Basocommunication

Basocommunication ባሶና ወራና ወረዳ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ ከሚገኙት 22 የገጠር ወረዳዎች አንዱ ግዙፍ ወረዳ ነው። ባሶና ወራና ወረዳ በሰሜን ሸዋ ዞን ከሚገኙት 24 የገጠር ወረዳዎች አንዷ ስትሆን በውስጧ 21 የገጠር ቀበሌዎችን ይዛለች

የወረዳው መንገድ ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት ተጨማሪ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ። #ደብረብርሃን ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ባሶና ወራና ኮሙኒኬሽን)በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወ...
03/09/2026

የወረዳው መንገድ ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት ተጨማሪ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
#ደብረብርሃን ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ባሶና ወራና ኮሙኒኬሽን)

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት ለክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በድጋሚ ግምቱ 20 ሺ ብር የሆነ 20 ደርዘን ደብተርና 1 ፓኬት እስክሪቢቶ ድጋፍ አድርጓል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ንጉሴ ፀጋዬ እንደገለፁት በጎ ፈቃድ "በጎነት ለራስ ነው"በሚል እሳቤ ከተሽከርካሪ ባለንብረቶችና ከአሽከርካሪዎች በተገኘ ገንዘብ የህዝብን አንድነትና መተባበርን የሚያጠናክር ትልቅ ተግባር መሆኑን የገለፁ ሲሆን በማህበረሰቡ ውስጥ የሚገኙ ችግረኛና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች መደገፍ በክረምት በጎ ፍቃድ ብቻ የሚተገበር ሳይሆን ቀጣይነት ኖሮት በልዩ ትኩረት ሊተገበር እንደሚገባ ተናግረዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳደሪና የትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አፈወርቅ ዘውዴ በበኩላቸው የክረምት የበጎ ፈቃድ ተግባር ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን ገልፀው ድጋፉ በችግር ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች በመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይፈናቀሉ ከማስቻሉም በላይ የእርስ በርስ መደጋገፍንና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑን ገልፀው ጽ/ቤቱን አመስግነዋል።

ለአርሶ አደሮች በፀረ ተባይ ኬሚካል አረጫጭና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱ ተገለጸ፤  #ደብረብርሃን ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም  (የባሶና ወራና ኮሙኒኬሽን)በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባ...
02/09/2026

ለአርሶ አደሮች በፀረ ተባይ ኬሚካል አረጫጭና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱ ተገለጸ፤
#ደብረብርሃን ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የባሶና ወራና ኮሙኒኬሽን)

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት የማናጅመንት አባላትና ባለሙያዎች በተገኙበት የልምድ ልውውጥ በማካሄድ በፀረ-ተባይ ኬሚካል አረጫጭና አጠቃቀም ዙሪያ ለአርሶ አደሮች ስልጠና ተሰጠ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ነገስ ወልደማሪያም ተሳታፊዎቹ ከአባሞቴና ከጉዶበረት ዙሪያ ቀበሌዎች የተወጣጡ 89 አርሶ አደሮችና ባለሙያዎች ሲሆኑ የፀረ-ተባይ ኬሚካል እርጭት፣ አልባሳትና ቁሳቁስ በማሟላት በተግባር ለመማማር በስንዴ ክላስተር ላይ በመስክ በመንቀሳቀስ ግንዛቤ መፍጠርና የኤክስቴሽን ድጋፍ ማድረግ ተችሏል። አርሶ አደሮች የኬሚካል አጠቃቀምን እዲያሻሽሉና ጤናቸውን እንዲጠብቁ በተግባር የተደገፈ ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል።

ስልጠናው በወረዳ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን፦ በፀረ-ተባይ ኬሚካል ምንነትና አይነቶች፣ የርጭት መከላከያ አልባሳት አጠቃቀም፣ አያያዝና ጥገና የሚያስከትለው ጉዳት፣ ከርጭት በፊትና በኋላ የሚወሰዱ ጥንቃቄዎችና ባህላዊ የተባይ መከላከያ ዘዴዎችን በሚመለከት ተሰጥቷል።

አርሶ አደሮቹም ስለተሰጣቸው ስልጠናና የልምድ ልውውጥ ቀደም ብሎ ግንዛቤው ስላልነበረን በሰውነታችን ላይ ጉዳት ደርሶብን ነበረ፤ አሁን በተሰጠን ስልጠና የፀረ ተባይ ኬሚካል አረጫጨትና የአልባሳት አጠቃቀም ሂደቱ ግልጽ ስለሆነልን እናመሠግናለን ብለዋል።

የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ እሱንዳለ ወግደረስ በተለያየ የሰብል አይነቶች የተዘሩ ሰርቶ ማሳያዎችን በመጎብኘት የመደገፍና በቀጣይ ሰፊ የሆነ ማህበረሰብ በማሳተፍ የገበሬ በአል እዲካሄድባቸው አስፈላጊውን ክትትል ተደርጓል። የኢሊኖ ክስተት ቢከሰት እሱን መከላከል የሚያስችል የተለያዩ እስትራክቸሮችን በመስራት የእርጥበት እቀባ ስራውን አጠናክሮ መስራት፣ ዩሪያ ማዳበርያ በአናት መጨመር በወቅቱ እንዲከወን ድጋፍ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የዞኑ ኮሙንኬሽን መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈፃፀም 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነደብረ ብርሃን፤ ነሃሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ...
02/09/2026

የዞኑ ኮሙንኬሽን መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈፃፀም 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነ

ደብረ ብርሃን፤ ነሃሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀሙ ከዞንች ተወዳድሮ 3ኛ በመውጣት ዕውቅናና ሽልማት ተቀበለ።

ሽልማቱን የተቀበሉት የዞኑ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተማለደ በላይሁን ለተገኘው የላቀ ውጤት በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ እንዲሁም አጋር አካላተ የላቀ በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሠራራት" በሚል ስያሜ ይከበራሉ። የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን ስያሜ እና አከባበር አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫው...
02/09/2026

የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሠራራት" በሚል ስያሜ ይከበራሉ።

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን ስያሜ እና አከባበር አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ደሲሳ ኢትዮጵያ ካሏት ልዩ ቀናት መካከል የጳጉሜን ቀናት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል። የጳጉሜን ወር ያለፈውን ዓመት ሥራዎቻችንን የምንገመግምበት፤ የሚቀጥለውን ዓመት ዕቅድ እና ተስፋም የምንሰንቅበት ልዩ ወር ስለመኾኑም አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ የጳጉሜን ወር ቀናትን በልዩ ስያሜ እያከበረች ነው። ይሄም ዜጎች የግል ዕቅዳቸውን ከሀገራዊ አቅጣጫ ጋር በማስተሳሰር ለሀገር ልማት የበኩላቸውን እንዲወጡ የሚያነሳሳ ነው ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታው።

በዚህ ዓመትም አምስቱም የጳጉሜን ቀናት በጋራ "የኢትዮጵያ ማንሠራራት" በሚል መሪ ቃል ይከበራሉ ነው ያሉት። ይህም በእርግጥም የኢትዮጵያን ማንሠራራት የሚያሳዩ ተጨባጭ ለውጦች የተመዘገቡበት ለመኾኑ ማሳያ ነው። ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የተጠናቀቀበት፣ ግዙፉ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ የተጀመረበት እና ሌሎችም ዐበይት ስኬቶች የተመዘገቡበት ዓመት ስለመኾኑም ለአብነት አንስተዋል።

እያንዳንዱ ቀናት የራሳቸው ስያሜ ተሰጥቷቸው የሚከበሩ ሲኾን በዚህም መሠረት፦

👉 ጳጉሜን 01፦ የእምርታ ቀን

ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ ጉዞ ተላቅቃ ወደ ፈጣን የኢኮኖሚ እምርታ ምህዋር መግባቷን የምናሳይበት ቀን ነው።

👉 ጳጉሜን 02፦የማንሠራራት ቀን
ኢትዮጵያ ወደሁለንተናዊ ከፍታ ጉዞዋን የጀመረችበት ዓመት በመኾኑ የተሰየመ ነው። ሀገራችን ከጎታች የእድገት ማነቆዎች ተላቅቃ ወደ የማንሠራራት ጉዞዋን ያፋጠነችበት ዓመት ለመኾኑም ማሳያ ነው።

