Birhan G/hiwot

Birhan G/hiwot Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Birhan G/hiwot, Public & Government Service, Debre Birhan.

ለሁሉም የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ቀደመ ቤቱ...
06/01/2026

ለሁሉም የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ቀደመ ቤቱ ሊመልስ፤ የተከፈተችውን ሲኦልን ወና አድርጎ የተዘጋችውን ገነት ሊከፍት ቃልኪዳን ነበረው።

ይህንንም ቃል ኪዳን ከድንግል ማርያም በመወለድ፤ ሰው ሆኖ የሰውን ልጅ ልያድን ወደዚህች ዓለም መጥቷል።

የሰማዩም የምድሩም ገዢ፤ የፍጥረት ሁሉ ጌታ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በንግስናው ሳይሆን በትህትናው በከብቶች በረት ተወለደ። ይህ ብዙ ምስጢር ያለው ፤ እልፍ ትምህርት የምንቀስምበት ልዩ በዓል ነው።

ይህን ታላቅ በዓል ስናከብር ከተረፈን ላይ ሳይሆን ካለን ላይ ቀንሰን ለሌሎች በመትረፍ፣ በመደጋገፍ፣ በመተሳሰብ፣ ይበልጥ የምንቀራረብበት፤ ለሰው መሆንን የምንማርበት፤ በአብሮ የመኖር ኢትዮጵያዊ ትውፊቶቻችንን የበለጠ በማጥበቅ እንዲሁም የከተማችንን የልማት ስራዎች በተቀናጀ መልኩ በመከወን ሊሆን ይገባል።

ደብረ ብርሃን ከተማችን ከመቸውም በላይ የኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን አጠናክራ እየቀጠለች ትገኛለች፤ ስለሆነም በሀሉም ዘርፎች ከተማችን አሁንም ቢሆን ለኢንቨስትመንት የሚሆን መሬቶችን በማዘጋጀት አልሚዎችን እየተጠባበቀች ትገኛለች።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የአብሮነት በዓል እንዲሆንም ከልብ እየተመኘሁ፡በድጋሜ ለመላው የከተማችን ነዋሪዎች እና ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ።

መልካም የገና በዓል ይሁንላችሁ !

ብራዉን ፉድ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ተመረቀ። በዛሬ እለት በደብረ ብርሃን ከተማ በ5.6ቢሊዮን የተገነባዉ ''ብራዉን ፉድ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ'' የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር  አቶ ተመስገ...
11/11/2025

ብራዉን ፉድ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ተመረቀ።

በዛሬ እለት በደብረ ብርሃን ከተማ በ5.6ቢሊዮን የተገነባዉ ''ብራዉን ፉድ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ'' የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ:የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ሌሎች የፌደራል ሚኒስትሮች የክልላችን ቢሮ ሀላፊዎች :የሰሜን ሸዋ ዞን እና የደብረ ብርሃን ከተማ አመራሮች እንዲሁም የሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት ማስመረቅ ችለናል።

የብራዉን ምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ለቢራ ፋብሪካዎቹ ግብዓት፣ የተመጣጠነ የህፃናት ምግብ ዱቄት አንዲሁም የእንስሳት መኖ የሚያመርት ይሆናል።

ፋብሪካው በቆሎን በግብዓትነት የሚጠቀም ሲሆን በቀን 3ሺ በአመት ደግሞ 1ሚሊዮን ኩንታል የማምረት አቅም ሲኖረዉ ከ420 በላይ ለሚሆኑ ዜጎችም የስራ እድል መፍጠር የሚችል አቅም ያለዉ ግዙፍ ፋብሪካ ነዉ።

ይህ የምረቃ ፕሮግራም በሰላም እንደጠናቀቅ ያላሰለሰ ድጋፋችሁን ከጎናችን ሆናችሁ ስትደግፉን ለነበራችሀ ሰላም ወዳድ የከተማችን ማህበረሰብ እና አጋር አካላት በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ።

ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት
'' ኑ ደብረ ብርሃን ከተማችንን በጋር እናልማ ''

