የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Dafala
  • የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ኢትዮጵያ ታምርት
ኢትዮጵያ ትሸምት
(2)

📢 የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት​የምክር ቤታችንን የማህበራዊ ትስስር ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋት እንዲሁም ወቅታዊ እና ተጨባጭ መረጃዎችን ለህብረተሰቡና ለክቡራን አባላቶቻችን በ...
30/06/2026

📢 የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

​የምክር ቤታችንን የማህበራዊ ትስስር ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋት እንዲሁም ወቅታዊ እና ተጨባጭ መረጃዎችን ለህብረተሰቡና ለክቡራን አባላቶቻችን በፍጥነት ለማድረስ፤ ከፌስቡክ ገጻችን በተጨማሪ በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ ፕላትፎርሞች ዝግጅታችንን አጠናቀን ቀርበናል።

​እርስዎም ከታች ያሉትን ማስፈንጠሪያዎች (ሊንኮች) በመጠቀም የገጾቻችን ቤተሰብ እንዲሆኑና መረጃዎችን በቅርበት እንዲከታተሉ በትህትና እንጋብዛለን!

​🔗 የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን..

​ድረ-ገጽ 📌 https://afarccsa.com/auth

​ፌስቡክ 📌 https://www.facebook.com/afarccsa

​ኤክስ (ትዊተር) 📌 https://x.com/afarccsaa

​ሊንክድኢን 📌 https://linkedin.com/company/afarccsa

​ኢንስታግራም 📌 https://www.instagram.com/afar.region

​📞 ሌሎች የመገናኛ አማራጮች..

​📧 ኢሜል 📌 [email protected]
​📞 ስልክ ቁጥር 📌 +251333169290

:
:

:​

እንኳን ለ1447ኛው ታላቁ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!​“ዒድ ሙባረክ!” 🤲🌙✨​የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር ሃጂ መሐመድ ሸሂም ...
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው ታላቁ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
​“ዒድ ሙባረክ!” 🤲🌙✨

​የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር ሃጂ መሐመድ ሸሂም ሀሰን፤ ለክልላችንና ለሀገራችን ሙስሊም ማህበረሰብ፣ በተለይም ለንግዱ ማህበረሰብ አባላት በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት የሚከተለውን ጥሪና የመልካም ምኞት መልእክት አስተላልፈዋል።

​ፍትሃዊ ግብይትና ታማኝነት..በዓሉ የደስታና የመስዋዕትነት ወቅት እንደመሆኑ፣ ነጋዴው ማህበረሰብ ምርትና አገልግሎትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለህዝቡ እፎይታ እንዲሆን።

​መተሳሰብና አብሮነት...የአረፋ በዓል የእርዱ ስጋ ለተቸገሩ ወገኖች የሚከፋፈልበት በመሆኑ፣ በንግዱ ዓለምም አቅመ ደካሞችን በማሰብ አብሮነትን እንድናጠናክር።

​“ይህ የዒድ በዓል በክልላችን የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ አዲስ ተነሳሽነት የምንፈጥርበት፣ በመካከላችን ያለውን ትብብር የምናጠናክርበትና ለክልላችን ብልፅግና በጋራ የምንቆምበት እንዲሆንልን እመኛለሁ።"

​በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የብልፅግና ይሁንልን!

​🤲🌙✨ በድጋሚ ዒድ ሙባረክ! 🤲🌙✨

Qafar Rakaakayak Culenti Biirok naharsi saqal Massakaxxâ le Cajji  Awel Abdu Awel miraacisa,fayya le miraaciini abak Rag...
20/04/2026

Qafar Rakaakayak Culenti Biirok naharsi saqal Massakaxxâ le Cajji Awel Abdu Awel miraacisa,fayya le miraaciini abak Rag Tabaatabsah soomali Rakaakay Culen.

