02/06/2026
የጃናሞራ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ የሠው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ሰራተኞች የዲጅታል ምዝገባ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን አስታወቀ።
ግንቦት 25/2018 ዓ.ም
የመንግስት ሰራተኞችን ፐርሶኔል መረጃ ማጥራትና ማረጋገጥ |ቆጠራ|ስራ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት ይዞ እየሰራ መሆኑን ጽ/ቤቱ አስታውቋል።
የ/ቤቱ ሃላፊ አቶ አማረ ታደሰ እንደገለጹት የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ ወደ ዲጅታል በማሸጋገር የሰራተኛውን ጥቅም ለማስከበር እና የመረጃ አያያዙን ለማዘመን ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
ከግንቦት ወር መጀመሪያ ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኘው የመንግስት ሰራተኞች የአካል ቆጠራ ተግባር እስከ አሁን 12 ያክል ተቋማት ሰራተኞችን መረጃ የማጥራት ስራ መከናወን መቻሉን ሃላፊው ገልፀዋል።
ከፖሊስ አባላት ውጭ ያሉ በወረዳው ያሉ የሁሉም ተቋማት በቋሚነት እና ህጋዊ ውል ወስደው በኩንትራት እያገለገሉ የሚገኙ ሰራተኞች በወጣው የቆጠራ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በአካል በመገኘት ቆጠራ እንሚያካሄዱ የገለጹት አቶ አማረ የፋይዳ መታወቂያና የጽ/ቤት መታወቂያ ይዘው መገኘት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
የኔትወርክ መቆራረጥ፣ የመብራት መጥፋትና ሰራተኞች በቆጠራ ፕሮግራማቸው በወቅቱ አለመገኘት ችግሮች መስተዋላቸው ለሂደቱ ተግዳሮት ቢሆኑም ጽ/ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት ተይዞ እየተሰራ ነው ተብሏል።