አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ

አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን  ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ ANRS ethics & anti-corruption commission
Debire Birhan branch

03/09/2026

በታክስ አሰባሰብ ላይ የሚፈጠር ሙስና
🌿🌿🌿🌿🌿

የታክስ አሰባሰብ ስርዓት ውስጥ የሚፈጠር ሙስና በቀጥታ የመንግስትን የገቢ አቅም የሚጎዳ ከባድ ችግር ነው።

የግብር ገምጋሚዎችና ሰብሳቢዎች ጉቦ ተቀብለው ትክክለኛውን የግብር መጠን ሲቀንሱ ወይም ሙሉ በሙሉ ግብር እንዲታለፍ ሲያደርጉ መንግስት ማግኘት የነበረበትን ገቢ ያጣል። ይህ ገቢ ደግሞ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለመሠረተ ልማትና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ሊውል የነበረ ሀብት ነው።

በሌላ በኩል ህጋዊና በታማኝነት ግብር የሚከፍሉ ነጋዴዎች ካልከፈሉ ተወዳዳሪዎቻቸው ጋር ሲወዳደሩ ተጨማሪ ጫና ይደርስባቸዋል፣ ይህም ፍትሃዊ ያልሆነ የገበያ ውድድር ይፈጥራል።

በተጨማሪም ግብር ከፋዮች ስርዓቱ ላይ ያላቸው እምነት ሲሸረሸር በፈቃደኝነት ግብር የመክፈል ባህል ይዳከማል፣ ይህም የግብር ስወራን ልማድ ያባብሳል።

በአጠቃላይ በታክስ አሰባሰብ ላይ ያለው ሙስና የመንግስትን የፋይናንስ አቅም በማዳከም ለልማት ስራዎች የሚውል በጀት እንዲጠብ በማድረግ ሀገራዊ ልማትን ወደ ኋላ ይጎትታል።
#በአቶ ካሳ ርጥብነህ

03/09/2026
ትንሽዋ  ጉቦ ትልቁን የሀገር ስርቆት ትወልዳለችǃ💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈ሙስና ሲባል በተቋማትና ባለስልጣናት ደረጃ የሚፈጸም የገንዘብ ማጭበርበር ብቻ አይደለም። ከዕለት ተዕለት ኑሯችን እጅ መ...
03/09/2026

ትንሽዋ ጉቦ ትልቁን የሀገር ስርቆት ትወልዳለችǃ
💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈💈
ሙስና ሲባል በተቋማትና ባለስልጣናት ደረጃ የሚፈጸም የገንዘብ ማጭበርበር ብቻ አይደለም። ከዕለት ተዕለት ኑሯችን እጅ መንሻ ጉቦ ጀምሮ በሀገር ደረጃ የሚፈጸሙ ትላልቅ የሙስና ስርቆቶችን ያካትታል፡፡

ሙስና በአንድ ጀምበር ትልቅ የሀገር ዘረፋ ላይ አይደርስም የራሱ ደረጃ አለው።

ትናንሽ እጅ መንሻ
በዕለት ተዕለት ሕይወት አንድን መደበኛ አገልግሎት በፍጥነት ለማግኘት የሚሰጥ «የእጅ መንሻ» ወይም ትናንሽ ስጦታዎች ማኅበረሰቡ ዘንድ እንደ መደበኛ አሠራር መቆጠር ይጀምራሉ።

የጥቅም ትስስር እና አድልዎ
ትናንሽ ጉቦዎች እየተለመዱ ሲሄዱ ወደ መዋቅራዊ ደረጃ ይሸጋገራል። የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ለሥራው ብቃት ያላቸውን ዜጎች ትተው፣ ለዘመዶቻቸው፣ ለጓደኞቻቸው ወይም የጥቅም አጋሮቻቸው ቅድሚያ መስጠት ይጀምራሉ። ይህም ብቃት የሌላቸው ሰዎች የውሳኔ ሰጪነት ቦታ ላይ እንዲቀመጡ በር ይከፍታል።

