30/03/2026
የቦንጋ ከተማ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ተገመገመ::
21/07/2018 ዓ.ም
ካፋ/ቦንጋ
የካፋ ዞን ሠላምና ፀጥታ ሚሊሻ መምሪያ የዞን ፖሊስ ማናጅመንት እንዲሁም የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የፖሊስ ማናጅመንት ጋር በጋራ በመሆን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ሁኔታ ያለበትን ደረጃ ገመገመ::
በመድረኩም የከተማ አስተዳደሩ አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በተለይም ህገወጥ የነዳጅ ዝዉዉርን መቆጣጠርና ከህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ምላሽ እንዲያገኙ የማድረግ ሚና ፣ የስርቆት ወንጀልን ከመቼዉም በላይ ተቀናጅቶ የመከላከል ስራን ማጠናከርና ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ በልዩ ትኩረት መሠራት ያለበት መሆኑ በመድረኩ የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች ናቸዉ፡፡
በመሆኑም የመምሪያችን ሀላፊ አቶ ክፍሌ ጋነቾ ቀጣይ በዞናችንና ከተማችን ላይ ለሚደረገዉ አገር አቀፍ ምርጫ ምንም አይነት የጸጥታ ችግር ሳይፈጠር ሠላማዊ የሆነ የምርጫ አካባቢን መፍጠር እንደሚገባን አሳስበዉ በተለይም ህብረተሰቡን ያሳተፈ የጸጥታ ማስከበር ተግባራት ከመቼዉም የበለጠ በንቃት ማከናወን አለብን በማለት በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡
የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፐክተር ዳዊት ደሳለኝ እንዳሳሰቡት በቦንጋ ከተማ ሊኖር የሚችልን የጸጥታ ሁኔታ በመተንበይ ፣ ቀድሞ በመከላከልና የአካባቢዉን ማህበረሰብ በማሳተፍ ሠላማዊ የምርጫ አካባቢን መፍጠር አለብን በማለት አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም ሁሉም የከተማችን ነዋሪዎች የከተማዋን ጸጥታ በማስጠበቁ ረገድ በመንግስትና ፖሊስ ጎን በመሆን በጋራ እንዲሠሩ መልዕክት በማስተላለፍ በከተማዉ ሲስተዋል የነበሩ ችግሮችን በመለየት በቀጣይ መሰራት ያለባቸዉን የጸጥታ ተግባራትን ላይ መግባባት በመፍጠር የዕለቱን የግምገማ መድረክ አጠናቀዋል፡፡