Debre Tabor Communication

Debre Tabor  Communication this page is create to address honest information for society

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ  ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ...
02/06/2026

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

"ምርጫው የኢትዮጵያን የወደፊት የዴሞክራሲ አቅጣጫ ያመላከተ ነው" ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማ መንገድ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።...
02/06/2026

"ምርጫው የኢትዮጵያን የወደፊት የዴሞክራሲ አቅጣጫ ያመላከተ ነው" ምርጫ ቦርድ

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማ መንገድ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

ቦርዱ በአሁኑ ሰዓት የድምጽ መቁጠር እና የማረጋገጥ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጿል።

የቦርዱ ሠብሣቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ በጋዜጣዊ መግለጫው
የምርጫ ሂደቱ ውጤታማ እና የኢትዮጵያን የወደፊት የዴሞክራሲ ሂደት የሚያመላክት ስኬት የተመዘገበበት መኾኑን ነው የገለጹት።

የምርጫ ውጤቱን ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ወደ ምርጫ ክልሎች፣ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ወደ ማዕከላዊ ቋት ከላኩ በኋላ ምርጫ ቦርድ የማረጋገጥ ሥራ አከናውኖ አጠቃላይ ውጤቱን ይፋ የሚያደርግ ይኾናል ነው ያሉት ሠብሣቢዋ።

Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

02/06/2026
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና መስጫ ቀናትን ይፋ አደረገ። ባሕር ዳር፡ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም  ...
02/06/2026

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና መስጫ ቀናትን ይፋ አደረገ።

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች የሚሰጡበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት የ6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 08 እስከ ዐ9/2018 ዓ.ም ይሰጣል። የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ክልላዊ ፈተናውን እንደሚወስዱ ነው ከትምህርት ቢሮው የተገኘ መረጃ የጠቆመው።

Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጥሩ መንገድ መጠናቀቁን የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡የፀጥታ አካሉ ከማህበረሰቡ ጋር ሁኖ በሰራው ስራ በከተማ አስተዳደሩ የተካሄደው አገራዊ...
02/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጥሩ መንገድ መጠናቀቁን የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡

የፀጥታ አካሉ ከማህበረሰቡ ጋር ሁኖ በሰራው ስራ በከተማ አስተዳደሩ የተካሄደው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሰላማዊ በሆነ አግባብ መጠናቀቁንም መምሪያው አስታውቋል፡፡

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ያለው ዘለቀ እንዳሉት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በአግባቡ እንዲካሄድ ለማድረግ በትኩረት ተይዞ ሲሰራ መቆየቱን እና ሰፊ ዝግጅት መደረጉን አንስተው የፀጥታ ሀይሉ ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ ሁኖ በተሰራው ስራ ምርጫው በጥሩ መንገድ መጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡

ጽንፈኛ ሀይሉ ምርጫውን ለማደናቀፍ ሙከራ ቢያደርግም በጥምር ጦሩ የተቀናጀና የተደራጀ ስራ እንዲሁምም በህብረተሰቡ እገዛ ያሰበውን ሳያሳካ መመለሱን ጠቁመው ህዝቡም የነበረው ሁኔታ ሳይበግረው በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ለመስጠት ያሳየው ቁርጠኝነትና ፍላጎት ይበል የሚያሰኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሀላፊው አክለውም የጥፋት ሀይሉ መንግስት እንዳይኖር እና ሰላም እንዳይመጣ ለማድረግ እኩይ ተግባር ቢፈጽምም ማህበረሰቡ መንግስት ያስፈልገናል በማለት መንግስትን በመመስረት ሰላምን ለማጽናት ምርጫው ሰላማዊ ሁኖ እንዲጠናቀቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልፀዋል፡፡

ካለ ማህበረሰቡ ተሳትፎና እገዛ ሰላምን ማምጣት እና ፀጥታን ማረጋገጥ የሚቻል አለመሆኑንም ተናግረው የከተመዋ ህብረተሰብ እያደረገ ባለው ሁለንተናዊ ተሳትፎና እገዛ አንጻራዊ ሰላም እንዲመጣ እና የተሻለ ፀጥታ እንዲኖር ማድረግ መቻሉን አንስተው ማህበረሰቡ እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ተሳትፎና እገዛ አጠናክሮ ማስቀጠል አለበትም ብለዋል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል የፀጥታ አካሉ በትኩረት ይዞ እየሰራ መሆኑንም ተናግረው ህብረተሰቡ አካባቢውን መጠበቅ እና መረጃ ለፀጥታ ሀይሉ ሊሰጥ እንደሚገባ አስገንዝበው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በመሰረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀል እየተፈፀመ በመሆኑ ወንጀሉን ለማስቆም ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ትብብርና እገዛ እንዲያደርግም የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ያለው ዘለቀ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

