Debre Birhan Blood Bank Service

Debre Birhan Blood Bank Service It starts its real work on 23/07/06 E.C. It is established "TO SAVE THE LIFE OF AT RISK...."

ለመንዝ ማማ እና መንዝ ላሎ ወረዳ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች፣ ለወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤቶች፣ ሆስፒታል እና መላው አጋር አካላት፤​ደብረ ብርሃን ደም ባንክ ከሁለቱም ወረዳዎች ጋር በመተባበር ባካ...
26/08/2026

ለመንዝ ማማ እና መንዝ ላሎ ወረዳ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች፣ ለወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤቶች፣ ሆስፒታል እና መላው አጋር አካላት፤

​ደብረ ብርሃን ደም ባንክ ከሁለቱም ወረዳዎች ጋር በመተባበር ባካሄደው የደም ልገሳ መርሃ-ግብር/ንቅናቄ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ወገኖች የወገንን ህይወት ለማዳን ደማቸውን በነፃነት ለግሰዋል።

❤​ለክቡራን ደም ለጋሾች፦ የወገንን ህይወት ለመታደግ ደማችሁን በፈቃደኝነት በመለገስ የሰው ልጅ ህይወት እንዲቀጥል ላደረጋችሁት ታላቅ ሰብአዊነት ከልብ የመነጨ የከበረ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

❤​ለወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤቶች እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት፦ ከደም ባንካችን ጋር በቅርበት በመተባበር፣ ህዝቡን በማንቀሳቀስ እና ንቅናቄው በከፍተኛ ድምቀትና ስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁት ያልተቆጠበ ጥረት እና አርአያነት ያለው አጋርነት ምስጋናችን የላቀ ነው።

የጀመራችሁት ይህ የተቀደሰ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሙሉ እምነታችን ነው።

​ለሰጣችሁት ህይወት ሰጪ ደም እና ለወገን አለኝታነታችሁ ሁልጊዜም እናመሰግናለን!

​ከታላቅ አክብሮት ጋር፣
ደብረ ብርሃን ደም ባንክ

19/08/2026

👉የክረምት በጎ ፈቃድ የደም ልገሳ መርሐ ግብራችን አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን በደስታ እናሳውቃለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የእናንተ የደም ልገሳ ለብዙዎች ወገኖቻችን ህይወት መትረፍ ቁልፍ መፍትሄ ነው።

⌚️እስካሁን በፕሮግራሙ ተሳትፋችሁ ለለገሳችሁ በሙሉ የከበረ ምስጋናችንን እያቀረብን፤ ገና ለጋሾች ያልሆናችሁ ወገኖቻችን ሁሉ፣ ወደ ደም ልገሳ ማዕከላት በመምጣት ይህንን የተቀደሰ የሰብአዊነት ስራ እንድትቀላቀሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የእርስዎ ጥቂት ደቂቃ ለሌላው የህይወት ዘመን ነው። በጎነትን በደም ልገሳ እንግለጽ!

❤ከአክብሮት ጋር❤

☑️ደብረብርሃን ደም ባንክ አገልግሎት

🎇🎆 - ‼️🎇🎆ደብረብርሃን ደም ባንክ:- በ2018 በጀት ዓመት ባስመዘገበው የላቀ አፈጻጸም ከአማራ ክልል ደም ባንኮች መካከል 3ኛ ደረጃን በመያዝ የዘመናዊ ኤሌክትሪክ ሞተር ሽልማት በማግኘቱ...
29/07/2026

🎇🎆 - ‼️🎇🎆

ደብረብርሃን ደም ባንክ:- በ2018 በጀት ዓመት ባስመዘገበው የላቀ አፈጻጸም ከአማራ ክልል ደም ባንኮች መካከል 3ኛ ደረጃን በመያዝ የዘመናዊ ኤሌክትሪክ ሞተር ሽልማት በማግኘቱ ከፍተኛ ደስታና ኩራት ይሰማናል።

👉ይህ ውጤት የጥቂቶች ጥረት ሳይሆን፣ በተቀናጀ ቡድናዊ ሥራ፣ በታማኝነት፣ በትጋት እና ሕይወት ለማዳን በተደረገ ያልተቋረጠ ቁርጠኝነት የተገኘ የጋራ ስኬት ነው።

