Temesgen Tiruneh - ተመስገን ጥሩነህ

Temesgen Tiruneh - ተመስገን ጥሩነህ Deputy Prime Minister of Ethiopia 🇪🇹

04/09/2026

የሕብረተሰብን ጤና መጠበቅ የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሕዝብ አስቻይ መሰረት ነው በሚል መርህ እና ትጋት ለሚሰራው የመደመር መንግስት፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አበርክቶ ልዩ ትርጉም አለው።

የኢትዮጵያ ጥንካሬ ከተቋሞቿ ድምር አቅም የሚመነጭ ነው።ኢትዮጵያን በጤና እና በትምህርት እያገለገለ ያለውን የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅን የሥራ እንቅስቃሴ ዛሬ ተመልክተና...
04/09/2026

የኢትዮጵያ ጥንካሬ ከተቋሞቿ ድምር አቅም የሚመነጭ ነው።

ኢትዮጵያን በጤና እና በትምህርት እያገለገለ ያለውን የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅን የሥራ እንቅስቃሴ ዛሬ ተመልክተናል።

የሆስፒታሉን ብቻ ሳይሆን የሃገራችንን የጤና ዘርፍ ወደ ከፍተኛ ምዕራፍ የሚያሸጋግረረው አኩቴክ (ACCU-TECH) ዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ለሃገራችን የዘርፉ ልዩ መለያ እና አቅም ነው። ዘመናዊው ላቦራቶሪ በአንድ ጊዜ በርካታ ሳምፕሎችን ከመቀበሉም በላይ ለተወሰነ ጊዜ ሳምፕሎችን በጥንቃቄ ለማቆየትም የሚያስችል ነው።

በተጨማሪም በትምህርት ተቋሙ የስነተዋልዶ ጤና ልህቀት ማዕከልን፣ ለታካሚ እጅግ ምቹ የሆነውን የካንሰር የጨረር ህክምና ማዕከልን እና የአገልግሎት ነጻ የጥሪ ማዕከሉን ተመልክተናል።

ተቋሙ ከሆስፒታልነት በላይ፣ የሰው ኃይል ልማትን፣ የልዩ ሕክምና አገልግሎትን፣ ምርምርንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በአንድ ላይ ያቀናጀ ሀገራዊ የጤና ተቋም መሆኑን በጉብኝታችን አረጋግጠናል።

ከመላ ኢትዮጵያ እንዲሁም አህጉራችን አፍሪካ ለሚመጡ ታካሚዎች የኩላሊት፣ የልብ እና መሰል ውስብስብ የጤና እክሎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ብቃት ባላቸው ሀኪሞቹ አክሞ በማዳን እያበረከተ ያለው ሥራ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሕክምና ልህቀት ማዕከል እና የሕክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለመሆን የጀመረችው ጉዞ ትክክለኛ መስመር ላይ መሆኑን ያሳያል።

ሆስፒታሉ ከሆስፒታል ወደ ጤና ከተማ ከኮሌጅ ወደ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርገውን የልህቀት ጉዞ አጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል።

በቀጣይም የላቀ የሕክምና አቅምን፣ ትምህርትንና ምርምርን በማጠናከር ለሌሎች የሀገር ውስጥና አህጉራዊ ተቋማት ምሳሌነቱን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።

የሕብረተሰብ ጤና ድምር ውጤቱ በተሰማራበት ዘርፍ ሁሉ ውጤታማ ተግባር የሚከውን እና ለሀገሩ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚተጋ አምራች ሕብረተሰብ  መገንባት ነው።ኢትዮጵያን ላለፉት 100 ዓመታት ያ...
04/09/2026

የሕብረተሰብ ጤና ድምር ውጤቱ በተሰማራበት ዘርፍ ሁሉ ውጤታማ ተግባር የሚከውን እና ለሀገሩ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚተጋ አምራች ሕብረተሰብ መገንባት ነው።

ኢትዮጵያን ላለፉት 100 ዓመታት ያገለገለውን፣ ታሪካዊ ወረት እና ዘመናዊ አቅምን ያጣመረውን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን የሥራ እንቅስቃሴ ዛሬ ተመልክተናል።

