06/09/2026
የኢትዮጵያ_ማንሰራራት
ጳጉሜ_1 "የእምርታ_ቀን"
በመንዝ ማማ ምድር ወረዳ የእመርታ ቀን በስንዴ ክላስተር ጉብኝትና በፓናል ውይይቶች እየተከበረ ይገኛል።
በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ማማ ምድር ወረዳ የመጀመሪያው የጳጉሜ ቀን "የእመርታ ቀን" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።
ከተረጅነት_ወደ_ምርታማነት እየተደረገ ያለውን ሂደት በወረዳው ዘራም ቀበሌ የተዘራውን የስንዴ ክላስተር በመጎብኘትና የፓናል ውይይት በማድረግ እየተከበረ ሲሆን በጉብኝቱ ላይ የመንዝ ማማ ምድር ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የፕላንና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሸት የሺጥላ፣ የፓለቲክና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀብተማርያም የሺጥላ፣ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቄ ደበበ እንዲሁም የግብርና ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የወረዳ ጠቅላላ አመራሮችና የቀበሌ አመራሮች ተገኝተው ምርታማነትን በማሳደግ ላይ እየተከናወነ ያለውን ተግባር ጎብኝተዋል።
"የእምርታ_ቀን"