02/06/2026
ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ለተወጡ አካላት የቢጣ ወረዳ ምስጋና አቀረበ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡
በካፋ ዞን ከሚገኙ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አንዱ የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ሲሆን በምርጫ ክልሉ ሰላማዊ የሆነ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ተከናውኖ ተጠናቋል፡፡
የቢጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ፣ በወረዳው ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
ዜጎች ያሳዩት ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው ፣ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን መጠቀም መቻላቸውንም ነው ያብራሩት፡፡
ከምርጫ ማግስት ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች ወደሥራቸው የተመለሱ መሆናቸውን ተናግረው፣ ሌሎች ዜጎችም መደበኛ የዕለት ተዕለት ህይወታቸውን ማስቀጠላቸውን አብራርተዋል፡፡
በወረዳው ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን የተወጡ የፀጥታ አካላትንና ሁሉንም ነዋሪዎች አመስግነዋል፡፡
በቀጣይ የሚመለከተው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ የሚያደርገውን የምርጫ ውጤት በፀጋ መቀበል እንደሚገባም ነው የመከሩት፡፡