በመሆኑም ለዚህ ክብር መሠረት የሆናችሁ፦
❤የደብረብርሃን ደም ባንክ ባለሙያዎችና ጠቅላላ ሠራተኞች፣
❤ሕይወትን በመታደግ የሰብዓዊነት አርአያ የሆናችሁ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች፣
❤ከጎናችን ሆናችሁ ያልተቋረጠ ድጋፍና ትብብር ላደረጋችሁ አጋር አካላት፣
ከልብ የመነጨ የእንኳን ደስ አላችሁ! እንዲሁም ከፍ ያለ ምስጋናችንን ማቅረብ እንወዳለን።

👉ይህ ሽልማት የእስካሁኑን ስኬት ብቻ የሚያሳይ ሳይሆን፣ ወደፊትም የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት፣ በጎ ፈቃደኛ የደም ልገሳን ለማጠናከር እና ብዙ ሕይወቶችን ለማዳን የሚያነሳሳን አዲስ ተስፋ ነው።

🤝በአንድነታችን ተጠናክረን፣ በትብብራችን ተስፋን እየፈጠርን፣ ሕይወትን ማዳን እንቀጥላለን!

በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ!

✅ለሚ፣ ደነባ፣ጫጫ፣ ሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር እና ደብረ ብርሃን ከተሞች ላይ በከፍተኛ ንቅናቄ በተዘጋጀው የደም ልገሳ መርሃ ግብር በአስደናቂ ሁኔታ በመሳካቱ በጎ ፈቃደኛ ለጋሾች፣ ፕሮግራሙ...
23/07/2026

✅ለሚ፣ ደነባ፣ጫጫ፣ ሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር እና ደብረ ብርሃን ከተሞች ላይ በከፍተኛ ንቅናቄ በተዘጋጀው የደም ልገሳ መርሃ ግብር በአስደናቂ ሁኔታ በመሳካቱ በጎ ፈቃደኛ ለጋሾች፣ ፕሮግራሙን ላዘጋጁ፣ ላስተባበሩ፣ ለደገፉ እንዲሁም በየደረጃው ለተሳተፉ ሁሉ ከልብ የመነጨ ክብርና ምስጋናችንን እናቀርባለን።

✅ደም መለገስ ቸርነት ብቻ ሳይሆን የሰው ሕይወትን የሚያድን ከፍተኛ ሰብዓዊ ተግባር ነው። እያንዳንዱ የተለገሰ የደም ከረጢት ለአደጋ ተጎጂዎች፣ ለወላድ እናቶች፣ ለቀዶ ሕክምና ታካሚዎች፣ እንዲሁም ለበርካታ የደም ፍላጎት ያላቸው ታካሚዎች አዲስ ተስፋና ሕይወት ይሰጣል።

✅ይህ ታላቅ ተሳትፎ የማህበረሰባችንን መተሳሰብ፣ መተጋገዝ እና አንድነት በግልጽ ያሳየ ተግባር ነው። በቀጣይም የደም ልገሳ በልዩ ዝግጅቶች ብቻ የሚከናወን ሳይሆን የሁሉም ዜጋ የመደበኛ ተግባርና የማህበረሰብ ባህል እንዲሆን ሁላችንም በትጋት ልንሰራ ይገባል።

✅"ደም መለገስ ሕይወትን መስጠት ነው።" ስለዚህ ዛሬ የጀመርነውን ይህን በጎ ባህል በማስቀጠል ነገ ብዙ ሕይወቶችን እናድን፤ የደም ልገሳንም የሁላችን የዘወትር ባህል እናድርገው።

✅በድጋሚ ለሁሉም ለጋሾች፣ ለአዘጋጆች፣ ለአስተባባሪዎች፣ ለአጋር ተቋማት እና ለመላው ማህበረሰብ ከልብ እናመሰግናለን። የእናንተ በጎ ተግባር ብዙ ሕይወቶችን አድኗል፤ ወደፊትም ተስፋን ማብራቱን ይቀጥላል።

