Janamora Communications

Janamora  Communications የጃናሞራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የወረዳውን ህብረተሰብ የመረጃ ተጠቃሚ ማድረግ ነው።

‎የጃናሞራ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ የሠው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ሰራተኞች የዲጅታል ምዝገባ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን አስታወቀ።‎‎ግንቦት 25/2018 ዓ.ም‎የመንግስት...
02/06/2026

‎የጃናሞራ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ የሠው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ሰራተኞች የዲጅታል ምዝገባ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን አስታወቀ።

‎ግንቦት 25/2018 ዓ.ም
‎የመንግስት ሰራተኞችን ፐርሶኔል መረጃ ማጥራትና ማረጋገጥ |ቆጠራ|ስራ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት ይዞ እየሰራ መሆኑን ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

‎የ/ቤቱ ሃላፊ አቶ አማረ ታደሰ እንደገለጹት የመንግስት ሰራተኞችን መረጃ ወደ ዲጅታል በማሸጋገር የሰራተኛውን ጥቅም ለማስከበር እና የመረጃ አያያዙን ለማዘመን ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ከግንቦት ወር መጀመሪያ ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኘው የመንግስት ሰራተኞች የአካል ቆጠራ ተግባር እስከ አሁን 12 ያክል ተቋማት ሰራተኞችን መረጃ የማጥራት ስራ መከናወን መቻሉን ሃላፊው ገልፀዋል።

‎ከፖሊስ አባላት ውጭ ያሉ በወረዳው ያሉ የሁሉም ተቋማት በቋሚነት እና ህጋዊ ውል ወስደው በኩንትራት እያገለገሉ የሚገኙ ሰራተኞች በወጣው የቆጠራ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በአካል በመገኘት ቆጠራ እንሚያካሄዱ የገለጹት አቶ አማረ የፋይዳ መታወቂያና የጽ/ቤት መታወቂያ ይዘው መገኘት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

‎የኔትወርክ መቆራረጥ፣ የመብራት መጥፋትና ሰራተኞች በቆጠራ ፕሮግራማቸው በወቅቱ አለመገኘት ችግሮች መስተዋላቸው ለሂደቱ ተግዳሮት ቢሆኑም ጽ/ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት ተይዞ እየተሰራ ነው ተብሏል።

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ...
02/06/2026

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡

በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡

ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡

የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ግንቦት 25 2018፣አዲስአበባ፣ኢትዮጵያ

የድምፅ መስጫ ሰዓት እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ተራዘመ ***************************የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12:00 ሰ...
01/06/2026

የድምፅ መስጫ ሰዓት እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ተራዘመ
***************************

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በዚህም መሠረት በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) በተደነገገው መሠረት፤ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ተብሎ በመታመኑ የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ እኩለ ሌሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም የተመዘገቡ መራጮች መርጠው በተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ አሳስቧል፡፡

#የኢትዮጵያምርጫ #ምርጫ2018 #የምርጫቦርድ #ኢትዮጵያ

"በምንም ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ለሀገሬ እገኝላታለሁ" ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
01/06/2026

"በምንም ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ለሀገሬ እገኝላታለሁ"

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ቢስቲማ ምርጫ ጣቢያ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።   #በምርጫ ብቻ  electio  #ኢትዮጵያ ትመርጣለች...
01/06/2026

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ቢስቲማ ምርጫ ጣቢያ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

#በምርጫ ብቻ
electio #ኢትዮጵያ ትመርጣለች

አሚኮ

01/06/2026

‎የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ምኞታችን ነው የበኩላችንን እንወጣለን!
‎የመካነ ብርሃን ምርጫ ጣቢያ ድምፅ ለመስጠት በመጠባበቅ ላይ የተገኙ ዜጎች፤

‎"ኢትዮጵያ እየመረጠተች ነው"!

"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው"!ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ  እና ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ድምጽ ሰጡ። በባሕርዳር ከተማ ምርጫ ክልል  የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ተወካዮች ምክ...
01/06/2026

"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው"!