ለ2018 አዲስ አመት እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰንባለፈው 2017 በጀት አመት በከተማችን በኢንቨስትመንት ዘርፉ  ተጨባጭ ለውጦችን በህዝባችን የዘላቂ ልማት ላይ በመመርኮዝ ለተሰራው ስራ በከፍ...
10/09/2025

ለ2018 አዲስ አመት እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን

ባለፈው 2017 በጀት አመት በከተማችን በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተጨባጭ ለውጦችን በህዝባችን የዘላቂ ልማት ላይ በመመርኮዝ ለተሰራው ስራ በከፍተኛ የአፈጻጸም ድርሻ የክልላችን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ እውቅናና ሽልማት ሰጥቶናል።

ለዚህ የላቀ የዘመኑ የኢኮኖሚ ውጤት የአንበሳውን ድርሻ የተወጣው የከተማችን አመራር ፣ ሰላም ወዳዱ የከተማችን ህዝብ ፣ የጸጥታ መዋቅራችን እንዲሁም በተለየ መልኩ የክልላችን መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ሳይንሳዊ አልቆ ማየት ትኩረት ነው።

የሁለተናዊ ህብር ከተማችን ደብረ ብርሃን ብዙ ለውጥን እያስተናገደች ትገኛለች በዚህ የለውጥ መሸጋገሪያ ምሰሶ የኢኮኖሚ ክንፍ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ማርሽ ቀያሪው መሆኑ ይታወቃል።

በ2018 አዲስ አመትም የዘርፉን አገልግሎት በቴክኖሎጂ በማቀናጀት የኢንዱስትሪ ቅንጅታዊ የመልማት አውታርን የበለጠ በማስፋት የኢኮኖሚውን ልዕቀት በአዲስ መንፈስ እና ጥንካሬ ለስኬት የልማት መሬቶችን በማዘጋጀት ለመቀበል ተዘጋጅተናል።

ስለሆነም ለዚህ የጋራ እድገትና ልማት የዘርፉ ለትውልዱ ብስራት ለመሆን በጋራ እንድንረባረብ ጥሪ አቀርባለሁ።

አዲሱ አመት የሰላም ፣ የጽናት ፣ የህብረት እሴቶችን በማቀናጀት የጎህ መሻትን በመላበስ ምሉዕ ዕይታ ያለውን ብርሃንን ወደ ተጨባጭ የኢንቨስትመንት ደረጃ የምንሸጋገርበት እንዲሆን እመኛለሁ። 2018 መልካም የስራ ዘመን ፣ መልካም አዲስ አመት ይሁንልን።

አቶ ብርሃን ገብረሂዎት
የደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኀላፊ

እንኳን ደስ አላችሁ።መምሪያችን  በ2017 በጀት አመት በተሰሩ ስራዎች  #1ኛ በመወጣት ተሸላሚ ሆኗል።የደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ  ካሉት   የከተማ አስተዳደሮች...
04/09/2025

እንኳን ደስ አላችሁ።

መምሪያችን በ2017 በጀት አመት በተሰሩ ስራዎች #1ኛ በመወጣት ተሸላሚ ሆኗል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ካሉት የከተማ አስተዳደሮች ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያዎቸ #1ኛ በመውጣት ሜዳሊያ፣ የላፕቶፕ ኮምፒውተር የዋንጫ አንድ መቶ ሽብር እና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗል።

የከተማችን የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ለዚህ ውጤታማ ስራ እንዲበቃ ላደረጋችሁ የከተማ አስተዳደሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ፣ በየደረጃው ላላችሁ ጠቅላላ አመራሮች ፣ ለተቋማችን ባለሙያዎች (experts) ፣ የጸጥታ አካላት ፣ ሰላምና ልማት ወዳዱ የከተማችን ህዝብ እንዲሁም ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምር ምክረ ሀሳብ ለለገሳችሁ አካላት ሁሉ ምስጋናዬ የላቀ ነው።