በደብረታቦር ከተማ በትናትነው እለት የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በጥሩ መንገድ እንዲጠናቀቅ ላደረጉት የፀጥታ አካላት እና ህዝቡ ምስጋና ቀርቧል፡፡

ደብረታቦር ኮሙኒኬሽን ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም

"ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የአማራ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ትልቅ ዋጋ ከፍሏል" በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤትበአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ...
02/06/2026

"ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የአማራ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ትልቅ ዋጋ ከፍሏል" በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል። ምክር ቤቱ የአማራ ሕዝብ ለዴሞክራሲ በከፈለው መሥዋዕትነት ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን አስታውቋል።

23 የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚገኙበት ይህ ምክር ቤት፣ ምርጫው በነፃነት እና ያለምንም ተጽዕኖ የተካሄደ እና ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ መሆኑን ገልጾ፣ ለመላው የአማራ ሕዝብ እና ለምርጫው ስኬት ድርሻ ለነበራቸው አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴሃን) ሊቀመንበር እና የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ እንደገለጹት፣ ምርጫው ዜጎች ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤትነታቸውን ያረጋገጡበት እና ለሀገራችን የዴሞክራሲ ልምምድ ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ ታሪካዊ ክስተት ነው።

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ተዓማኒ ሆኖ መከወኑን የገለጹት ሰብሳቢው፣ በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ብለዋል።

ሕዝቡ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በነቂስ ወጥቶ መሳተፉን እና "ይሆነኛል፤ ይበጀኛል" የሚለውን መምረጡን አቶ ተስፋሁን ጠቁመዋል። ምርጫውን ለማደናቀፍ ከውስጥም ከውጭም ጥረቶች ቢደረጉም፣ በጀግናው የፀጥታ ሠራዊት ማክሸፍ በመቻሉ ለሁሉም የፀጥታ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድኅረ-ምርጫ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን በፀጋ ለመቀበል ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን አቶ ተስፋሁን አሳስበዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።

ከምርጫ ማግሥት ለሀገር ሰላም እና ልማት መሥራት ይገባል።በደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የድምጽ ውጤት ይፋ አድርገዋል።  የከተማዋ ነዋሪዎችም በምርጫ ጣቢያዎች በመገ...
02/06/2026

ከምርጫ ማግሥት ለሀገር ሰላም እና ልማት መሥራት ይገባል።

በደብረ ታቦር ከተማ አሥተዳደር የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የድምጽ ውጤት ይፋ አድርገዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎችም በምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ጊዜያዊ የድምፅ ውጤቶችን እየተመለከቱ ነው።

ውጤቱን ሲመለከቱ ካገኘናቸው መካከል አቶ ልብሴነው መሥፍን እና ወይዘሮ እናንዬ ፈንታዬ የተካሄደው ምርጫ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንደነበር አንስተዋል።

ማኅበረሰቡ ከምርጫ ማግሥት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚያሳውቀውን ውጤት በጸጋ ተቀብሎ እና ከአሸናፊው ጎን ኾኖ ለሀገር ሰላም እና ልማት መሥራት አለበት ነው ያሉት።

ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ ሀገራቸውን ማስቀጠል እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።
ለኢትዮጵያ የሚገባትም ኾነ ለሕዝብ የሚበጀው ሰላማዊ ሂደት ነው ብለዋል።


#ኢትዮጵያ🇪🇹

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በከፍተኛ ስኬት፣  ሥልጡን ...
02/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በከፍተኛ ስኬት፣ ሥልጡን እና ሕዝባዊ ተሳትፎ በጎላበት መልክ በታላቅ የሕዝብ ድል መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ተወዳዳሪ የሌለው ሚና ለተጫወቱት የክልሉ ፖሊስ፣ ለጀግናዉ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል የጸጥታ እና የብሔራዊ ደኅንነት አካላት ፣ለክልሉ ሚሊሻ፣ ሰላም አስከባሪ እና ለመላዉ ሕዝብ ምስጋና አቅርቧል።

ሁልጊዜ ሰላም እና ልማትን ቀዳሚ የሚያደርገው የክልሉ ሕዝብ የምርጫ ካርድ ከመውሰድ ጀምሮ በምርጫው ዕለት በታላቅ ትዕግስት እና ሥነ ሥርዓት ድምፅ እስከመስጠት ድረስ ያሳየው ፍቅር እና ሀገር ወዳድነት የታሪክ ማህደር የማይረሳው መኾኑን ገልጿል።