✅ይህን ተሞክሮ ሁሉም አካላት/አካባቢዎች እንዲወስዱት/እንዲያሰፉት እንፈልጋለን።

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በልቼ ቀበሌ (05/11/2018) በተካሄደው የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ላይ ማህበረሰቡን በማንቀሳቀስ እና ደም በመለገስ ላሳያችሁት አስደናቂ ተሳትፎ 91✅ ዩኒት ደም...
12/07/2026

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በልቼ ቀበሌ (05/11/2018) በተካሄደው የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ላይ ማህበረሰቡን በማንቀሳቀስ እና ደም በመለገስ ላሳያችሁት አስደናቂ ተሳትፎ 91✅ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ ተችሏል።

ይህም ፕሮግራሙ ከመካሄዱ በፊት ምን ያክል ከፍተኛ ቅድመ-ዝግጅት እና ውጤታማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እንደተሰራ በተግባር ያሳየ ነው።

:

ለወገን ህይወት መታደግ ሲሉ ውድ ደማቸውን በነፃነት ለለገሱ የቀበሌው በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች በደም ባንካችን እና በህክምና ተጠቃሚዎች ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

:

መርሃ-ግብሩ በሚገባ ታቅዶ፣ ህዝቡ በንቃት እንዲሳተፍ ላስተባበራችሁ፣ ግንዛቤ ለፈጠራችሁ እና ለደገፋችሁን በሙሉ ያለን አክብሮት የላቀ ነው። የእናንተ ቅንጅት እና ጥረት ባይኖር ይህ ውጤት አይታሰብም ነበር።

ይህ የጀመራችሁት መልካም ተግባር እና አጋርነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሙሉ እምነታችን ነው።

ስላደረጋችሁት መልካም አስተዋጽኦ ሁሉ እናመሰግናለን!

ይህን ተሞክሮ ሌሎችም እንዲጋሩት እናሳስባለን።

ከታላቅ አክብሮት ጋር

የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ መርሀ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል!መርሀ ግብሩ በዛሬው (20/10/18) ዕለት በደማቅ ሁኔታ መከፈቱን ለክቡራን ደም ለጋሾቻችን በደስታ እናበስራለን።ይህ የደም ልገሳ...
28/06/2026

የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ መርሀ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል!

መርሀ ግብሩ በዛሬው (20/10/18) ዕለት በደማቅ ሁኔታ መከፈቱን ለክቡራን ደም ለጋሾቻችን በደስታ እናበስራለን።

ይህ የደም ልገሳ ንቅናቄ በሆስፒታል አልጋ ላይ ሆነው የእኛን እገዛ ለሚጠባበቁ እናቶች፣ ህጻናት እና የአደጋ ተጎጂዎች ትልቅ የተስፋ ብርሃን ነው።

ሁላችሁም ወደ ልገሳ ማዕከላችን በመምጣት የዚህ የተቀደሰ ተግባር አሻራችሁን እንድታርፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ፈቃደኛ ልብ እና ጥቂት ደቂቃዎች የአንድን ወገን ህይወት ሙሉ ያደርጋሉ!

ኑ! ዛሬውኑ ደም በመለገስ የ2019 በጀት ዓመትን በቸርነት እንጀምር!

ለእነዋሪ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት​ቅን የደም ልገሳ አስተባባሪ መምህራን እና ተማሪዎች፤​ሁልጊዜም በቅንነት ደም በመለገስ እና የልገሳ ዘመቻዎችን ግንባር ቀደም ሆናችሁ በማስተባበር ...
12/06/2026

ለእነዋሪ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት
​ቅን የደም ልገሳ አስተባባሪ መምህራን እና ተማሪዎች፤

​ሁልጊዜም በቅንነት ደም በመለገስ እና የልገሳ ዘመቻዎችን ግንባር ቀደም ሆናችሁ በማስተባበር በደም እጦት የተቸገሩ ታካሚዎች እንዲድኑ ስለምታግዙ ከልብ እናመሰግናለን።
​ለታመሙ ወገኖቻችን ህይወት ለመታደግ ለምታደርጉት መልካም አስተዋጽኦ እና ለምታሳዩት አጋርነት ያለንን ምስጋና እንገልጻለን።
​ስለ መልካም ስራችሁ እናመሰግናለን!