የሰነድ ማጭበርበር
ብቃት የሌላቸው በጥቅም የተሳሰሩ ሰዎች ሥልጣን ላይ ሲወጡ የሰነድና ሌሎች ማጭበርበሮችን በማከናወን የሐሰት ሰነዶችን ማዘጋጀት እና የሕዝብ ንብረቶችን በስውር ወደ ግል ማዞርን የመሳሰሉ ዶርጊቶች ይፈፀማሉ፡፡

የሀገር ሀብት ዘረፋ
በዚህ ደረጃ ላይ ሙሰኞቹ የሀገሪቱን የሕግ አስከባሪ፣ የፍትሕ እና የቁጥጥር ሥርዓቶች በሙሉ በቁጥጥራቸው ሥር ያደርጋሉ። ሕግ የሚወጣውና የሚተገበረው ሕዝብን ለመጥቀም ሳይሆን የጥቂት ባለሥልጣናትና ነጋዴዎችን ዘረፋ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት ይሆናል። በዚህ ጊዜ የሀገር ሀብት ሙሉ ለሙሉ ለዘረፋ ይዳረጋል።

02/09/2026

የቅጣት ገደብ ምንነት
👉👉👉👉👉👉
ገደብ በወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ሰው የተፈረደበትን ቅጣት ከመፈፀሙ በፊት ለተወሰነ ጊዜ ቅጣቱ ታግዶለት አመሉ ቢፈተን ሁለተኛ ጥፋት ከማድረግ የሚታገድ መሆኑንና ለጠባዩ መሻሻል አንድ ጽኑ ማስጠንቀቂ ብቻ የሚበቃ መሆኑን ፍርድ ቤት ሲያምንበት ቅጣቱን በመወሰን እና የፈተና ጊዜ በመስጠት አፈፃፀሙ ታግዶ እንዲቆይ የሚያደርግበት ስርዓት ስለመሆኑ ከወንጀል ሕጉ አንቀጽ 192 መረዳት ይቻላል፡፡ ለመልካም ጠባይ የሚሰጠው የፈተና ጊዜ የሚወሰነው የወንጀሉን ከባድነት፣ የወንጀል ድርጊት መደጋገም ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት እና በጥፋተኛው ላይ ሊጣልበት የሚቻለውን እምነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ሲሆን የፈተናው ጊዜ የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር ሆኖ ከ2 ዓመት ሊያንስ ከ5 ዓመት ሊበልጥ እንደማይችል በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 196 ተደንግጓል፡፡ ሆኖም ከቅጣቱ ጋር የጥንቃቄ እርምጃዎች ተወስነው ከሆነ እንዚህ የጥንቃቄ እርምጃዎች አይታገዱም፡፡