በተለይ ለከተሜነት ኢንቨስትመንት ኢኮኖሚ ትልቁ ኮሊደር ከመሆኑም በላይ ለዚህ የዘመናዊ የሁለተናዊ የውድድር አለም የላቀ እሳቤ የላቀ ግብ በረጅሙ አሻግሮ በማየት የተቀናጀ መልስ የሚሠጥ ነው።

ስለሆነም በቀጣይ በጀት አመትም በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉ "አርቀን በማሠብ አልቀን እንሰራለን" በቴክኖሎጂ ቅልጥፍና በታነጸ ስርአት አገልግሎታችንን የበለጠ ግብ እንዲያሳካ በማዘመን በቅንጅት ለለውጡ ፍኖተ ካርታ እንተጋለን።

'' አርቀን በማሰብ አልቀን እንስራለን ''

በዛሬዉ እለት የ2017 ዓ.ም ተግባራት አፈፃጸም ግምገማ እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እካሄደናል።   በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ200 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ...
21/07/2025

በዛሬዉ እለት የ2017 ዓ.ም ተግባራት አፈፃጸም ግምገማ እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እካሄደናል።

በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ200 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት አቅደን 36 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 232 ባለሃብቶች ፈቃድ መስጠት ችለናል።

እነዚህም ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡ ከ21 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚችሉ ናቸዉ።

በዚሁ በጀት አመት 16 ኢንዱስትሪዎችን ምርት ለማስጀመር አቅደን 25 ኢንዱስሪዎች ወደ ምርት አስገብተን ለ5 ሺህ 200 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

በተጨማሪም ከ58 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተኪ ምርት ማምረት ሲችሉ 8 ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ለውጭ ገበያ ምርታቸውን ማቅረብ ችለዋል።

ለዚህም እቅድ መሳካት በየደረጃዉ ያሉ አጋር አካላት ቅንጂታዊ አሰራር እየተሻሻለ መምጣቱ :የተሻለ አገልግሎት አሰጣጥ መኖሩ : ጠንካራ የፕሮሞሽን ስራ መሰራቱ : የከተማችን ማህበረሰብ ለልማትና ለሰላማ ቁርጠኛ መሆኑ ለዚህ አፈፃፀም ትልቅ ሚና ነበራቸዉ።
በመጨረሻም ለዚህ ለተሻለ ዉጤት አፈፃፀም ለነበራቸዉ የመምሪያዉ ቡድኖችና ባለሙያዎችን የእዉቅና ሽልማት በመስጠት መድረኩን ማጠናቀቅ ችለናል።

'' የተሻለ ትጋት ለተሻለ ዉጤት''       =====================    በዛሬ እለት በጎንደር ከተማ "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሀሳብ በክልላችን በሶስተኛዉ ...
03/06/2025

'' የተሻለ ትጋት ለተሻለ ዉጤት''
=====================
በዛሬ እለት በጎንደር ከተማ "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሀሳብ በክልላችን በሶስተኛዉ የኢትዮጵያ ታምርት የማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ በ2017 አ.ም በክልሉ ከሚገኙ ዞኖች እና ከተማ አስተዳደሮች የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ :-
በ2015 አ.ም
በ2016አ.ም
በ2017አ.ም
ለሶስት ተከታታይ አመታት 1ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

በመሆኑም ይህ ውጤት እንዲመዘገብ የበኩላችሁን ላበረከታችሁ የከተማችን አጠቃላይ አርመራር፣ ባለሙያዎች እና አጋር አካላት እንዲሁም ለታታሪው እና ሰላም ወዳዱ የደብረ ብረሀን ከተማ ህዝብ በሙሉ ፡
የምስጋና እና የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክቴን እስተላልፋለሁ።

ይህ ውጤት በሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፡ ባላሳለሰ መታከት ድካም እና ጥረት እንዲሁም በከተማችን ነዋሪዎች ተራማጅ አሳቢነት እና የአዲስ ሀሳብ ተግባሪነት የተገኘ ውጤት መሆኑ እሙን።

