10/01/2026
።
ጥር 1 ቀን 2018 ዓ/ም
ፍ/ሠላም፣
በዞናችን የሚገኙ ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድ እድሳት ያለ ቅጣት የሚታደስበት ጊዜ ከሀምሌ 1 እስከ ታህሳስ 30 ብቻ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግን በነጋዴው ቸልተኝነት እና ከሲስተም ችግር ጋር ተያይዞ ነጋዴው የንግድ ፈቃዱን ሳያድስ በመቅረቱ ለቅጣት እንዳይዳረግ ታሳቢ በማድረግ ለ15 ቀን ብቻ የተራዘመ መሆኑን የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታውቋል።
የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድና ገበየ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለልኝ አሠፋ በዞናችን የምትገኙ ነጋዴዎች ፈቃድ አውጥታችሁ በመዘናጋት ያላሳደሳችሁ ነጋዴዎች በክልሉ አማካኝነት የተራዘመውን ጊዜ በመጠቀም ከሰኞ እስከ አርብ ዘወትር በስራ ሰአት እና ቅዳሜ እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ በወረዳ ደረጃ ወደ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ፈጥነው በመሄድ በማደስ ካላስፈላጊ ወጭና ቅጣት ራሳችሁን እንድትጠብቁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አክለዉም በዞናችን ውስጥ የምትገኙ ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድ ማደሻ ጊዜ ካሳለፋችሁ የንግድ ምዝገባ አዋጅ 980/2008 መሰረት በህግ ያስቀጣል፣ የንግድ ፍቃድ ያሰርዛል በማለት ጥብቅ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የቅጣቱን የገንዘብ መጠን እንደቆይታው ደረጃ በመጠን የተቀመጠውን የህግ ድንጋጌ ዝርዝር አመላክተዋል።
#1ኛ, ከጥር 1 እስከ 30 = 2,500 ብር
#2ኛ, ከየካቲት 1 እስከ 30 = 4,000 ብር
#3ኛ, ከመጋቢት 1 እስከ 30 = 5,500 ብር
#4ኛ, ከሚያዚያ 1 እስከ 30 = 7,000 ብር
#5ኛ, ከግንቦት 1 እስከ 30 = 8,500 ብር
#6ኛ, ከሰኔ 1 እስከ 30 = 10, 000 ብር እያለ ፈቃድ እስከ መሰረዝ ድረስ ስለሚያስቀጣ ፈቃደዎን በተሰጠው ጊዜ ብቻ በመጠቀም ፈጥነው ማሳደስ እንዳለባቸው የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለልኝ አሠፋ በድጋሜ ጥብቅ ማሳሠቢያ ሠጥተዋል ።