የሕብረተሰብን ጤና መጠበቅ ለዘላቂ ሀገራዊ ብልጽግና መሠረት ነው። ተቋሙም በወረርሽኝ ልየታ፣ በበሽታ ክትትልና ምላሽ፣ በላብራቶሪ፣ በምርምር፣ በዲጂታላይዜሽን እና በጤና ስጋት ዝግጁነት የሀገሪቱን የጤና ሥርዓት በጥንካሬ እየደገፈ ይገኛል።

በክልሎች የድንገተኛ ሕብረተሰብ ጤና አደጋ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከላትን ማቋቋሙና የሪፈራል ላብራቶሪዎችን ማስፋፋቱ የሀገሪቱን የጤና ዝግጁነት አቅም እያጠናከረ ያለ ወሳኝ ተግባር ነው።

በቀጣይም የአፍሪካ የሕብረተሰብ ጤና የልህቀት ማዕከል ለመሆን በከፍተኛ ትጋት እየሠራ ይገኛል። ከዚህ በተጨማሪም የዓለም የጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል በመሆን ዓለም አቀፍ ሚናውን ለማጠናከር ብርቱ ጥረት እያደረገ ነው።

የትላንትን ታሪክ ጠብቆ፣ ዛሬን በዘመናዊነት ዋጅቶ፣ ወደ ነገ የሚገሰግስ እንደዚህ ያለ ተቋምን መደገፍና ማጠናከር ለነገ የማንለው ተግባር ነው። ኢንስቲትዩቱ የሀገርን ብልፅግና ለማፋጠን ወሳኝ አቅም በመሆኑ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል።

03/09/2026
03/09/2026

በመደመር መንግሥት ተቋማዊ ለውጥ የሚለካው ተቋማትን ገለልተኛ፣ ዘመናዊ፣ ዲጂታላይዝድ እና ውጤታማ በማድረግ የዜጎችን ሁለንተናዊ የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል ነው። ከዚህም አኳያ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሚበረታታ ለውጥ ላይ ይገኛል።

የመደመር መንግስት የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረገ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ግልጽ በሆነ መንገድ እንዲመራ ይፈልጋል። ከዓመታት በፊት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግ...
02/09/2026

የመደመር መንግስት የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረገ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ግልጽ በሆነ መንገድ እንዲመራ ይፈልጋል።

ከዓመታት በፊት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሚሰጣቸው አገልግሎቶች የህዝብ ቅሬታ ከሚስተዋልባቸው ተቋማት ውስጥ አንዱ ነበር።

አሁን ግን ታሪክ ተቀይሯል። በዓመት የማይስተናገድ ዜጋ ጉዳዩን በቀን ውስጥ ፈፅሞ የሚመለስበት ተቋም ሆኗል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን በዲጂታል በማዘመን አገልግሎቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ እያሸጋገረ ይገኛል።

ዛሬ በአገልግሎቱ ዋና መሥሪያ ቤት ተገኝተን እንደተመለከትነው፣ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተቋማዊ ሪፎርምና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ሥራዎች የተቋሙን ስምና የሥራ ባህል በአዲስ መልክ እየቀየሩ ነው።

በተለይም አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ማሸጋገሩ ተገልጋዮች ፈጣን፣ ግልጽና እንግልትን የቀነሰ አገልግሎት እንዲያገኙና እርካታቸውም እንዲጨምር እያደረገ ይገኛል።

አገልግሎቱ በብቁ የሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ ራሱን በማደራጀት የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት፣ የቪዛ፣ የጉዞ ሰነዶች፣ ለውጭ ዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን እንዲሁም የአየርና የመሬት ድንበር ቁጥጥርን ጨምሮ በርካታ ተግባራትን በውጤታማነት እያከናወነ ነው።

እያንዳንዱ ሪፎርም የሚለካው ዜጎች በሚያገኙት የአገልግሎት ጥራት፣ በሚቆጥቡት ጊዜና በሚያገኙት እርካታ ነው። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ተቋማዊ ለውጥም መንግሥት ቀልጣፋ፣ ግልጽ፣ ተጠያቂና ዜጋ-ተኮር የሆነ የአገልግሎት ሥርዓት ለመገንባት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት ያሳያል።