Qafar Rakaakayak Culenti Biiroh Miraaciinul Abak Raak Tabaatabsa Gexisak Geytimtah tan Butta Sheger Siitik Furih Magaala...
18/04/2026

Qafar Rakaakayak Culenti Biiroh Miraaciinul Abak Raak Tabaatabsa Gexisak Geytimtah tan Butta Sheger Siitik Furih Magaalak Baxaabaxsale Daddos Fanteenaani Kee Sekter Kutbeh Buxaaxit Gufne Aben.

Qafar Rakaakayak Culenti Biiroh Saqalaay Abak Raag Tabaatabsih Buttak Koobaahiseh Yan Massakaxxale Cajji Awwal Qabdu Awwal Miraacisah Yan Butta Sheger Siitih Magaala Culeenih Yanin Wak Sheger Siitih Magaalak Ciggiila Kantiiba Gifta Guyyo Gelgello Kee Furih Magaalak Culenti Kutbeh Buxah Saqolti Qax Meqeh Yan Garayyu Keenih Abte.

ዛሬ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ የአንድ ቀን አዲስአበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል ።በውድድሩ ላይ የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር ...
18/04/2026

ዛሬ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ የአንድ ቀን አዲስአበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል ።

በውድድሩ ላይ የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር ሃጂ መሃመድ ሸሂም እና የአፋር ክልል አትሌቲክስ ፌደሬሽን ልኡካን ቡድን ተገኝተዋል ።

Qafar Tellemmo kee Luulah Eglak Naharsi Pressident Mohammed Shacim Cassanaay Leeda Missoybak Fantti Makaadoh Adoytaa kee...
15/04/2026

Qafar Tellemmo kee Luulah Eglak Naharsi Pressident Mohammed Shacim Cassanaay Leeda Missoybak Fantti Makaadoh Adoytaa kee Samara Logyi Magaalah Xiinissok Naharsi Saqal Massakaxxale Qabdu Muusa Husseen kee

Kalah tan Baxaabaxsale Rakaakayaay Rasitte kee Daqooritik tewqeh tan Miraaciino kee Mihrat leela Edde Tengeleh tan Qafar Rakaakayak culenti Biiroh Koobaahissol amaarah Rakaakayih doolatak Culenti Biiro Luk Bahridaar Magaalal Gexisak Geytimah yan Abak Raag tabaatabsih taddeera Qaxmeqe Gurral Gexsitak Geytimta.

የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 📍

በሰመራ ከተማ በ70 ሚሊዮን ብር የተገነባው ዘመናዊ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ተመረቀ​ሰመራ — በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በ70 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የሁለተኛ ደረጃ የቁ...
31/03/2026

በሰመራ ከተማ በ70 ሚሊዮን ብር የተገነባው ዘመናዊ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ተመረቀ

​ሰመራ — በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በ70 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል፣ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አወል አርባ እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

​የዚህ ማዕከል ግንባታ መንግሥት የግብይት ሥርዓት ስብራቶችን ለመጠገንና የገበያ መሠረተ ልማት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል። ማዕከሉ የክልሉን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የሀገሪቱን የንግድና የኢኮኖሚ ምሰሶ በማጠናከር ረገድ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።

​የፕሮጀክቱ ስፋት፦ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት በመላ ሀገሪቱ እየተገነቡ ካሉት 1,950 የቀዳሚና እሁድ የገበያ ማዕከላት በተጨማሪ፣ በ1 ቢሊዮን ብር በጀት በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች እየተገነቡ ካሉ 10 ተመሳሳይ የሁለተኛ ደረጃ ማዕከላት መካከል አንዱ ነው።

​የኤክስፖርት ስኬት፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ባለፉት 8 ወራት ብቻ ከእንስሳት ሀብት 39 ሚሊዮን ዶላር ተገኝቷል።

​አጠቃላይ አፈጻጸም፦ በጠቅላላ የኤክስፖርት ንግድ የታቀደውን 116% በማሳካት 6.76 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል።

​ይህ አዲስ ማዕከል የአካባቢውን የእንስሳት ሀብት ለገበያ በማቅረብ ረገድ የሚታዩ የጥራትና የደረጃ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል

የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

 #እንኳን ለ1447 የዒድ አል-ፈጥር እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ​“ዒድ ሙባረክ!”   🤲🌙✨​የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ መሐ...
19/03/2026

#እንኳን ለ1447 የዒድ አል-ፈጥር እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

​“ዒድ ሙባረክ!”
🤲🌙✨

​የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ መሐመድ ሸሂም ሀሰን ለክልላችንና ለሀገራችን ሙስሊም ማህበረሰብ፣ በተለይም ለንግዱ ማህበረሰብ አባላት በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት የሚከተለውን የሥራ መመሪያና የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል።

​ለንግዱ ማህበረሰብ የተላለፈ ጥሪ....

