02/09/2026
በሂውማን ካፒታል ኦፕሬሽን ( ) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በህፃናት ዕድገት ክትትልና ማበልፀግ ዙሪያ ለጤና ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ነሃሴ 27/2018 ዓ.ም
የጃናሞራ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት በሂውማን ካፒታል ኦፕሬሽን ዓለም ባንክ (HCO) ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ እድሜያቸው ከሁለት አመት በታች ለሆኑ ህፃናት እድገት፣ ክተትል እና ማበልፀግ (Growth Monitoring &Revitalatio / አስመልክቶ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል።
በስልጠናው የቀበሌ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችና የጤና ጣቢያዎች የስርአተ ምግብ ተጠሪዎች ተሳትፈዋል።
ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ እነደሆነም ከጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።