Debre Markos city communication

Debre Markos city  communication ዓላማው ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃን ለህዝብ ማድረስ ነው።

🚜🌱 የአፈር ማዳበሪያ ችግር እንዳያጋጥም በትኩረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።በአማራ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በማረስ...
04/06/2026

🚜🌱 የአፈር ማዳበሪያ ችግር እንዳያጋጥም በትኩረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በአማራ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በማረስ ከ205 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ሰብል ለማምረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኀላፊ አጀበ ስንሻው ለአሚኮ ገልጸዋል።

ዕቅዱን ለማሳካት ደግሞ የአፈር ማዳበሪያ እና የምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ በትኩረት እየተሠራ እንደኾነ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

🌱🚜 ክልሉ በዚህ ዓመት፦

🚜 8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ ለማስገባት አቅዷል። ከዚህ ውስጥ 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የሚኾነው የክልሉ የአፈር ማዳበሪያ ዕቅድ ወደብ ላይ ደርሷል።

🚜 3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል የሚኾነው የአፈር ማዳበሪያ ደግሞ ወደ ክልሉ ተጓጉዞ ደርሷል። ከባለፈው ዓመት ተርፎ የነበረ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት ክልሉ ውስጥ መኖሩን አንስተዋል።

🚜 በጥቅል 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ለሥርጭት ቀርቧል። እስከ አሁን ባለው ጊዜም አርሶአደሮች ገዝተው የወሰዱት እና የተሠራጨው 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንደኾነ ተናግረዋል።

ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ አፈጻጸም እንዳለው ነው የገለጹት። ለስርጭት የቀረበው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ቀድመው ከሚዘሩ ሰብሎች አኳያ በጥሩ የሚታይ እንደኾነም አንስተዋል።

🌱 በሌላ በኩል፦
🚜 220 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች ለማቅረብ ታቅዷል።
እስከ አሁን ባለው ጊዜ 208 ሺህ ኩንታል የሰብል ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት ድልድል ተደርጓል።

🚜 72 ሺህ ኩንታል የሚኾነው የሰብል ምርጥ ዘርም ተሠራጭቷል።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በደጅ አዝማች ተድላ ጓሉ ክፍለ ከተማ የአለም አካባቢ ቀን አከባበርን ምክንያት በማድረግ "የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን እንግታ" በሚል መሪ ሃሳብ የተለያዩ...
04/06/2026

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በደጅ አዝማች ተድላ ጓሉ ክፍለ ከተማ የአለም አካባቢ ቀን አከባበርን ምክንያት በማድረግ "የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን እንግታ" በሚል መሪ ሃሳብ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በፅዳት ዘመቻ ተከብሯል።

በፅዳት ዘመቻው የተገኙት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፅዳትና ውበት አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ቸርነት አለማየሁ የዘንድሮውን የአለም አካባቢ ቀን ስናከብር አሁን ላይ እየገጠመን ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በመረዳት ችግሩን ሊቀለብስ የሚችል የተለያዩ ተግባራትን በመፈፀም ሊሆን ይገባል ብለዋል።

በፅዳት ዘመቻው የመምሪያ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች፣ ባለሙያዎች ፣ በጎ ፈቃደኞ ወጣቶች እንዲሁም የደረቅ ቆሻሻ አንሽ ማህበራትና የምግብ ዋስትና ሰሪ ሀይሎች ተሳትፈዋል።

መረጃው የከተማ አስተዳደሩ ፅዳትና ውበት አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ፅ/ቤት ነው።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
‎ቴሌግራም https://t.me/dmcomunicationoffice
‎ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php id=100064865823018
‎ቲክቶክ www.tiktok.com/
ዩቲብ:https://youtube.com/...

