን ሚና መወጣቱን ገልጸው፣ በማግስቱም ድምፁ ወደ ምርጫ ክልሉ እስኪመለስ ሥራውን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን የተወጡ የህብረተሰብ ክፍሎችንና የፀጥታ አካላትን አመስግነዋል፡፡

ኢትዮጵያ መርጣለች!

01/06/2026
01/06/2026
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደት ተራዘመየድምፅ መስጠት ሒደቱ ከ12 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡በዛሬው ዕለት ...
01/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደት ተራዘመ

የድምፅ መስጠት ሒደቱ ከ12 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡

በዛሬው ዕለት ከጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ በመውጣት ድምጹን እየሰጠ ይገኛል፡፡

በብልጽግና ፓርቲ የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ አፈወርቅ አለሙ በቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በምርጫ ጣቢያ "ለ" ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል።ህብረተሰቡ መብቱን ተጠቅሞ በቀሩት ሰዓታት ቀጣይ ...
01/06/2026

በብልጽግና ፓርቲ የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ አፈወርቅ አለሙ በቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል በምርጫ ጣቢያ "ለ" ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል።

ህብረተሰቡ መብቱን ተጠቅሞ በቀሩት ሰዓታት ቀጣይ መንግስቱን ሊመርጥ እንደሚገባ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ አፈወርቅ እኔም በተመዘገብኩበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት መርጫለሁ ብለዋል።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን

Address

Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bita Woreda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share