Bita Woreda Communication

Bita Woreda Communication የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የቆዳና ሌጦ ምርት ብክነትን ለመቀነስ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የቢጣ ወረዳ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀየጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ነፃነት ወንድሙ እንደገለፁት በወረዳው ከ...
03/09/2026

የቆዳና ሌጦ ምርት ብክነትን ለመቀነስ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የቢጣ ወረዳ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ

የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ነፃነት ወንድሙ እንደገለፁት በወረዳው ከዚህ ቀደም በዘርፉ የተሰማራ ነጋዴ ባለመኖሩ ምክንያት የቆዳና ሌጦ ምርት በየቦታው ሲባክንና የአካባቢን ንፅህና ሲበክል መቆየቱን አስታውሰዋል።

ይህንን ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት የወረዳው ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ነው ኃላፊው የጠቀሱት።

አቶ ነፃነት እንዳመለከቱት፣ ከዚህ ቀደም ያጋጥም የነበረውን የምርት ብክነትና የአካባቢ ብክለት የሚያስቀር አዲስ እድል በመፈጠሩ በዘርፉ ለመሰማራት ፈቃደኛ ለሆነ ነጋዴ ምርቱን በማቅረብ ህብረተሰቡ ተጨማሪ ገቢ ከማግኘት ባሻገር የአካባቢውን ንፅህና እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።

በወረዳው በቆዳና ሌጦ ንግድ ዘርፍ የተሰማሩት ባለሀብትና ነጋዴ አቶ ቆጭቶ ወልደጊዮርጊስ እንደገለጹት፣ አሁን ላይ ምርቱን በስፋት ለመረከብና ለገበያ ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ህብረተሰቡ የሚያመርተውን የቆዳና ሌጦ ምርት ያለስጋት እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም የቆዳና ሌጦ ምርት ጥራቱን ጠብቆ እንዲቆይና እንዳይበላሽ ለማድረግ የጨው አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ፣ የሚመለከተው አካል አስፈላጊውን የጨው አቅርቦት እንዲያመቻችላቸው ባለሀብቱ ጥሪ አቅርበዋል።

በባለሀብቱ በኩል የተጠየቀውን የጨው አቅርቦት ከሚመለከታቸው ጋር በመነጋገር የመፍትሔ እርምጃ እንደሚወሰድ ጽ/ቤቱ አመላክቷል።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
03/09/2026

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች

ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”

ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

02/09/2026
በቢጣ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ እየተካሄደ ይገኛልየግምገማው መድረክ በወረዳው የመንግስትና ፓርቲ ዕቅዶችንና ኢኒሼቲቮችን በተጨባጭ የመፈፀም አቅም...
02/09/2026

በቢጣ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

የግምገማው መድረክ በወረዳው የመንግስትና ፓርቲ ዕቅዶችንና ኢኒሼቲቮችን በተጨባጭ የመፈፀም አቅምን በማጎልበት በሀገራችን ኢኮኖሚ ላይ አዎንታዊ አበርክቶ ያለው ስለመሆኑ ተጠቁሟል።

የወረዳውን እምቅ የልማት አቅም ወደ ተጨባጭ ሀብት ለመቀየር የተዘጋጁ ስትራተጂካዊ ዕቅዶችን ከማስፈጸም አንፃር የሚስተዋሉ ጠንካራ ጎኖችን የማስቀጠል እንዲሁም ውስንነቶች ላይ የእርምት እርምጃዎችን መውሰድ የሚያስችል መድረክ መሆኑ ነው የተጠቆመው።

የወረዳው አመራር አላማ ተኮርና ልማትን በተገቢው መንገድ ማሳለጥ እንዲችል መሰል የግምገማ መድረኮች ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል።

መድረኩን የካፋ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አክሊሉ አሰፋ እና የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ መሸሻ እየመሩት የሚገኝ ሲሆን የወረዳው የስራ አስፈፃሚዎችና አጠቃላይ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛል።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

የማሽቃሬ ባሮ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ከማጠናከሩ ባለፈ የካፋን ባህልና የቱሪዝም ሀብቶች ለአለም ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የሚፈጥር ነው፦ አቶ ዳግማዊ ማሞበካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ለሚከበረው ...
01/09/2026

የማሽቃሬ ባሮ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ከማጠናከሩ ባለፈ የካፋን ባህልና የቱሪዝም ሀብቶች ለአለም ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የሚፈጥር ነው፦ አቶ ዳግማዊ ማሞ

በካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ለሚከበረው የ2019 ዓ.ም የማሽቃሬ ባሮ፥ ባህላዊና ታሪካዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት እንዲከበር የሚያስችል አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ እንዳመላከቱት፣ በዓሉ የአካባቢውን ባህላዊ እሴትና ማንነት በሚያጎላ መልኩ ለማክበር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ከአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዓሉ ካለፉት ዓመታት በተለየ ሁኔታ የባህሉን ትውፊት ሳይለቅ ለትውልድ ማስተላለፍ በሚያስችል መልኩ እንዲከናወን ዝግጅቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል ነው ያሉት።

ማሽቃሬ ባሮ በአካባቢው ህዝብ ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠውና ህብረተሰቡ አብሮነቱን፣ ባህሉንና ማንነቱን የሚያንጸባርቅበት ጥንታዊ በዓል ስለመሆኑ ዋና አስተዳዳሪው ጠቁመዋል።

የወረዳው አስተዳደር በዓሉን ለመታደም ለሚመጡ እንግዶችና ለወረዳው ነዋሪዎች ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

"እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 አመተ-ምህረት ድረስ ግብራቸውን የማይከፍሉ ግብር ከፋዮች ይቀጣሉ"፦ የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ፅህጸት ቤት ግብር ከፋዮች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ግብራቸውን...
01/09/2026

"እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 አመተ-ምህረት ድረስ ግብራቸውን የማይከፍሉ ግብር ከፋዮች ይቀጣሉ"፦ የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ፅህጸት ቤት

ግብር ከፋዮች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ግብራቸውን በመክፈል ግዴታቸውን እንዲወጡ በካፋ ዞን የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት አሳሰበ።

በወረዳው 1መቶ 18 የደረጃ "ሀ" እና 9 መቶ 75 የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች እንዳሉ ከፅህፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

በተያዘው በጀት ዓመት ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ 609ሚሊዮን 611 ሺ ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ መስፍን ቆጶ ተናግረዋል።

እስካሁን ከ5ሚሊዮን 930ሺህ ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።

ዕቅዱ ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ብልጫ ያሳየ መሆኑን የጠቆሙት ሀላፊው፣ ለዚህ ስራ ስኬታማነት ደግሞ የሁሉም ህብረተሰብ ቁርጠኝነት ወሳኝ እንደሆነ አንስተዋል።

የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች መክፈያ ጊዜ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ መቅረቱን በማስታወስ፣ ግብር ከፋዮች በወቅቱ በመክፈል ከቅጣት ራሳቸውን መታደግ እንዲችሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ከነሐሴ 30 ቀን 2018 አመተ-ምህረት በኃላ ቅጣት ስለሚኖር ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር በወቅቱ በመክፈል ግዴታቸውን እንዲወጡ አቶ መስፍን አሳስበዋል።

ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ለማስቆም በወረዳው ባሉ አራቱም የማዘጋጃ ከተሞች ግብረ-ሀይል በማቋቋም እየተሰራ ነው ያሉት ኃላፊው በተያዘው በጀት ዓመት በእስካሁኑ 100 ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊ ማዕቀፍ መመለስ ተችሎል ብለዋል።

በቢጣ ወረዳ የ2019 ዓ.ም ማሽቃሬ ባሮ፥ ባህላዊ ትውፊቱን ጠብቆ እንዲከበር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የወረዳው ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ የወረዳው ባህል፣...
01/09/2026

በቢጣ ወረዳ የ2019 ዓ.ም ማሽቃሬ ባሮ፥ ባህላዊ ትውፊቱን ጠብቆ እንዲከበር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የወረዳው ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ

የወረዳው ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ ተክሌ እንደገለፁት የ2019 ዓ.ም የካፊቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ማሽቃሬ ባሮ" ባህላዊ ትዉፊቱን በጠበቀ መልኩ በደማቅ ስነ ስርዓቶች ለማክበር በቂ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በቅድመ ዝግጅቱም የባህል መንደሩን ከማስዋብ ጀምሮ በዓሉ በደማቅ ባህላዊ ክዋኔዎች ደምቆ እንዲውል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ ኃላፊው አብራርተዋል።

በያዝነው አመት የበዓሉ አከባበር በዩኔስኮ እንዲመዘገብ እየተደረገ ያለው ጥረት ዕውን እንዲሆን ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ባህላዊ አልባሳትን ከማዘጋጀት ጀምሮ በበዓሉ አከባበር በባለቤትነት ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለበት ነው አቶ ተረፈ ጥሪ ያቀረቡት።