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት የቅድመ በጀት ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።********ግንቦት27/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን:የደብረ ማር...
04/06/2026

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት የቅድመ በጀት ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።
********
ግንቦት27/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን:የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የቅድመ በጀት ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

​የከተማችንን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥና የህዝባችንን መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ይፋዊ የቅድመ በጀት ውይይት ማካሄድ ይገባል ሲሉ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ መኮነን ሙሉአዳም ገልፀዋል።

ይህ መድረክ የበጀት ዝግጅቱ ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና አሳታፊነትን የተላበሰ እንዲሆን ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ስለመሆኑ የገለፁት ደግሞ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ ኀላፊ አቶ ታሪኩ ታደሰ ናቸው።

በመድረኩ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ መኮነን ሙሉአዳምን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ የመምሪያ፣የክፍለ ከተማ የተቋማት የስራ ኀላፊወች፣ የየተቋማቱ የዕቅድ ባመለያወች እና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
‎ቴሌግራም https://t.me/dmcomunicationoffice
‎ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php id=100064865823018
‎ቲክቶክ www.tiktok.com/
ዩቲብ:https://youtube.com/...

የሲቪልና ቤተሰብ  ምዝገባ   የበጀት ዓመቱ የስራ አፈፃፀም ግምገማ እና የዕቅድ ኦረንቴሽን መድረክ ተካሄደ፡፡*********ግንቦት26/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን):የደብረ ማርቆስ ...
03/06/2026

የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የበጀት ዓመቱ የስራ አፈፃፀም ግምገማ እና የዕቅድ ኦረንቴሽን መድረክ ተካሄደ፡፡
*********
ግንቦት26/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን):የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ቡድን የ4ኛውን ሩብ ዓመት የምዝገባ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የአብይና የቴክኒክ ኮሜቴዎች ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ማጠቃለያ ወራት የልደት፣የጋብቻ፣ ሞትና ፍች ምዝገባዎችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ ሰፊ ጥረት መደረጉን በሪ ፖርቱ ተመላክቷል።

በበጀት አመቱ የተመዘገቡ የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ሞትና ጉዲፍቻ በአምስቱም የኩነት አይነቶች 171% መፈፀም መቻሉን በሪፖርት ቀርቧል።

ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር የተደረገው ቅንጅታዊ አሰራር የግንዛቤ ፈጠራ ላይ ከዚህ በፊት ከነበረው አፈፃፀም ከ91% ወደ 101% አፈፃፀም መድረስ ተችሏል ሲሉ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ቡድን መሪ ወ/ሮ ሰላም ዙርባቸው በሪፖርቱ አመላክተዋል።

​አንድ ከተማም ሆነ ሀገር የወደፊት የልማት፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ዕቅዶቹን በአግባቡ ቀርጾ ለመንቀሳቀስ አስተማማኝና ዘመናዊ የሕዝብ መረጃ ሊኖረው ይገባል ያሉት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የፕላን መምሪያ ሃላፊ አቶ ማማሩ ገድፍ ገልፀው፤ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ (ልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺና ሞት) የዚሁ ስትራቴጂካዊ መረጃ መገኛ መሠረት ነው ብለዋል።

የመምሪያ ሃላፊ አክለው በከተማ የዲጂታል ምዝገባ ሥርዓትን በማጠናከርና አገልግሎቱን ተደራሽ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ሲሉም ተናግረዋል።

በቀጣይ ጊዜያት ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት አገልግሎት አሰጣጥን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታልና ዘመናዊ አሠራር ለማሸጋገር ትኩረት ተሰጦ ይሰራል ሲሉ ሃላፊው ገልፀዋል።

ዜጎች ኩነቶች በተከሰቱ የጊዜ ገደብ ውስጥ የመመዝገብ ባህላቸው እንዲያሳደርጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ጥንካሬዎች አጠናክረው እንደሚቀጥሉና የታዩ ድክመቶች በማረም ትኩረት ሰጠው እንደሚሰሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስተያየታቸውን ሰጠዋል ።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
‎ቴሌግራም https://t.me/dmcomunicationoffice
‎ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php id=100064865823018
‎ቲክቶክ www.tiktok.com/
ዩቲብ:https://youtube.com/...