02/09/2026

የሕጋዊ ሥነ-ልክ ክልከላዎችን መተላለፍ የሚያስከትለው የሕግ ተጠያቂነት
🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫🚫
የወንጀል ቅጣት
 በአዋጁ አንቀጽ 19/1 ስር እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው ሌላውን ለመጉዳት ወይም ለራሱ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በአዋጁ አንቀጽ ከተመለከቱት የመለኪያ አሀዶች እና የአሃዶች ብዜቶች ውጭ በመጠቀም ምርት ወይም አገልግሎት ሲሸጥ ከተገኘ ከብር 10,000 እስከ ብር 50,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ3 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚቀጣ ሲሆን ድርጊቱ የተፈፀመው ለሁለተኛ ጊዜ ከሆነ ቅጣቱ ከብር 51,000 እስከ 100,000 የሚደርስ መቀጮ ወይም ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት የሚደርስ ቀላል እሥራት ይሆናል፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው በቸልተኛነት በሆነ ጊዜ ቅጣቱ ከብር 10,000 እስከ ብር 20,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከስድስት ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ይሆናል (አንቀጽ 19(6))፡፡
 ማንኛውም ሰው እያወቀ የመለኪያ መሣሪያዎችን ዓይነት ወይም ንድፍ ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አቅርቦ ሳያስጸድቅ እና የተስማሚነት የምስክር ወረቀት ሳይሰጠው ሲያመርት፣ ወደ ውጭ አገር ሲልክ፣ ወደ አገር ውስጥ ሲያስገባ ወይም ሲያከፋፍል ከተገኘ ከብር 100,000 እስከ ብር 250,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት በሚደርስ ቀላል እስራት ይቀጣል (አንቀጽ 19(2))፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው በቸልተኛነት በሆነ ጊዜ ከብር 10,000 እስከ 20,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ6 ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ይሆናል (አንቀጽ 19(6))፡፡
ማንኛውም ሰው ሌላውን ለመጉዳት ወይም ለራሱ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በአዋጁ መሠረት የመለኪያ መሳሪያን ለትክክለኛነት ማረጋገጥ ሳያቀርብ አገልግሎት ሲሰጥ ከተገኘ ከብር 10,000 እስከ 20,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ3 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል (አንቀጽ 19(3))፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው በቸልተኛነት በሆነ ጊዜ ከብር 10,000 እስከ ብር 20,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ6 ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ይሆናል (አንቀጽ 19(6))፡፡
 ማንኛውም ሰው በሕግ ሥልጣን ሳይኖረው አስቦ የመለኪያ መሳሪያን የትክክለኛነት ማረጋገጫ ምልክት ካላቀቀ፣ በሌላ ከተካ ወይም የፕሎምብ እሽግን ከበጠሰ ከብር 150,000 እስከ ብር 300,000 በሚደርስ መቀጮ እና ከ1 ዓመት እስከ 5 አመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል (አንቀጽ 19(4))፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው በቸልተኛነት በሆነ ጊዜ ከብር 50,000 እስከ ብር 100,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ1 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ይሆናል (አንቀጽ 19(7))፡፡
 ማንኛውም ሰው ለራሱ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ተገቢውን መግለጫ ሳያደርግ፣ በመግለጫው ላይ የተጣራ መጠን ሳይገልጽ፣ በመግለጫው ላይ ከተገለጸው ጋር በማይጣጣም ሁኔታ ወይም የይለፍ የምስክር ወረቀት ሳይሰጠው የታሸገ ምርት ሲያመርት፣ ሲያሽግ፣ ወደ ውጭ አገር ሲልክ፣ ወደ አገር ውስጥ ሲያስገባ፣ ለሽያጭ ሲያቀርብ ወይም በሌላ መንገድ ሲያስተላልፍ ከተገኘ ከብር 100,000 እስከ ብር 200,000 በሚደርስ መቀጮ እና ከ3 አመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል (አንቀጽ 19(5))፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው በቸልተኛነት በሆነ ጊዜ ከብር 50,000 እስከ 100,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም ከ1 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ይሆናል (አንቀጽ 19(7))፡፡
 ማንኛውም የሕጋዊ ሥነ-ልክ ኦፊሰር ወይም ጠጋኝ ለራሱያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የመለኪያ መሳሪያን ወይም የታሸገ ምርትን ትክክለኛነት በዛባ ሁኔታ ካረጋገጠ ወይም ከጠገነ ከብር 50,000 እስከ ብር 100,000 በሚደርስ መቀጮ እና ከ3 አመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል (አንቀጽ 19(8))፡፡

01/09/2026

#ሌብነት ላይ ጠንከር ያለ ርምጃ እንወስዳለን!

**************

ትውልድን በሥነምግባር፣ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች

https://play.google.com/store/apps/details?id=com.codewaveet.ecis

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች

https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

31/08/2026

ሙስናን ለመግታት መቀመጥ ያለባቸዉ ቅድመ ሁኔታዎች፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ሙስናን በዘላቂነት ለመግታትና ለመከላከል አጠቃላይ አደረጃጀትን፣ ህግን፣ ቴክኖሎጂንና የህብረተሰብ ግንዛቤን ያቀናጀ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ያስፈልጋል።

በዋናነት መቀመጥ ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች፦

1. ፖለቲካዊ ቁርጠኝነትና የባለቤትነት ስሜት፦
የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ሙስናን የመዋጋት ግልጽ፣ የማያወላውልና በተግባር የሚታይ ቁርጠኝነት ሊኖራቸው ይገባል። አመራሮች በግልፅነትና በታማኝነት በመስራት ለሌላው አርአያ መሆን አለባቸው።

