በከተሞች የሚታየውን የሥራ አጥነት ቁጥር ለመቀነስና ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ የኢንቨስትመንት አቅምን ለማጎለበት፣ በከተሞች ልማትን ለማፋጠንና መልካም አስተዳደርን ለመገንባት፣ የንግድ ሥርዓቱን ዘመናዊ ለማድረግ ከመስከረም 2003 ዓ.ም ጀምሮ የንግድ ኢንዱስትሪ ከተማ ልማት ሴክተር ተብሎ በመጠራትና መዋቅራዊ አደረጃጀቱን እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በማድረስ ለ5 ዓመታት ያህል በከተሞች የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን አከናውኗል፡፡
በመሆኑም ሴክተሩ በመጀመሪያው ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን የተጣሉ ግቦችን ለማሳካት ሰፊ ርብርብ በማድረግ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ ችሏል፡፡
ይሁንና በሴክተሩና በስሩ በሚገኙ
ተቋማት ላይ የሚታዩ የአደረጃጀት ክፍተቶችን በመፈተሽ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን ከመጀመሪያው ምዕራፍ ጀምሮ አዲስ አደረጃጀት በአዋጅ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡
በዚህም መሠረት በቀድሞ ስሙ ን/ኢ/ከ/ል/ቢሮ ተብሎ የሚጠራው አደረጃጀት የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ፣የንግድና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ፣ እና የኢንቨስትመንት ኮሚሽን በሚል የአደረጃጀትና የመዋቅር ለውጥ ተደርጓል፡፡
ስለሆነም ይህ ጽሁፍ በዋናነት የሚዳስሰው ከጥቅምት 16/2008 ዓ.ም ጀምሮ በአዋጅ ቁጥር 161/2008 ፀድቆ ወደ ተግባር በገባው በከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ላይ ትኩረት በማድረግ መረጃውን ለአንባቢው እንዲደርስ ያደርጋል፡፡
Alerts
Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Region Urban Development and Construction Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.