Basocommunication

Basocommunication ባሶና ወራና ወረዳ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ ከሚገኙት 22 የገጠር ወረዳዎች አንዱ ግዙፍ ወረዳ ነው። ባሶና ወራና ወረዳ በሰሜን ሸዋ ዞን ከሚገኙት 24 የገጠር ወረዳዎች አንዷ ስትሆን በውስጧ 21 የገጠር ቀበሌዎችን ይዛለች

01/06/2026

ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዘመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዝሟል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡

ምርጫ ቦርድ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሒደት ላይ እንደነበር ጠቅሷል፡፡

ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ ውሳኔ ማሳለፉን አመልክቷል፡፡

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል።

በዚህ መሰረትም የድምጽ መስጫ ሒደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ነው ቦርዱ ያስታወቀው፡፡

የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሒደቱን እንዲያከናውኑም ቦርዱ አሳስቧል፡፡

#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያእየመረጠችነው #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል

 !‎‎በሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወረና ህዝብ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ይበጀኛል የሚለውን መንግስት ለመምረጥ  በማለዳ ተሰልፎ በሰላማዊ መንገድ ድምጹን እየሰጠ ነው።
01/06/2026

!

‎በሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወረና ህዝብ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ይበጀኛል የሚለውን መንግስት ለመምረጥ በማለዳ ተሰልፎ በሰላማዊ መንገድ ድምጹን እየሰጠ ነው።

01/06/2026
 #ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!በሰሜን ሸዋ ዞን በባሶና ወራና ወረዳ በተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች ድምፁን የሚሰጠው ህዝብ ተሰልፎ እየመረጠ ነው።
01/06/2026

#ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

በሰሜን ሸዋ ዞን በባሶና ወራና ወረዳ በተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች ድምፁን የሚሰጠው ህዝብ ተሰልፎ እየመረጠ ነው።

ድምጽ መስጠት ተጀመረ!ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ🇪🇹 !
01/06/2026

ድምጽ መስጠት ተጀመረ!
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም
ኢትዮጵያ🇪🇹
!

31/05/2026
በተሳሳተ መንገድ ጫካ ገብተው የነበሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀበሉ።‎‎በሰሜን ሸዋ ዞን አሳግርት ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች በተሳሳተ መንገድ ወደ ጫካ ገብተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ...
30/05/2026

በተሳሳተ መንገድ ጫካ ገብተው የነበሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀበሉ።

‎በሰሜን ሸዋ ዞን አሳግርት ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች በተሳሳተ መንገድ ወደ ጫካ ገብተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ገብተዋል።

‎ታጣቂዎቹ በተሳሳተ መረጃ የጽንፈኛ ቡድኑን መቀላቀላቸውን በመግለጽ በትጥቅ ትግል የሚመጣ ለውጥ አለመኖሩን በመረዳት የመንግስትን የሰላም ጥሪ መቀበላቸው ገልጸዋል።

ለህዝብ ሰላም እና ደኅንነት ቅድሚያ በመስጠት የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉት ታጣቂዎች ሌሎች ታጣቂዎችም የሰላም ጥሪውን እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የመረጃ ምንጫችን የአሳግርት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን የፊት ገፅ /የፌስቡክ ገጽ/ ነው

30/05/2026
29/05/2026
ፖሊስ ምርጫው  በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ዝግጁነት ወደ ተግባር መግባቱን ገለጸ። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም በአማራ ክልል የሚገኘው የጸጥታ ኃይል በ...
29/05/2026

ፖሊስ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ዝግጁነት ወደ ተግባር መግባቱን ገለጸ።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም በአማራ ክልል የሚገኘው የጸጥታ ኃይል በሰው ኃይልና በሎጀስቲክስ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱ ታወቀ።

የክልሉ የፖሊስ ኃይል ከመከላከያ፣ ከፌዴራልና ከሌሎች የክልሉ የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት፤ በየመንገዱ፣ በየኬላውና በየሰፈሩ በቂ የሰው ኃይል በማሰማራት ቀንና ሌሊት በትጋት እየሰራ ይገኛል።

የትራፊክ ፖሊስን ጨምሮ መላው የጸጥታ አካል የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆንና የሕዝቡ መደበኛ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል በየተሰማራበት ቦታ ውጤታማ ሥራ እያከናወነ መሆኑ ተረጋግጧል።

ሕገ-ወጥ የታጠቁ ኃይሎች በሕዝቡ ላይ ውዥንብር ለመፍጠርና እንቅስቃሴን ለማደናቀፍ የሚያስተላልፉት መረጃ መሬት ላይ የሌለና ፍጹም የሐሰት በመሆኑ ሕብረተሰቡ ሳይደናገጥ መደበኛ ተግባሩን እንዲያከናውን አሳስቧል።

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለሀብቶችና አሽከርካሪዎች የጸጥታ ኃይሉን አስተማማኝ ከላላ በመተማመን የተለመደውን የሕዝብ አገልግሎት ያለ ምንም ስጋት እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።

የጸጥታ ኃይሉ የክልሉን ሰላም ለማፍረስና ምርጫውን ለመበጥበጥ የሚሞክር የትኞቹንም ሕገ-ወጥ አካላት እንቅስቃሴ ለማክሸፍና ሕግና ሥርዓትን ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ተጠንቀቅና ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።ፖሊስ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ዝግጁነት ወደ ተግባር መግባቱን ገለጸ።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም በአማራ ክልል የሚገኘው የጸጥታ ኃይል በሰው ኃይልና በሎጀስቲክስ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱ ታወቀ።

የክልሉ የፖሊስ ኃይል ከመከላከያ፣ ከፌዴራልና ከሌሎች የክልሉ የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት፤ በየመንገዱ፣ በየኬላውና በየሰፈሩ በቂ የሰው ኃይል በማሰማራት ቀንና ሌሊት በትጋት እየሰራ ይገኛል።

የትራፊክ ፖሊስን ጨምሮ መላው የጸጥታ አካል የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆንና የሕዝቡ መደበኛ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል በየተሰማራበት ቦታ ውጤታማ ሥራ እያከናወነ መሆኑ ተረጋግጧል።

ሕገ-ወጥ የታጠቁ ኃይሎች በሕዝቡ ላይ ውዥንብር ለመፍጠርና እንቅስቃሴን ለማደናቀፍ የሚያስተላልፉት መረጃ መሬት ላይ የሌለና ፍጹም የሐሰት በመሆኑ ሕብረተሰቡ ሳይደናገጥ መደበኛ ተግባሩን እንዲያከናውን አሳስቧል።

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለሀብቶችና አሽከርካሪዎች የጸጥታ ኃይሉን አስተማማኝ ከላላ በመተማመን የተለመደውን የሕዝብ አገልግሎት ያለ ምንም ስጋት እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።

የጸጥታ ኃይሉ የክልሉን ሰላም ለማፍረስና ምርጫውን ለመበጥበጥ የሚሞክር የትኞቹንም ሕገ-ወጥ አካላት እንቅስቃሴ ለማክሸፍና ሕግና ሥርዓትን ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ተጠንቀቅና ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

Address

Debre Berhan
251

Telephone

251116813902

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Basocommunication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Basocommunication:

Share