❄️‎በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በንጉስ ተክለ ሀይማኖት ክፍለ ከተማ በሳምንቱ የተከናወኑ ፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም የፀጥታ ስራዎችን ግምገማዊ ውይይት ተካሄደ ።‎****...
03/06/2026

❄️‎በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በንጉስ ተክለ ሀይማኖት ክፍለ ከተማ በሳምንቱ የተከናወኑ ፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም የፀጥታ ስራዎችን ግምገማዊ ውይይት ተካሄደ ።
‎********
‎ በንጉስ ተክለሀይማኖት ክፍለ ከተማ የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፀጥታ ሥራዎች እና በቀጣይ በትኩረት በሚሹ ተግባራት ዙሪያ ግምገማዊ ውይይት ተካሄደ።
በዉይይቱ የከተማ ደጋፊ አመራሮች የክፍለ ከተማ እና የቀበሌ አመራሮች ተሳትፍዋል።
መረጃው የክፍለ ከተማው ህዝብ ግንኙነት ነው

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት የ4ኛው ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው።**********ግንቦት 26/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽ...
03/06/2026

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት የ4ኛው ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው።
**********
ግንቦት 26/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን):የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛው ሩብ ዓመትና የዓመቱ ማጠቃለያ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።

​በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩና የየቀበሌው የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን፥ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የልደት፣ የጋብቻ፣ የፍቺና የሞት ኩነቶች ምዝገባ አፈጻጸም፣ የሰነድ አያያዝ ጥራት እና የህዝብ እርካታ ደረጃ በዝርዝር እየተገመገመ ይገኛል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
‎ቴሌግራም https://t.me/dmcomunicationoffice
‎ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php id=100064865823018
‎ቲክቶክ www.tiktok.com/
ዩቲብ:https://youtube.com/...

 #የሰቆጣ ቃልኪዳን ምን እንደሆነ ያውቃሉ?የሰቆጣ ቃልኪዳን (Seqota Declaration) በኢትዮጵያ በሕፃናት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር (Stunting) እና የስርዓተ-ምግብ እጥረትን ...
03/06/2026