በምርጫው ዕለት ኅብረተሰቡ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመውጣት በክልሉ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ያከናወነው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ያለምንም መሰላቸት እስከ ምሽት ሰአት መከናወኑን አረጋግጧል።

ኅብረተሰቡ ረጅም ሰልፎችን በታጋሽነት በመሰለፍ፣ የመምረጥ መብቱን በአግባቡ መጠቀሙ የሠለጠነ ዴሞክራሲያዊ ባሕሉን ያሳየበት እና ለምርጫው ስኬታማነት ትልቁን ድርሻ ያበረከተበት መኾኑንም ጠቁሟል።

ምርጫው የክልሉን ሕዝብ ብስለት፣ ሰላም ወዳድነት እና ለሀገር ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ዳግም ለዓለም ያስመሰከረበት ታሪካዊ ምዕራፍ መኾኑንም ዋና ጠቅላይ መምሪያው አመላክቷል።

የጸጥታ ኃይሉ ሂደቱን በበላይነት በመምራት፣ የእያንዳንዱን አካባቢ ኅብረተሰብ በተደራጀ እና በተቀናጀ መልኩ በማንቀሳቀስ፣ ከሕዝብ የተውጣጡ የሰላም ኮሚቴዎችን እና አደረጃጀቶችን ከራሱ የጸጥታ መዋቅር ጋር በማስተሳሰር የጋራ የሰላም ግንባር መፍጠር በመቻሉ ሰላሙን ማረጋገጥ መቻሉንም አስታውቋል።

ይህንን ሥራ ስኬታማ ለማድረግ የጸጥታ ኃይሉ አባላት ሌት ከቀን ያሳዩት ከፍተኛ ልፋት፣ ድካም እና ተጋድሎ በአንዳንድ ቦታዎች የምርጫውን ሂደት ለማደፍረስ እና ሁከት ለመፍጠር አልመው የተንቀሳቀሱ ሕገ ወጥ አካላትን የጥፋት ሴራ ቀድሞ በተዘጋጀ ስልታዊ የመከላከል እቅድ ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ መቻሉንም አመላክቷል።

የጸጥታ ኃይሉ የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ የመወጣት ጀግንነት፣ ሙያዊ ብቃት እና የገባውን ቃልኪዳን በታማኝነት በመፈጸም የሕዝቡን ደኅንነት በልዩ ጥንቃቄ የማስጠበቅ ሥራ፤ ከተቋማዊ ኩራት ባሻገር ለክልሉ እና ለሀገሪቱ ታላቅ ክብርን ያጎናጸፈ ተግባር በመኾኑ ላቅ ያለ ምስጋናና እውቅና ሰጥቷል ነው ያለው።

ምርጫውን ለማወክ የሞከሩ ማናቸውንም የጸረ ሰላም ኃይሎች የጥፋት አጀንዳ ሙሉ በሙሉ ያከሸፈ ታላቅ የሕዝብ ድል የተመዘገበው ሕዝቡ ያሳየው አስተዋይነት እና የሰላም ባለቤትነት ስሜት በመኖሩ እንደኾነም አንስቷል።

ለታሪካዊ ድሉ መገኘት ሕዝቡ ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም፣ መረጃዎችን በወቅቱ በመለዋወጥ እና ለሰላም ጥበቃው ግንባር ቀደም ጠባቂ በመኾን ያሳየው ጠንካራና የተቀናጀ ጥምረት ዋነኛ መሠረት ነበር ተብሏል።

በምርጫው ወቅት የታየውን መልካም የሕዝብ፣ የፖሊስ ቅንጅታዊ አሠራር እና አደረጃጀት ይበልጥ በማጠናከር የክልሉን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በቀጣይም በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቋል።

ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ለሲቪክ ማኅበራት፣ ለመገናኛ
ብዙኃን ተቋማት፣ ለውጭ እና የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች እና ለሰላም ወዳዱ ማኅበረሰብ በሙሉ ምስጋና አቅርቧል።

ከአማራ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የተጀመረውን የሰላምና የዴሞክራሲ ጉዞ በጋራ ለማስቀጠል የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እንደሚሠራም አስገንዝበዋል።

በደብረ ታቦር ከተማ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ ተደርጓል።
02/06/2026

በደብረ ታቦር ከተማ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ ተደርጓል።

በደብረ ታቦር ከተማ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ መሆን ጀምሯል።        ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም
02/06/2026

በደብረ ታቦር ከተማ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ መሆን ጀምሯል።

ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ/ም

Address

Debre Tabor

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Tabor Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share