ይህንኑ ተግባራችንንም በቀጣይ አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑ ለመግለፅ እወዳለሁ አመሰግናለሁ።

ኑ ከተማችንን በጋራ እናልማ !!
'' ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት ''

ዛሬ በከተማችን ደብረ ብርሃን"ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ ለሶስተኛ ግዜ ማካሄድ ችለናል።   በመድረኩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕ...
25/05/2025

ዛሬ በከተማችን ደብረ ብርሃን"ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ ለሶስተኛ ግዜ ማካሄድ ችለናል።

በመድረኩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ(ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኋላፊ እንድሪስ አብዱ ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸትን ፣አልሚ ባለሃብቶች በተገኙበት የከተማችንን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የሚያሳይ የዉይይት ሰነድ ያቀረብን ሲሆን ፡

በከተማችን ደብረ ብርሃን እስከ 1998 ዓ.ም ድረስ አንድ የብልደርብስ ፋብሪካ የነበራት ከተማችን አሁን ላይ በኢንድስትሪዉ ዘርፍ ብቻ 145 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 745 ፕሮጀክቶች በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ ሲሆን በምግብና ፋርማሲዮቲካል 256፤በጨርቃጨርቅ 89፣በብረታ ብረትና እንጨት ውጤቶች 193፣በኬሚካልና ኮንስትራክሽን 207 ማድረስ ችለናል።

በመጨረሻም አልሚ ባለሀብቶቻችን የፋይናንስ፣የመብራት፣የመንገድ፣የግብዓት አቅርቦትን በተመለከተ ያነሷቸዉን ጥያቄዎች ከተማ አስተዳደሩና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ያሉትን ችግሮች በጋራ ለመፍታት ድምዳሜ ላይ ደርሰናል።

በትላንቱ መርሐ ግብራችን ላይም ያስመረቅናቸዉን ፋብሪካቸዉ የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት የዕለቱን የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ አጠናቀናል ።

''' ኑ ደብረብርሃን ከተማችንን በጋራ እናልማ ''

በዛሬዉ ዕለት በከተማችን ደብረብርሃን በ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ካቲታል የተገነቡ ለ835 ዜጎች ስራ ዕድል መፍጠር የቻሉ ሶስት አምራች ኢንደስትሪዎችን የክልል ከፈተኛ አመራሮች በተገኙበት አስመር...
24/05/2025

በዛሬዉ ዕለት በከተማችን ደብረብርሃን በ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ካቲታል የተገነቡ ለ835 ዜጎች ስራ ዕድል መፍጠር የቻሉ ሶስት አምራች ኢንደስትሪዎችን የክልል ከፈተኛ አመራሮች በተገኙበት አስመርቀን: በተጨማሪ ሶስት ኢንደስትሪዎችን ማስጎብኝት ችለናል።

በዚህም የምርቃትና የጎብኝት ፕሮግራም ላይ የአብክመ ም/ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አብዱ ሁሴን(ዶ.ር) ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ(ዶ.ር) ፣ የአብክመ ኢንደ/ኢንቨ/ቢሮ ሀላፊ እንድሪስ አቡዱ : የከተማችን አጠቃላይ አመራሮች በተገኙበት ሶስት ኢንደስትሪዎችን አስመርቀን ሶስት ተጨማሪ ኢንደስትሪዎችን ማስጎብኘት ችለናል።
እነዚህ የተመረቁ ሶስት ኢንደስትሪዎችን ለሀገራችን:ለክልላችን ብሎም ለከተማችን ከዉጭ ሊገቡ የሚችሉ ምርቶችን የመተካት ከፍተኛ ሚና አላቸዉ።
ዉቧና ደጋማዋ የሰላም አንባሳደር የሆነቺዉ ከተማችን ደብረብርሃን ሰላሟን አስጠብቃ ለአልሚዎቿ እንዲሁም ለነዋሪዎቿ ተስማሚ የሆነዉን መልከዓ ምድሯን ከሰላሟ ጋር አጣምራ ፣ የአሰራርና የልማት ጎዳናዋን ዘመናዊነትን በተላበሰ መልኩ እያዘመነች ያለቺ ከተማ ናት።
ለዚህም የከተማችን ሰላም ወዳድ ማህበረሰብ እና ከላይኛዉ እስከ ታቺኛዉ ያለዉ አመራር በጋራና በቅንጂት ተናቦ የመፈፀም ጉልህ ማሳያ ነዉ ።
በቀጣይም ለሀገር እና ለትዉልድ ተሻጋሪ እንዲሁም ተስፋ ሰጭ ፋብሪካዎችን የምናስመርቅ ይሆናል።

