06/09/2026
መቀነት የሴቶች ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር 4ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል።
ጳጉሜ 1/2018ዓ.ም (ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን): በደብረ ማርቆስ ከተማ የሚገኘው መቀነት የሴቶች ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር 4ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን "በመቀነታችን እንቆጥባለን፤ ተባብረን እናድጋለን፤ባንካችንን እንገነባለን"! በሚል መሪ መለዕክት አባላቱ፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።
በዕለቱም አጠቃላይ የኦዲት ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ቀርቦ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በተጨማሪም ማህበሯን ለማሳደግ የሚያግዙ አዳዲስ ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጓል።
የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተቋቋመችው መቀነት የሴቶች ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ከተመሰረተችበት ጊዜ ጀምሮ የሴቶችን ቁጠባ በማበረታታት፣ የብድር አገልግሎት በመስጠትና ሌሎች የአባላቷን በተለይም የሴቶችን የፋይናንስ አቅም የሚያሳድጉ በርካታ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የማህበሩ ሰብሳቢ ወ/ሮ ስንታየሁ ከበደ ተናግረዋል።
ማህበሩ ከሶስት ዓመት በፊት በ 43 አባላት
በ 76ሺ ብር ተጀምሮ በአሁኑ ሰዓት የአባላቱን ቁጥር 143 በማድረስ የካፒታል መጠኑንም ከ2.4 ሚሊየን ብር በላይ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።
ከአባላቱ መካከልም 126ቱ ሴቶች መሆናቸውን ገልፀዋል።
2019 በጀት ዓመትም 200 አዳስ አባላትን በማፍራት ማፍራትየቁጠባ መጠንን ለማሳደግ ከአባላት 8ሚ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገለፁት ሰብሳቢዋ ከተለያዩ የገንዘብ ማግኛ ምንጮች አጠቃላይ ካፒታሉን 13ሚሊየን500ሺ በማድረስና 11 ሚሊየን ብር በማበደር ከ1ሚሊየን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ለማግኘት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።
ለንግድ ማስፋፊያ፣ ለመኖሪያ ቤት፣ ለባጃጅ መግዣ፣ለቤት ቁሳቁስ መግዣ፣ ለአደጋ ጊዜና ለልዩ ብድር በአጭር ጊዜ ለማበደር መታቀዱንም ወ/ሮ ስንታየሁ ገልፀዋል።
አስተያይታቸውን የሰጡ የማህበሩ አባላት በኦዲት የታዩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠልና የተሰጡትን ክፍተቶች በማረም ማህበሩን ለማሳደግ በትብብር መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ቴሌግራም https://t.me/dmcomunicationoffice
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php id=100064865823018
ቲክቶክ www.tiktok.com/
ዩቲብ:https://youtube.com/?si=h8-iiu60Df-Te3qJ