Gebretsadik Shawo General Hospital

Gebretsadik Shawo General Hospital KAFFA ZONE GENERAL HOSPITAL

10/09/2025

ለመላው የክልላችን ህዝቦችና ኢትዮጵያዊያን በሙሉ እንኳን ለ2018 ዓ/ም የዘመን መለወጫ በዓል በሠላም እና በጤና አደረሳችሁ !!!

‎ የ2018 ዓ/ም የዘመን መለወጫ ስናከብር የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ አገልግሎት በሰጠበት ማግስትና ኢትዮጵያችን ማንሰራራት የጀመረችበት በመሆኑ ደስታችን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል።

‎ውድ የክልላችን ህዝቦች አዲሱ ዓመት የሠላም ፣የፍቅር ፣ የጤና ፣የብልጽግና እና ያቀድነውን ሁሉ የምናሳካበት ዓመት እንዲሆንልን መልካም ምኞቴን በራሴና በደ/ምዕ/ ኢት/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ ስም እገልጻለው።

‎በጤናው ዘርፍ ማህበራዊ ብልፅግናን ለማስፈን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት፣ ፍትሃዊነት እና ጥራትን በማረጋገጥ የእናቶችንና የህጻናትን ሞት መቀነስ፣ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ዘርፈ ብዙ ተግባራት ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ ሲሆን ተግባሩም ተጠናክሮ ይቀጥላል።

‎ ፍትሐዊ የጤና አገልግሎትን ለማዳረስ የጤና መድህን አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል ከወትሮ በተለየ ስልት በ2018 ይሰራል።

‎በተለይም በክልላችን በወረርሽኝ መልክ የተከሰተውን የወባ በሽታ በአመራሩ ዘንድ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲመራ በማድረግ ውጤት እየተመዘገበ ሲሆን የክረምት ወቅት መውጣትን ተከትሎ የወባ በሽታ ሊጨምር ስለሚችል በየደረጃው የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ህዝባችን በማሳተፍ የመከ/መቆ/ ተግባር ተጠናክሮ ይሰራል።

‎ህዝባችን በበዓል ወቅት ጤናችን የሚያውኩ ከባዕድ ነገር ጋር የተቀላቀሉ የምግብ እና የምግብ ነክ ምርቶች ራሱን መጠበቅ እና በግብይት ወቅት በምርቶች ላይ ከወትሮ የተለየ ጥርጣሬ ሲኖር ለሚመለከተው አካል ጥቆማ እንዲያደርግ አሳስባለሁ።

‎በዓዲሱ ዓመት የአገሪቱን ከፍታ ለማረጋገጥ በትብብር፣በቅንጅት፣ በውጤታማነት፣በይቅርታና በምህረት የምንሰራበት ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልፃለው።

‎በድጋሚ ለመላው ኢትዮጵያውያን፣ የጤና አመራሮቻችን፣ የጤና ባለሙያዎቻችን፣ የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞቻችንና የጤናው ሴክተር ቤተሰቦች እንኳን አደረሳችሁ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንልን!!!

አቶ ‎ኢብራሂም ተማም
የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ

19/08/2025
ተቋማትን ለታማሚዎች የሚማራኪ ከማድረግ አንፃር  ጤና ሚኒስቴር በሁሉም ጤና ተቋማት  ካሽ የሚባል  initiative ማውረዱ ይታወሳል:: ስለሆነም የቦንጋ ገብረጻድቅ ጠቅላላ ሆስፒታል በኢሀክ...
11/05/2025

ተቋማትን ለታማሚዎች የሚማራኪ ከማድረግ አንፃር ጤና ሚኒስቴር በሁሉም ጤና ተቋማት ካሽ የሚባል initiative ማውረዱ ይታወሳል::
ስለሆነም የቦንጋ ገብረጻድቅ ጠቅላላ ሆስፒታል በኢሀክ 3ርድ ሳይክል ሲሸልም ከመሸለሚያ መስፈርቶች አንዱ ተቋማትን ጽዱና ለተገልጋይ ምቹ ከማድረግ አንጻር መሆኑ ይታወቃል:: ይህንንም ስራ ከማስቀጠል አንፃር አሁንም ሆስፒታላችን ሰራተኞችን ያሳተፈ የጽዳት ዘመቻ በሳምንት አንድ ቀን አራት ቀን እያካሄደ ይገኛል:: በፎቶ እይታ....

ለሁሉም ሼር በማድረግ ይህንን መረጃ አድረሱ ::
01/01/2025

ለሁሉም ሼር በማድረግ ይህንን መረጃ አድረሱ ::

 #በደ/ምዕ/ኢት/ሕ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ ባካሄደው  የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6ወር አፈፃፀም ጉባኤ በጤናዉ ዘርፍ ላበረከቱት  አስተዋፆ የተሰጠ የምስጋና ምስክር ወረቀት ጥር_201...
08/02/2024

#በደ/ምዕ/ኢት/ሕ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ ባካሄደው የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6ወር አፈፃፀም ጉባኤ በጤናዉ ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋፆ የተሰጠ የምስጋና ምስክር ወረቀት
ጥር_2016 ዓ.ም
😂😘😘

16/08/2023
15/08/2023

ክፍት የስራ ማስታወቂያ
11/08/2023

ክፍት የስራ ማስታወቂያ

ሁሉም ህብረተሰብ እና ማህበረሰብ ይህንን በመተግበር የኮሌራ በሽታን መከላከል ይችላል!!
11/08/2023

ሁሉም ህብረተሰብ እና ማህበረሰብ ይህንን በመተግበር የኮሌራ በሽታን መከላከል ይችላል!!