ይህ ዉጤት የተሻለና የተሳካ እንዲሆን ለተሳተፋችሁ የክልል እና የከተማችን አጠቃላይ አመራሮችን እንዲሁም ሰላም ወዳዱ የከተማችን ማህበረሰብ ከልብ አመሰግናለሁ ።
'' ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት ''
''' ኑ ከማችን ደብረብርሃን በጋራ እናልማ '''

19/04/2025

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች ኢትዮጵያዉያንና ትወልደ ኢትዮጵያዉያን በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም በፍቅር በጤና ጠብቆ አደረሰን አደረሳችሁ።

ዛሬ በከተማችን በ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ካፒታል የተገነቡ አምስት አምራች ፋብሪካዎችን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አስመርቀናል።   በምረቃ መርሃ-ግብራችን ላይ የኢፌደሪ  ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ...
25/02/2025

ዛሬ በከተማችን በ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ካፒታል የተገነቡ አምስት አምራች ፋብሪካዎችን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አስመርቀናል።

በምረቃ መርሃ-ግብራችን ላይ የኢፌደሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ክቡር መላኩ አለበል ፣ የአማራ ክልል ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ፋንቱ ተስፋዬ፣ የክልላችን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኀላፊ ክቡር ይርጋ ሲሳይ፣ የክልላችን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኀላፊ ክቡር እንድሪስ አብዱ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ክቡር በድሉ ውብሸትን ጨምሮ የከተማችን በየደረጃው ያሉ አመራሮች በተገኙበት 5ቱ ፋብሪካዎች አስመርቀናል።

እነዚህ ፋብሪካዎች ለሀገራችን እና ለከተማችን ከፍተኛ ሚና ያላቸው ሲሆኑ የውጭ ምንዛሬን ያስገኛሉ፤ በዶላር የሚገዙ ለውስጥ ፍጆታ የሚውሉ ምርቶችንም የመተካት ሚና አላቸው።

በቀጣይም ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 17 አምራች ኢንዱስትሪዎችንም የምናስመርቅ ይሆናል።

ከተማችን በታሪካዊ ምዕራፏ ያላትን ፊት ቀዳሚነት በዘመናዊ የኢኮኖሚ ኮሊደርም በፍጥነት እንድትጓዝ አገልግሎታችንን በማዘመን ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋና ፈጣን በማድረግ እየሰራን እንገኛለን የመጣውም ውጤት በሁለተናዊ መታተር እና በቅንጀት ነው።

በቀጣይም በርካታ ተስፋን ያቀፉ ለአካባቢ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችን አቅም፤ ለትውልድ ተሻጋሪ ሁለተናዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ፋብሪካዎችን እናሥመርቃለን።

በዚህ ውጤታማ ስራ ላይ ለተሳተፋችሁ የፌደራል፣ የክልል፣ ተቀዳሚ ከንቲባን ጨምሮ የከተማ አመራሮች ፣የጸጥታ አካላት መላው ልማት ወዳዱ ማህበረሰባችን ከፍ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።

" ኑ ደብረብርሃን ከተማችንን በጋራ እናልማ "

ለሁሉም የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ቀደመ ቤቱ ...
06/01/2025

ለሁሉም የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ቀደመ ቤቱ ሊመልስ፤ የተከፈተችውን ሲኦልን ወና አድርጎ የተዘጋችውን ገነት ሊከፍት ቃልኪዳን ነበረው።