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ድምጽ ሰጡ።

በባሕርዳር ከተማ ምርጫ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር እና በባሕርዳር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ አረጋ ከበደ በባሕርዳር ድምጽ ሰጥተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ርእሰ መሥተዳድሩ ድምጽ የሰጡት በባሕርዳር ከተማ ግሽ ዓባይ በሚገኘው ሕዳሴ የምርጫ ጣቢያ ነው።

አሚኮ

‎"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነዉ" !‎በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የምርጫ ክልል ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከ94 ሺህ በላይ ዜጎች ተመዝግበው በ113 የድምጽ መስጫ ጣቢያ  ድምፃቸውን እየሰጡ ይ...
01/06/2026

‎"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነዉ" !
‎በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የምርጫ ክልል ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከ94 ሺህ በላይ ዜጎች ተመዝግበው በ113 የድምጽ መስጫ ጣቢያ ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

‎የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እየተካሄደ ይገኛል።

‎በጃናሞራ ወረዳ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዜጎች ይበጀኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከጥዋቱ 12 ሰዓት ጀምረው የድምጽ መስጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጫቸውን እየሰጡ ነው።
01/06/2026

‎በጃናሞራ ወረዳ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዜጎች ይበጀኛል ያሉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥ ከጥዋቱ 12 ሰዓት ጀምረው የድምጽ መስጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጫቸውን እየሰጡ ነው።

የመሬት ገፅታን መሠረት ያደረገ ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና አጠቃቀም በሚል እቅድ አልሞ አየሰራ የሚገኝው ፓክት ፕሮጀክት          ግንቦት 20/09/2018   በጃናሞራ ወረዳ ዋሰል ቀ...
28/05/2026

የመሬት ገፅታን መሠረት ያደረገ ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና አጠቃቀም በሚል እቅድ አልሞ አየሰራ የሚገኝው ፓክት ፕሮጀክት
ግንቦት 20/09/2018

በጃናሞራ ወረዳ ዋሰል ቀቤሌ በሁለት ተፋሰስ ማለትም አደይ ቆላና አማጃ ተፋሰስ879.89 ሂ/ክ የተጎዱ መሬቶች ወደነበረበት አንዲመልስ ዋናተግባር አደርጎ አየሰራ የሚገኝው አሳታፊ የግብርናና የአየር ንብረት ሽግግር/pact/ ፕሮግራም ነው ። የማህበረሰቡን አስተሳስብ ለመቀየር ማህበረሰቡን በአራት ማህበር በማደራጀት ወደ ስራ የገባ ሲሆን ከተደራጁት ማህበሮች
1, ዋሰል የገበሬወች ህብረት ስራ ማህበር
2,ታድጋለች ዋሰል የገበሬወች ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር
3,አማጃ ማህበረሰብ ተፋሰስ ልማት ተጠቃሚወች ህብረት ስራ ማህብር
4,አደይ ቆላ ማህበረሰብ ተፋሰስ ልማት ተጠቃሚወች ህብረት ስራ ማህበር ይገኙበታል።
ድርጅቱ ለአደራጃቸው ማህበሮች የልማት መርጃ መሳሪያወችን ዶማ ፣አካፋ፣መሎጊያ፣መዶሻ ፣ማረሻና ሜትር ድጋፍ እያደረገና ማህበሩ የተሻለ ገቢ እንዲኖረው እየሰራ ይገኛል።
ለሁሉም ማህበር አመራርና አባላት በበጀት የተደገፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አየሰጠ ይገኛል።
በቀጣይም ፦ለመስራት የታቀዱ ተግባራቶች
1,የንፁህ መጠጥዉሃ እና የመስኖ ግንባታ ስራ
2,የተፋሰስ ቤሮ ግንባታ
3,የግብአት መጋዝንና ለተደራጁ ማህበራት አስፈላጊ ግብአቶችን ለማሟላት አቅዶ እየሰራ ይገኛል።

Address

Writer
Debark'

Telephone

+251927564796

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Janamora Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share