2. ጠንካራና ነፃ ተቋማት፦
የፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ የኦዲት መስሪያ ቤቶችና የፍትህ አካላት ከማንኛውም ፖለቲካዊና ውጫዊ ጫና ነፃ ሆነው በገለልተኝነት የመስራት ስልጣን ሊኖራቸው ይገባል። በእነዚህ ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎችን የሙያ፣ የቴክኖሎጂና የቁሳቁስ አቅም በተገቢዉ ሁኔታ ማሳደግ።

3. ግልጽነትና ተጠያቂነት፦
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ፣ የግዥ ስርዓት፣ የጨረታ ሂደቶችና የሀብት ድልድል ለህዝብ ግልጽና ክፍት መሆን አለባቸው። የመንግስት ተሾሚዎችና ሰራተኞች ንብረታቸውንና የገቢ ምንጫቸውን የሚያስመዝግቡበትና አጠራጣሪ ሀብቶች የሚመረመሩበት ስርዓት መዘርጋት አለበት።

የውስጥና የውጭ ኦዲት አሰራርን ማጠናከርና የኦዲት ግኝቶች ላይ ፈጣን የእርምጃ መውሰጃ መንገድ መዘርጋት።

4. የህግ ማዕቀፍና የፍትህ ስርዓት የበላይነት፦
ሙስናን፣ የጥቅም ግጭትን እና ህገ-ወጥ ሀብት ማከማቸትን የሚከለክሉ ግልጽ ህጎች መኖር። ህጉ በማንኛውም ሰው ላይ ያለ አድልኦ በእኩልነት የሚተገበር መሆኑን ማረጋገጥ።
ሙስናን የሚጠቁሙና ምስክርነት የሚሰጡ አካላትን ከበቀልና ከጥቃት የሚጠብቅ የህግ ማዕቀፍ መዘርጋት።

5. ዲጂታላይዜሽንና የአሰራር ዘመናዊነት፦
የሰውና የሰው ግንኙነትን የሚቀንሱ የአገልግሎት መስጫ ስርዓቶችን (ለምሳሌ፡ ዲጂታል ታክስ፣ የመንግስት ግዥ፣ የመታወቂያና ፍቃድ አሰጣጥ) መዘርጋት።

የገንዘብ ዝውውር በባንክና በዲጂታል መንገድ ብቻ እንዲሆን ማድረግ ህገ-ወጥ የገንዘብ ቅብብልን ይቀንሳል።

6. የህዝብና የሲቪክ ማህበራት መሳተፍ፦
በትምህርት ቤቶች፣ በሃይማኖት ተቋማትና በብዙሃን መገናኛዎች የዜጎችን ሥነ-ምግባርና ታማኝነት የሚያጎለብቱ ትምህርቶችን መስጠት።

መገናኛ ብዙሃን መረጃዎችን ነፃ ሆነው እንዲያገኙና የሙስና ወንጀሎችን በመርመር ለህዝብ እንዲያቀርቡ ሁኔታዎችን ማመቻቸት።

ህዝባዊ ማህበራት የመንግስት አሰራርን እንዲከታተሉና እንዲሞግቱ ማበረታታት።

7. ተመጣጣኝ የሰራተኞች ክፍያና ማበረታቻ፦
ለመንግስት ሰራተኞች የሚከፈል ደመወዝ የወቅቱን የኑሮ ውድነት ያገናዘበ እንዲሆን ማድረግ (ይህም ለሙስና የሚገፋፋውን የኢኮኖሚ ጫና ይቀንሳል)።

የስራ እድገትና ሹመት በዝምድና ወይም በፖለቲካ ወገንተኝነት ሳይሆን በችሎታና በሥነ-ምግባር ላይ ብቻ እንዲሆን ማድረግ የሚሉ ናቸዉ።

Address

Asmara Road
Debre Birhan
2510116375964

Telephone

+251920082315

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ:

Shortcuts

Share