በቀጣይም የተቋሙን የዲጂታል ሽግግር በማፋጠን፣ የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ጥራትን በማሳደግ፣ ተቋማዊ ዐቅሙን በማጠናከር እና የተገልጋዮችን እርካታ በተጨባጭ በማረጋገጥ ላይ መትጋት ይገባል። የተገልጋዮችን ሐሳብና ቅሬታ ራስን ለማሻሻል መነሻ አድርጎ መቁጠር ከተቻለ ከዚህም በላይ መለወጥ ይቻላል።

01/09/2026
01/09/2026

የኢትዮጵያ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ አቅም የተቀናጀ ተቋማዊ የለውጥ እርምጃም ተትቶ የቆየውን የሥራ ቦታ ወደ ማራኪ የሥራ ከባቢነት ለመቀየር አስችሎታል።

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም ያከናወናቸው ተግባራት ኢትዮጵያ አሳታፊና አካታች ልማትን እያረጋገጠች ያለች ሀገር መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው።ዛሬ የስደተኞች ተመላሾች አገልግሎት በ...
31/08/2026

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም ያከናወናቸው ተግባራት ኢትዮጵያ አሳታፊና አካታች ልማትን እያረጋገጠች ያለች ሀገር መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው።

ዛሬ የስደተኞች ተመላሾች አገልግሎት በራስ ዐቅም ያከናወነውን ውጤታማ ተቋማዊ ሪፎርም በአገልግሎቱ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ተገኝተን ተመልክተናል። ይህ ሪፎርም የሥራ ቦታን ከማሻሻል ባለፈ፣ የሥራ ባህልን፣ የአገልግሎት ጥራትንና ተቋማዊ ዐቅምን የሚያጎለብት ለውጥ ነው።

የአገልግሎቱ አመራሮች፣ ሠራተኞችና ስደተኞች በመቀናጀት በዋና መሥሪያ ቤቱ፣ በ6 ክልሎች በሚገኙ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችና በ27 መጠለያ ጣቢያዎች ያከናወኑት ሥራ፣ በራስ አቅም ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ያሳየ ጥሩ ተሞክሮ ነው።

በተለይም የመደመር መንግሥት የግብርና እመርታ ማሳያ የሆነውን የሌማት ትሩፋትን በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በዶሮና እንስሳት እርባታ፣ በንብ ማነብና በተለያዩ የዕጽዋት ልማት ዘርፎች የተጀመሩ ሥራዎች፣ ተቋማዊ ሪፎርም የሚለካው በተሻለ የሥራ አካባቢ ብቻ ሳይሆን በሚፈጥረው ምርታማነትና ውጤት ጭምር መሆኑን ያሳያሉ።

ኢትዮጵያ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ዓለም አቀፍ ስደተኞችን በመቀበል፣ መብትና ክብራቸውን በማስጠበቅ ከተቀባዩ ማኅበረሰብ ጋር በማስተሣሠር በልማት ዕድሎች ተጠቃሚ እያደረገች ነው። ስደተኞቹ የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናቸውም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፏቸውን እያሳደገ ይገኛል።

በራስ ዐቅም የሚመጣ ለውጥ የተቋምን ዐቅም ያጎለብታል፤ ይህ ደግሞ የሀገርን ዐቅም ይገነባል። በስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ያየነው ስኬታማ ጉዞ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።

31/08/2026

ባሕር ዳር የኢትዮጵያ አዲስ የልማት ጅምሮች መታያ!

በከተማዋ የተገነቡት የቱሪስት መስህቦች ባሕር ዳር ውብ ብቻ ሳትሆን ወደ ከፍተኛ የልማት ኡደት እየተሸጋገረች ለመሆኗ ማሳያዎች ናቸው።

Address

Debra Markos

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Temesgen Tiruneh - ተመስገን ጥሩነህ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Temesgen Tiruneh - ተመስገን ጥሩነህ:

Shortcuts

Share