#የሰቆጣ ቃልኪዳን ምን እንደሆነ ያውቃሉ?
የሰቆጣ ቃልኪዳን (Seqota Declaration) በኢትዮጵያ በሕፃናት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር (Stunting) እና የስርዓተ-ምግብ እጥረትን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት በነሐሴ ወር 2007 ዓ.ም (እ.ኤ.አ ጁላይ 2015) ይፋ የተደረገ ከፍተኛ አገራዊና መንግስታዊ ስምምነት ነው።
ይህ ቃልኪዳን የተሰየመው በወቅቱ በድርቅ እና በምግብ እጥረት ክፉኛ ተጎድቶ በነበረው የዋግ ኽምራ ዞን ዋና ከተማ ሰቆጣ ላይ በመፈረሙ ነው።
ስለ ሰቆጣ ቃልኪዳን ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
1. ዋናው ግብ
የቃልኪዳኑ ዋነኛ ዓላማ እድሜያቸው ከሁለት ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር ሙሉ በሙሉ (ዜሮ) ማድረስ ነው።
ረሃብን ማስወገድ፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እና የስርዓተ-ምግብ አቅርቦትን ማሻሻል ላይ ያተኩራል።
2. የትግበራ ስልት (ቅንጅታዊ አሰራር)
ይህ መርሃ-ግብር በአንድ መሥሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ 9 ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች (ለምሳሌ፦ ጤና፣ ግብርና፣ ውሃና ኢነርጂ፣ ትምህርት፣ የመንግስት ኮምኒኬሽን ፣ገንዘብ... ወዘተ) ቅንጅት የሚመራ ነው። ይህም ምግብ-ነክ የሆኑ (Nutrition-specific) እና ምግብ-ነክ ያልሆኑ ነገር ግን ተፅዕኖ ያላቸውን (Nutrition-sensitive) ለምሳሌ እንደ ንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና የጓሮ አትክልት ልማትን ያጠቃልላል።
3. የተመዘገቡ ውጤቶች
በኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲቲዩት (EPHI) እና በተለያዩ አጋር ድርጅቶች የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ይህ ቃልኪዳን በተገበረባቸው ወረዳዎች በርካታ ሺህ ሕፃናትን ከመቀንጨር እንዲሁም ከሞት መታደግ ተችሏል። በተለይም ነፍሰ-ጡር እናቶች፣ ወላዶች እና ሕፃናት የዶሮ፣ የፍየል እንዲሁም የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ድጋፎችንና ግንዛቤዎችን እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ይገኛል።
የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደርም ከየካቲት/2018 ዓ.ም ጀምሮ ከግብርና፣ ከጤና ፣ከትምህርት ፣ከእንሰሳት ሃብት፣ ከውሃ፣ሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ፣ከንግድና ገበያ ልማት፣ከኢንቨስትመንት፣ከፕላን ልማት፣ከሃይማኖት ተቋማት እና ከኮምኒኬሽን መምሪያ ጋር ተቀናጅቶ ወደ ስራ በመግባት ለበርካታ አጥቢና ነፍሰጡር እናቶች፣ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እና ለትምህርት ተቋማት የግንዛቤ ፈጠራ ስራ የተሰራ ሲሆን ከግንዛቤ ፈጠራ ስራ ባሻገርም የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም የዶሮ ስርጭት በማድረግ ልዩ ልዩ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል ፡፡
ስለሆነም ስለ ሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም በቅድሚያ ራሳችን አውቀን በመቀጠል ለሌሎች ወላጅ እናቶች በማሳወቅ የከተማችንን የህጻናትን መቀንጨር ችግር ልናስወገድ ይገባል መልዕክታችን ነው፡፡
መቀንጨርን እንከላከል ሁላችን !
በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮምኒኬሽን መምሪያ የተዘጋጀ
ግንቦት/2018 ዓ.ም

❝የሚሊሻ ኃይላችን ባለፉት 30 ዓመታት የተጓዘበት መስመር የጀግንነት፣ የራስን ጥቅም ለሕዝብ አሳልፎ የመስጠት እና ታላቅ ሕዝባዊነት የተንጸባረቀበት ስኬታማ ጉዞ ነው!❞ ኮሚሽነር አስቻለው አ...
03/06/2026

❝የሚሊሻ ኃይላችን ባለፉት 30 ዓመታት የተጓዘበት መስመር የጀግንነት፣ የራስን ጥቅም ለሕዝብ አሳልፎ የመስጠት እና ታላቅ ሕዝባዊነት የተንጸባረቀበት ስኬታማ ጉዞ ነው!❞ ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ

የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከበረውን 30ኛ ዓመት የክልሉ ሚሊሻ የምስረታ በዓልን በማስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ እንደተናገሩት የክልሉ ሚሊሻ ሰራዊት በክልል ደረጃ ከተመሰረተ 1988 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሶስት አስርተ ዓመታት ረጅም የጀግንነት፣ የራስን ጥቅም ለህዝብ የመስጠትና የህዝባዊነት ጉዞን አሳልፏል ብለዋል።

ባለፉት 30 ዓመታት የክልሉ ሚሊሻ መደበኛ ስራውን ሳያስተጓጉል በአንድ እጁ አምራች በሌላ እጁ ደግሞ የሰላም ዘብ በመሆን የውስጥ ባንዳዎችን ከመታገል እስከ ታሪካዊ የውጭ ጠላቶቻችን አደብ በማስያዝ እስከ ህይወት መስዕዋትነት የዘለቀ ገድል ሲፈፅም ቆይቷል እየፈፀመም ይገኛል ሲሉ ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ በሰጡት መግለጫ አብራርተዋል።