​ክቡር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ፕሬዝዳንቱ በበዓሉ ሰሞን የንግዱ ማህበረሰብ ሊያሳየው የሚገባውን ማህበራዊ ኃላፊነት አስመልክቶ የሚከተሉትን ነጥቦች አጽንኦት ሰጥተዋል።

​ፍትሃዊ ግብይት፦ በዓሉ የደስታና የመረዳዳት ወቅት እንደመሆኑ፣ ነጋዴው ማህበረሰብ ምርትና አገልግሎትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለህዝቡ እፎይታ እንዲሆን።
​የታማኝነት ስነ-ምግባር፦ የንግድ ስራን ከትርፍ በላይ በታማኝነትና በታታሪነት በማከናወን፣ የክልላችንን የንግድ እንቅስቃሴ ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ።

​አብሮነትና መረዳዳት፦ በረመዳን የታየው የመረዳዳትና የመደጋገፍ እሴት በንግዱ ዓለምም ተጠናክሮ እንዲቀጥልና አቅመ ደካማ ወገኖችን በማሰብ በዓሉን በጋራ እንድናከብር።

​''የዘንድሮው የዒድ በዓል በክልላችን የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ አዲስ ተነሳሽነት የምንፈጥርበት፣ በመካከላችን ያለውን ትብብር የምናጠናክርበትና ለክልላችን ብልፅግና በጋራ የምንቆምበት እንዲሆንልን እመኛለሁ።"

ክቡር አቶ መሐመድ ሸሂም ሀሰን
የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕረዚዳንት

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የብልፅግና ይሁንልን!

🤲🌙✨​በድጋሚ ዒድ ሙባረክ!🤲🌙✨
:
:





በኢትዮጵያ እና በቱርክዬ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ እንዲያድግ ተስማምተናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)በኢትዮጵያ እና በቱርክዬ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ ቢያንስ ወደ ...
17/02/2026

በኢትዮጵያ እና በቱርክዬ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ እንዲያድግ ተስማምተናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በኢትዮጵያ እና በቱርክዬ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ ቢያንስ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር እና ከዚያም በላይ ማደግ እንዳለበት ከቱርክዬ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን ጋር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የገለጹት በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ከሚገኙት የቱርክዬ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን ጋር በሰጡት የጋራ መግለጫ ነው።

በመግለጫቸውም፥ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ልውውጥ ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንዲሸጋገር እና የቱርክዬ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት በማድረግ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው የአፍሪካ ገበያ እንዲሠሩ ከፕሬዚዳንት ኤርዶዋን ጋር መምከራቸውን አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምትጠብቅ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ይህን የኢኮኖሚ ዕድል ለጋራ ዕድገት መጠቀም ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ፕሬዚዳንት ኤርዶዋንን፥ የሰው ዘር እና የቡና መገኛ ወደሆነችው፤ በቅኝ ወዳልተገዛችው እና ከፍተኛ ክብር፣ ኩራት እንዲሁም የማደግ ተስፋ ወዳላት ወደ ኢትዮጵያ "እንኳን ደኅና መጡ" ብለዋቸዋል።

በተጨማሪም ፕሬዚዳንት ኤርዶዋን በደቡብ አፍሪካ በነበረው የቡድን 20 ስብሰባ ወቅት የተደረገላቸውን ግብዣ አክብረው ኢትዮጵያን በመጎብኘታቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በለሚ ታደሰ

Address

Semera
Dafala
7220

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአፋር ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት:

Shortcuts

Share