04/08/2026
በክረምት የምትፈካ ታሪክ፣ተፈጥሮና ባህል የደመቁባት ባለታሪክ ከተማ፤
#ደብረታቦርን #በደብረታቦር!
(ቡሔ፣አሸንድዬ፣አድርሽኝና ደብረታቦር )
👉ደብረታቦርን በደብረታቦር በዓላት በውስጡ ደብረታቦርን፣አሸንድዬን፣ቡሔንና አድርሽኝ መንፈሳዊና ባህላዊ በዓላትን አቅፎ በታሪካዊቷ ደብረታቦር ከተማ ከነሐሴ 13 ጀምሮ የሚከበር በዓል ነው።
👉ይህ በዓል በደብረታቦር ከተማና በሌሎች አካባቢዎች በየአመቱ በድምቀት ይከበራል፡፡
👉የደብረ ታቦር መንፈሳዊ በዓል የተጀመረው የኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን በደብረ ታቦር ተራራ ከመግለጡ ጋር ተያይዞ ነው፡፡
👉የደብረ ታቦር ድምቀት የኾነው ቡሄ ማለት በራ፣ ብርሃን ኾነ፣ ደመቀ የሚል ትርጉም ያለው ነው፡፡
👉በቡሄ በዓል እናቶች ሙልሙል በመጋገር ለሕፃናት እና ለወጣቶች በማደል ያደምቁታል፡፡
👉በቡሄ በዓል በደብረ ታቦር ከተማ ከተገኙ ወጣትና ታዳጊዎች የደስታ ጅራፍ በማጮህ እና በብርሃነ መለኮቱ አምሳል ችቦ በማብራት በሚያሳዩት ትእይንት ይደሰታሉ፡፡
👉ሌላው በቡሄ በዓል በደብረ ታቦር ከሚታዩ ትእይንቶች መካከል እርስ በእርስ መጠያየቅ ሲኾን እናቶች እና አባቶች ለክርስትና ልጆቻቸው ያዘጋጁትን ሙልሙል ዳቦ በመስጠት በዓሉን ያደምቃሉ፡፡
👉ሌሎች የአሸንድዬ በዓል በልጃገረዶች ዘንድ የሚዘወተር የነጻነት በዓል።
👉አድርሽኝም በጎንደር ልዩ ቦታ የሚሰጠው ማህበራዊ ትስስርና መተሳሰብን የሚያጠናክር በዓል ነው።
በደብረ ታቦር ከተማ የቡሄ፣የአሸንድዬና የአድርሽኝ በዓላትን በጋራ እናክብር።
ደብረታቦር ኮሙኒኬሽን ሀምሌ 28 ቀን 2018 ዓ/ም