 /ቤትርዕሳነ መምህራን እና መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች በሙሉሁልጊዜም በቅንነትና በቁርጠኝነት ግንባር ቀደም በመሆን ለምታደርጉት የደም ልገሳ ማስተባበር እና የህይወት አድን ስራ ከልብ የመነ...
09/06/2026

/ቤት
ርዕሳነ መምህራን እና መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች በሙሉ
ሁልጊዜም በቅንነትና በቁርጠኝነት ግንባር ቀደም በመሆን ለምታደርጉት የደም ልገሳ ማስተባበር እና የህይወት አድን ስራ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
​በትምህርት ቤትዎ ውስጥ እውቀትን ብቻ ሳይሆን፣ ሰብአዊነትንና ለወገን መድረስን በተግባር መማር_ማስተማር ለምታሳዩት አርአያነት ትልቅ ክብር አለን። የእናንተ ቸርነትና በእያንዳንዷ ዘመቻ የምታፈሱት የህይወት ጠብታ ለብዙዎች ተስፋና ፈገግታ ሆኗል።
​ለላቀ ሰብአዊነታችሁ እና ለቀጣይ አጋርነታችሁ ምስጋናችን አያልቅም!
​“ደም መለገስ ህይወትን መታደግ ነው!”

ለፊታውራሪ ገበየሁ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት​​የትምህርት ቤታችሁ መጠሪያ የሆነው የጀግናው የፊታውራሪ ገበየሁ ስም የሀገር ፍቅርና የጀግንነት ምልክት ነው። እናንተም ዛሬ በጦር ሜዳ ...
08/06/2026

ለፊታውራሪ ገበየሁ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት

​የትምህርት ቤታችሁ መጠሪያ የሆነው የጀግናው የፊታውራሪ ገበየሁ ስም የሀገር ፍቅርና የጀግንነት ምልክት ነው። እናንተም ዛሬ በጦር ሜዳ ሳይሆን በሰብአዊነት አደባባይ፣ ለወገን ደም በመለገስ ያንን ታላቅ የጀግንነት ታሪክ በተግባር እያደሳችሁት ትገኛላችሁ።
​ሁልጊዜም የደም ልገሳ ጥሪን በቅንነት ተቀብላችሁ፣ ግንባር ቀደም በመሆን ለምታሳዩት አጋርነት እና ለምታበረክቱት የህይወት ስጦታ ታላቅ ክብርና ምስጋና አለን። የእናንተ ፈቃደኛ ልብ በቃሬዛ ላይ ላሉ ብዙ ወገኖቻችን ዳግም የመኖር ተስፋ ሆኗል።
​ስለ እያንዳንዱ የህይወት ጠብታ እና ስለ ድንቅ አርአያነታችሁ ከልብ እናመሰግናለን!

አሁን ተጀምሯል! ፈጥነው ይድረሱ! 🩸​"የእርስዎ ጥቂት ደቂቃ... ለአንድ ወገን ሙሉ ሕይወት ነው!"​በደም እጥረት ለሚሰቃዩ ወገኖቻችን የመዳኛ ጊዜው አሁን ነው። ደብረ ብርሃን ደም ባንክ ከ...
07/06/2026

አሁን ተጀምሯል! ፈጥነው ይድረሱ! 🩸
​"የእርስዎ ጥቂት ደቂቃ... ለአንድ ወገን ሙሉ ሕይወት ነው!"
​በደም እጥረት ለሚሰቃዩ ወገኖቻችን የመዳኛ ጊዜው አሁን ነው። ደብረ ብርሃን ደም ባንክ ከማኅበረ ቅዱሳን ደብረ ብርሃን ማዕከል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ልዩ የደም ልገሳ መርሃ ግብር አሁን መጀመሩን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው።
​📍 ቦታ፦ በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ሕንጻ ዋና በር መግቢያ ላይ
​⏰ ሰዓት፦ አሁን ተጀምሮ ቀኑን ሙሉ ይቀጥላል!
​ኑ! የአንድን ወገን ሕይወት እንታደግ!

Address

Debre Birhan

Telephone

+251116811906

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Birhan Blood Bank Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share