በቀጣይ በዓሉን ከቀበሌ ጀምሮ በየመንደሩ ለትውልድ ታሪክን ማስተላለፍ በሚያስችል ሁነት እየተከበረ የሚቆይ መሆኑን በመጥቀስ፥ በወረዳ ማዕከል ሁሉም በተገኘበት በልዩ ድባብ በወረዳው ባህል መንደር የሚከበር መሆኑን አመላክተዋል።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

የቢጣ ገነት ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ አንተነህ ብርሃኑ በከተማው ለሚገኙ ለ21 አቅመ ደካማ እናቶች የሙሉ አልባሳት ድጋፍ አበረከተወጣቱ ካበረከተው የአልባሳት ድጋፍ ባሻገር የማዕድ ማጋራት ዠ...
31/08/2026

የቢጣ ገነት ከተማ ነዋሪ የሆነው አቶ አንተነህ ብርሃኑ በከተማው ለሚገኙ ለ21 አቅመ ደካማ እናቶች የሙሉ አልባሳት ድጋፍ አበረከተ

ወጣቱ ካበረከተው የአልባሳት ድጋፍ ባሻገር የማዕድ ማጋራት ዠመርሐግብርም አከናውኗል።

በድጋፍ አሰጣጡ መርሐግብር የተገኙት የወረዳው ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም ገብሬ እንደገለፁት አቶ አንተነህ ብርሃኑ በየአመቱ አቅመ ደካሞችን በየቤታቸው ተዘዋውሮ በመደገፍ ምሳሌ መሆኑ የቻለ ወጣት መሆኑን ጠቅሰዋል።

በያዝነው አመት እየተከናወነ በሚገኘው የክረምት በጎ፣ ፈቃድ አገልግሎት፥ የወጣቶች የግል ተሳትፎ ካለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ ማደጉን ኃላፊዋ ጠቁመዋል።

በቀጣይም በሚከበሩ በዓላት ወጣቱም ይሁን ሌላው የህብረተሰብ ክፍል አቅመ ደካሞችን በማቅረብና በመደገፍ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ወ/ሮ አይናለም መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/Bittaworeda
በቲክ-ቶክ ገፃችን woreda.commu
ላይ በመቀላቀል ይከታተሉን
የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

   #የካፋን ማሽቃሮ በዓል ምክኒያት በማድረግ በመ/ር አርቲስት ወስናቸው አጥናፌ እና በወጣት ድምፃዊና የፋና ላምሮት አሸናፊው ኤልያስ ገዛኸኝ የተዘጋጀ ምርጥ የካፈኛ ሙዚቃ÷
30/08/2026




#የካፋን ማሽቃሮ በዓል ምክኒያት በማድረግ በመ/ር አርቲስት ወስናቸው አጥናፌ እና በወጣት ድምፃዊና የፋና ላምሮት አሸናፊው ኤልያስ ገዛኸኝ የተዘጋጀ ምርጥ የካፈኛ ሙዚቃ÷

ጠንካራ የአመራር ስርዓት እውን በማድረግ በምርጫ ወቅት ለህዝብ ቃል የተገቡ ስራዎችን መፈጸም ያስፈልጋል ፦ ኢንጂነር አስራት ገ/ማርያም(ዶ/ር)የካፋ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ግም...
29/08/2026

ጠንካራ የአመራር ስርዓት እውን በማድረግ በምርጫ ወቅት ለህዝብ ቃል የተገቡ ስራዎችን መፈጸም ያስፈልጋል ፦ ኢንጂነር አስራት ገ/ማርያም(ዶ/ር)

የካፋ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል ።

በመድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ክልል ደን፣ አከባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር አስራት ገ/ማርያም (ዶ/ር ) ጠንካራ የአመራር ስርዓት እውን በማድረግ በምርጫ ወቅት ለህዝብ ቃል የተገቡ ስራዎችን በመፈጸም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል ።

ባለፉት ዓመታት ተልዕኮዎችን በተሻለ መልኩ በመፈጸም የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መጠነ ሰፊ ተግባራት መፈጸማቸውን ገልጸው ያልተከናወኑ ስራዎችን ከምዘና በኋላ ለይቶ መፈጸም ያስፈልጋል ብለዋል።

ለመድረኩ ለምዘና መነሻ የሆነ ሰነድ በካፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ጋዎ አባመጫ እያቀረቡ ይገኛል ።

Kaffa Zone Prosperity Party

Address

Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bita Woreda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share