እንደ ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ ገለጻ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከበረውን 30ኛ ዓመት የአማራ ክልል ሚሊሻ የምስረታ በዓልን ስናከብር የሚሊሻውን ታሪካዊ ተጋድሎ እና መስዕዋትነት ለመዘከር፣ ለሚሊሻ አባላት እና ለቤተሰቦቻቸው ክብርና ምስጋና ለማቅረብ፣ ተቋማዊ ሪፎርም እና ዝግጁነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም የህብረተሰቡን እና የሚሊሻውን ትስስር ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

"የሚሊሻ ኃይላችን ባለፉት 30 ዓመታት የተጓዘበት መስመር የጀግንነት፣ የራስን ጥቅም ለሕዝብ አሳልፎ የመስጠት እና ታላቅ ሕዝባዊነት የተንጸባረቀበት ስኬታማ ጉዞ ነው!" ሲሉ ኮሚሽነሩ አስቻለው አላምሬ አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።

የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ተቋማዊ አደረጃጀቱን እና አቅሙን ከዘመኑ የፀጥታ ስጋቶች ጋር ለማስማማት ሰፊ የሪፎርም ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱንም ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።

ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ አክለውም 30ኛ ዓመት የአማራ ክልል ሚሊሻ የምስረታ በዓሉ በአብዛኛው ዞንና ወረዳ ቀድሞ የተከበረ ሲሆን በክልል ደረጃም ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም "የጀግንነት ታሪካችንን እያደስን፤ ዝግጁነታችንን እናረጋግጣለን!" በሚል መሪ ቃል እንደሚከበር ጠቁመዋል።

ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ፣ ህግና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን ማክበርና ማስከበር፣ የክልሉን ህዝብ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ማድረግ የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን በቀጣይ ከሚሰራቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል ተጠቃሽ ናቸውም ነው ያሉት ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው።

በመጨረሻም ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ ለሚሊሻ ተቋሙ መጎልበትና ለክልላችን ህዝብ ሰላም ሲሉ ዘርፈ ብዙ መስዕዋትነት ለከፈሉ የሚሊሻ አባላትና ቤተሰቦቻቸው፣ ለመላው የክልሉ ማህበረሰብ እና ሌሎች የክልሉና የፌዴራል የጸጥታ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በግብርና ፕሮጀክት ዘርፍ ለመሰማራት ጥያቄ ያቀረቡ ባለሃብቶች የተሟላ እውቀትና ክህሎት ኑሯቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማድረግ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።*******************ግን...
03/06/2026

በግብርና ፕሮጀክት ዘርፍ ለመሰማራት ጥያቄ ያቀረቡ ባለሃብቶች የተሟላ እውቀትና ክህሎት ኑሯቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማድረግ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።
*******************
ግንቦት 26/2018ዓ.ም(ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን): በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በግብርና ፕሮጀክት ዘርፍ በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ጥያቄ ያቀረቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ በሚገቡበት ሁኔታ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በውይት መድረኩ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተመስገን ተድላ፣ ፕሮጀክት ያቀረቡ ባለሃብቶችና የሚመለከታቸው የተቋሙ ሰራተኞች እየተሳተፉ ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
‎ቴሌግራም https://t.me/dmcomunicationoffice
‎ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php id=100064865823018
‎ቲክቶክ www.tiktok.com/
ዩቲብ:https://youtube.com/... See

የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት፣ ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ በጋራ ባወጡት መግለጫ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ያደነቁ ሲሆን፤ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት፣ ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ በጋራ ባወጡት መግለጫ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ያደነቁ ሲሆን፤ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለእጩዎችና ለሲቪል ማኅበራት ለምርጫው ስኬት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እንዲሁም ለአፍሪካ ኅብረትና ለኢጋድ የምርጫ ታዛቢነት ሚና እውቅና ሰጥተዋል።

FDRE Government Communication Service-በኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

Address

Debre Mark'os
381

Telephone

+251587714141

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Markos city communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share