ይህንንም ቃል ኪዳን ከድንግል ማርያም በመወለድ፤ ሰው ሆኖ የሰውን ልጅ ልያድን ወደዚህች ዓለም መጥቷል።

የሰማዩም የምድሩም ገዢ፤ የፍጥረት ሁሉ ጌታ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በንግስናው ሳይሆን በትህትናው በከብቶች በረት ተወለደ። ይህ ብዙ ምስጢር ያለው ፤ እልፍ ትምህርት የምንቀስምበት ህቡዕ ክንዋኔ ነው።

የጌታ ልደት ከራስ በላይ ለሰው መሆንን የፈታ ቅኔ ነው። የሰው ልጅ ፍቅር ከሰማያዊው ዙፋኑ በልጦበታል። ለቃል የመታመን ፤ ለፍቅረ ልዕልና የሚከፈል መስዋዕትነትን ያሳየ የፍጥረት ሁሉ አስተምህሮ ነው።

ይህን ታላቅ የትህትና በዓል ስናከብር ከተረፈን ላይ ሳይሆን ካለን ላይ ቀንሰን ለሌሎች በመትረፍ፣ በመደጋገፍ፣ በመተሳሰብ፣ ይበልጥ የምንቀራረብበት፤ ለሰው መሆንን የምንማርበት፤ በአብሮ የመኖር ኢትዮጵያዊ ትውፊቶቻችንን የበለጠ በማጥበቅ እንዲሁም የከተማችንን የልማት ስራ በራዕይ ከፍታ በላቀ ተስፋ በማንገብ በድምቀትና በአብሮነት መንፈስ ሊሆን ይገባል።

ደብረ ብርሃን ከተማችን የኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን አጠናክራ እየቀጠለች ነው፤ ስለሆነም በተለያዩ ዘርፎች ከተማችንን አሁንም ቢሆን ለኢንቨስትመንት የሚሆን መሬቶችን በማዘጋጀት አልሚዎችን እየተጠባበቀች ትገኛለች፤
ከተማችን ኑ! በጋራ እናልማ ለማለት እወዳለሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የአብሮነት በዓል እንዲሆንም ከልብ እመኛለሁ። በድጋሜ ለመላው የከተማችን ነዋሪዎች እና ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ።

መልካም የገና በዓል ይሁንላችሁ !

ብርሃን ገ/ሂዎት
የደብረ ብርሃን ከተማ አስ/ኢን/ኢንቨስትመንት መምሪያ ሀላፊ

የፊቤላ የኤሌክትሪክ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ለከተማችን አገልግሎት የሚሠጡ ባሶችን ገጣጥሞ  ዛሬ አስረክቧል::እንኳን ደስ አላችሁ!በከተማችን የሚገኘው ፊቤላ የመኪና መገጣጠሚያን ጨምሮ ሌሎች ፋብሪ...
24/10/2024

የፊቤላ የኤሌክትሪክ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ለከተማችን አገልግሎት የሚሠጡ ባሶችን ገጣጥሞ ዛሬ አስረክቧል::
እንኳን ደስ አላችሁ!

በከተማችን የሚገኘው ፊቤላ የመኪና መገጣጠሚያን ጨምሮ ሌሎች ፋብሪካዎች የማህበራዊ ኀላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።

ዛሬ የፊቤላ መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ለከተማው መንግስት ሰራተኛና ለነዋሪው ሰርቪስ በመሆን የሚያገለግሉ መኪኖችን የከተማችን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት አስረክቧል።

የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት ፣ የራስን ምርት ለራስ ፍጆታ መጠቀም የሚለውን እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ ኀላፊነቶችን ፊቤላ ተግባራዊ አድርጓል።

ከላይ የተጠቀሰው ፋብሪካን ጨምሮ ሌሎቹም ለማህበረሰብ አገልግሎት ፣ ለከተማችን ሁለተናዊ እድገት ሚናቸውን እንድትወጡ አሳስባለሁ።

Address

Debre Birhan

Telephone

+251913868953

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Birhan G/hiwot posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share