Share and like  this official Regional health bureau Page to get more information and vacancy
10/07/2023

Share and like this official Regional health bureau Page to get more information and vacancy

ለጤና ተቋማት መልሶ ግንባታ የሚውል የ31 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ተደረገ

የአውሮፓ ሕብረት በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ጉዳት ለደረሰባቸው የጤና ተቋማት መልሶ ማቋቋሚያ የሚውል የ31 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡

በአማራ፣ አፋር እና ትግራይ ክልሎች የሚገኙ በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን 160 የጤና ተቋማት መልሶ ለማቋቋም የሚያስችል ገንዘብ ነው ሕብረቱ ድጋፍ ያደረገው፡፡

ድጋፉም÷በዋናነት የተጎዱ ጤና ጣቢያዎችን መልሶ ለማቋቋም፣ የፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ወገኖች ማገገሚያ ማዕከላትን ለማጠናከር እንዲሁም አማራጭ የጤና አገልግሎቶች ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ይውላል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የድጋፍ ፕሮጀክቱ ÷ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖችን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማድግ እንደሚውል የሕብረቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ

በሆስፒታላችን በተፈጥሮ የከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ችግር ላለባቸው ህጻናትና ልጆች በተሰጠው የነጻ ህክምና  አገልግሎት መደሰታቸውን በቦንጋ ገ/ጻድቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል  ያነጋገርናቸው የ...
12/06/2023

በሆስፒታላችን በተፈጥሮ የከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ችግር ላለባቸው ህጻናትና ልጆች በተሰጠው የነጻ ህክምና አገልግሎት መደሰታቸውን በቦንጋ ገ/ጻድቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል ያነጋገርናቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ተናገሩ።

ትረስት የተሰኘ በጎ አድራጎት ድርጅት ከሆስፒታሉ ጋር በመተባበር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚገኙ ዞኖች ለተውጣጡ የከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ችግር ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የነጻ ህክምናውን ተደራሽ አድርጓል።

የከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ይህ ነው የተባለ ትክክለኛ ምክንያት ባይኖረውም ከዘር ወይም ከቤተሰብ ተመሳሳይ ችግር ካለ በዕርግዝና ወቅት የሚወሰዱ መድሀኒቶችና ሌሎች ለችግሩ መንስኤ እንደሆኑ ጥናቶች ያሳያሉ።

በኢትዮጵያ የላንቃ መሰንጠቅ ላጋጠማቸው ህጻናት በበቂ ሁኔታ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አለመኖራቸውና ለህክምናው ወጪ በማጣቸው ምክንያት በርካቶች ሲቸገሩ ቆይተዋል።

ትረስት የበጎ አድራጎት ድርጅትም ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ የሚደርሱ የኢኮኖሚ ና ስነ ልቦና ጫናዎችን ለማስቀረት በተለያዪ የሀገሪቱ ክፍሎች ውስጥ በመዘዋዋር በዘርፉ የህክምና አገልግሎት ከሚሰጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ነጻ የህክምና አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን የማህበሩ መስራችና ዳይሬክተር አቶ ደሴ ዳቼ ተናግረዋል።

በዚህም ከ 1ሺ 8መቶ በላይ የከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ችግር ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ህክምናውን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ያሉት ዳይሬክተሩ በቀጣይም ከአጋር ድርጅቶች ጋር በተመባበር አገልቱን በቅርበትና በስፋት ለመስጠት እንቅስቃሴዎች እያደረግን እንገኛለን ብለዋል።

የቦንጋ ገ/ጻድቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ፍቅረማርያም ጳውሎስ የተሰጠው አገልግሎት በሆስፒታሉ በመደበኛነት ይሰጡ ከነበሩ አገልግሎቶች በተለየ መልኩ የችግሩ ተጋላጮችን ተጠቃሚ ያደረገ ነው ብለዋል።

በሆስፒታሉ የነጻ ህክምና አገልግሎቱ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል ከዳውሮ ዞን የመጡት ወይዘሮ ሊያ ባሳ እና ከካፋ ዞን ሺሾንዴ ወረዳ የመጡት አቶ ወርቁ ገ/ስላሴ በሰጡት አስተያየት ድርጅቱ መሉ የትንስፖርት እና የህክምና ወጪያቸውን ሸፍኖ ለልጆቻቸው በሰጠው የህክምና አገልግሎት መደሰታቸውን ገልጸዋል ።

ከዚህ ቀደም ስለ ከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ግንዛቤው እንደሌላቸውና በህክምና የሚስተካከል መሆኑን እዳልተረዱ የገለጹት ተገልጋዮቹ ድርጅቱ ከብዙ ኢኮኖሚያዊና ስነ_ልቦናዊ ጫናዎች እንዳላቀቃቸውም ተናግረዋል።

ድርጅቱ በቀጣይ ህክምናውን በአካባቢው ለሚገኙ ሌሎች የችግሩ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሰራም ተገልጿል። ካፉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ

Address

Bonga, Kaffa
Bonga
16

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gebretsadik Shawo General Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gebretsadik Shawo General Hospital:

Share