👉 ጳጉሜን 03፦ የጽናት ቀን፦
ኢትዮጵያ በረጅም ታሪኳ በርካታ ፈተናዎችን አሳልፋለች፤ ነጻነት እና ሉዓላዊነቷንም በጽናት አስጠብቃ ኖራለች። ይህንን ጽናት ማስቀጠል የዛሬው ትውልድም ኀላፊነት መኾኑን ለማስገንዘብ ነው ቀኑ "የጽናት ቀን" ተብሎ የሚከበረው። በቀኑም ከጥዋቱ 12:00 ላይ በመላው ኢትዮጵያ እና በኢምባሲዎችም ጭምር በሁሉም የመንግሥት እና የግል ተቋማት የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት ምልክት የኾነውን ሰንደቅ አላማ ከፍ በማድረግ ብሔራዊ መዝሙር ይዘመራል ብለዋል።

👉 ጳጉሜን 04፦ የኅብር ቀን
ኢትዮጵያ የብዝኀ ማንነቶች ሀገር ናት፤ ብዝኀነት ኅብረታችን እና ጌጣችን ነው፤ የኃይላችን እና የጥንካሬያችንም ምንጭ ነው። ለዚህም ቀኑ የኅብር ቀን ተብሎ ተሰይሞ ይከበራል። በቀኑ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ይከናወናሉ።

👉 ጳጉሜን 05፦ የነገ ቀን

ይህ ስያሜ ኢትዮጵያ ነገን ዛሬ ላይ ኾና የምትሠራ ሀገር መኾኗን መልዕክት ለማስተላለፍ ነው። ነገን ለመገንባት ዛሬን በጥንካሬ መሥራት እንደሚያስፈልግም ማሳያ ነው ብለዋል።

የወረዳው የሴት አመራሮች የትስስር ፎረም በቀጣይ አመት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ መሆኑን አሳወቀ  #ደብረብርሃን ነሀሴ 27/2018ዓ.ም(ባሶ ኮሙኒኬሽን)በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ...
02/09/2026

የወረዳው የሴት አመራሮች የትስስር ፎረም በቀጣይ አመት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰራ መሆኑን አሳወቀ
#ደብረብርሃን ነሀሴ 27/2018ዓ.ም(ባሶ ኮሙኒኬሽን)

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ የሴት አመራሮች የትስስር ፎረም የ2019 በጀት አመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሔደ።

የበጀት አመቱን ዕቅድ የቀረቡት የወረዳው ሴቶች፣ ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የፎረሙ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ውቢት ጌታነህ እንደገለፁት ሴቶችን ማብቃት ሀገርን ማፅናት በመሆነ በሁሉም ዘርፍ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሴቶችን የውሳኔ ሰጪነት ሚና ከፍ ማድረግ ላይ ፎረሙ የቀጣይ ጊዜ አላማ አድርጎ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ዕቅዱ ሁሉን አቀፍ የሚያሰራ ዕቅድ መሆኑን እና ዕቅዱ ላይ ቢካቲቱ እና ቢጨመር ያሉትን ሀሳብና አስተያየታቸው አንስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሀረጓ ጌታነህ በመድረክ ማጠቃላያ ሃሳባቸው በቀጣይ በጀት አመት የሴቶች ውሳኔ ሰጪነት ሚና ላይ ተሳትፏቸው የላቀ ለማድረግ እና አንድነታችንና አብሮነታችን የሚያጠናክር መሆን አለበት ብለዋል።

ኃላፊዋ አክለውም በቀጣይ በጀት አመት እስከ ቀበሌ ያሉ የሴት አመራሮች በሰላም እና በሀገር ግንባታ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉና ሴት አመራሮች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተገቢው መንገድ እንዲፈቱ በማድርግ ረገድ ከፍተኛ ስራ እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል።

02/09/2026
"የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የድርሻውን እየተወጣ ነው" -አቶ አባይ መንግሥቴ​የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላ...
02/09/2026

"የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የድርሻውን እየተወጣ ነው" -አቶ አባይ መንግሥቴ

​የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም፣ የተመዘገቡ ስኬቶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን የሚገመግም መድረክ እያካሄደ ነው።

​በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግርና የሥራ መመሪያ ያስተላለፉት የቢሮው ሃላፊ አቶ አባይ መንግሥቴ፤ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መረጃ ለሕዝብ ከማድረስ ባሻገር በክልሉ ሰላም፣ መረጋጋትና ልማት እንዲሰፍን ታሪካዊ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አክለውም በክልሉ ለተገኘው የሰላም አየርና ለሕዝቡ አብሮነት መጎልበት ዘርፉ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን አብራርተዋል።

​በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተግባራት የዘርፉን ኃያልነት በተግባር ያረጋገጡ እንደነበሩ የጠቆሙት ሃላፊው፤ እነዚህ ሥራዎች የሕዝቡን የልማት እንቅስቃሴ የሚያፋጥኑ፣ እውነትን የሚያጎሉና የክልሉን መልካም ገጽታ በመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል።

​በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የተወጣው ሚና በታሪክ የሚዘከር መሆኑን ጠቅሰዋል።

​ዘርፉ የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ የልማት ፍላጎት በማንጸባረቅ ረገድ የተጫወተው ሚና ለልማት ሥራዎች መፋጠን ትልቅ አቅም መሆኑንም አቶ አባይ አብራርተዋል።

​በመድረኩ ያለፉትን ስኬቶችና ያጋጠሙ ማነቆዎችን በመፈተሽ፤ በቀጣይ የበጀት ዓመት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና ሁለንተናዊ እድገት በላቀ ኃላፊነት እንዲሠራ መንገድ የሚጠርግ መሆኑ ተመላክቷል።

02/09/2026
በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና እና ሽልማት ተበረከተላቸውየአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ...
01/09/2026

በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና እና ሽልማት ተበረከተላቸው

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በሠላም፣ በልማት በመልካም አስተዳደር እና በፓርቲ ተግባራት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖች እና ከተማ አስተዳድሮች እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በዚህም የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ከጥቅል የክልሉ ዞኖች 2ኛ ደረጃ በመያዝ የእውቅናና ሽልማት ተበርክቶለታል።

እንኳን ደስ አለን !!

የባሶና ወራና ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች እና ወጣት ክንፍ በዘላቂ ሰላምና ልማትን ግንባታ ዙሪያ ውይይት አካሄደ! #ደብረብርሃን ነሐሴ 26/2018ዓ/ም (ባሶ ኮሙኒኬሽን)በአማራ ክልል ሰሜን...
01/09/2026

የባሶና ወራና ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች እና ወጣት ክንፍ በዘላቂ ሰላምና ልማትን ግንባታ ዙሪያ ውይይት አካሄደ!

#ደብረብርሃን ነሐሴ 26/2018ዓ/ም (ባሶ ኮሙኒኬሽን)

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ወጣት ክንፍ እና ሴቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት «የውጪ የወረራ ስጋት እና የውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን!» በሚል መሪ ቃል ከአባላት ጋር የውይይት ተካሄዷል።

የውይይት መነሻ ሰነዱን ያቀረቡት የባሶና ወራና ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሀሳብ ታደሰ እንደተናገሩት ሴቶች እና ወጣቶች ለሰላም እና ለልማት ግንባታ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ በመሆኑ የህብረተሰቡን ሰላም አደጋ ላይ የሚጥሉ የውጪ ወረራ ስጋቶችንና የፅንፈኝነት አደጋዎችን በጋራ የመመከት ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የዉይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የውጫዊ ወረራ ስጋትን እና ውስጣዊ ጽንፈኝነትን ለመመከት አንድነትን፣ የህዝብ አብሮነትን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ገልፀው በተለይም ወጣቶች እና ሴቶች በቅንጅት በመስራት የህግ የበላይነትን በማስከበርና አንድነትን በማጠናከር መንግስት በሚያደርገው የሠላም ግንባታ ስራ ተሳትፏችንን አጠናክረው እንቀጥላለን ብለዋል።

በመጨረሻም የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ወጣት ክንፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሸሻ ተክለወልድ በመድረክ ማጠቃለያ ሃሳባቸው የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ፅንፈኛ ሃይሎች እየሠነዘሩብን ያለውን ጥቃት ማምከን የሚቻለው ወጣቶች እና ሴቶች በአንድነት እና በቁርጠኝነት የጎላ ተሳትፎ ማድረግ ስችሉ በመሆኑን የሀገራችንን ሰላም ለማጽናት እና የተጀመረውን ልማት ለማፋጠን ሁላችንም ከፀጥታ አካላት ጎን በመቆምና በማገዝ የድርሻውን መወጣት አለበት ሲሉ አሳስበዋል።

Address

Debre Berhan
251

Telephone

251116813902

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Basocommunication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Basocommunication:

Shortcuts

Share