03/06/2026
#ደሴ ከተማ #ከምርጫ ድባብ ወደ #ልማት እምርታ ማስቀጠል ተግባር እነሆ ብላለች።
ለደሴ ከተማ ደጋፊ የተመደቡ የክልል አመራሮች ፣ የከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ እና ሌሎች አመራሮች የልማት ስራን ላፍታም ሳይቆም ማስቀጠል ስራ በማወጅ የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ቃሲም አበራ ስለመሰረተ ልማቱ ማብራሪያ ሲሰጡ ፤ ከሰላም ሆስፒታል በታች በወሎ ባህል አባ አዳራሽ ወጣት ማዕከል እስከ ሸል ያለው የኮሪደር ልማት ቀሪ ስራዎች አስፓልት ስራውን ጨምሮ በዚህ በጀት ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልፀዋል።
ይህን አስገራሚ የከተማችንን አይን ከፍች መንገድ ስራ በረጅሙ አስቦ ማስቀጠል አይቀሬ የቤት ስራችን ነው ፤ ያሉት የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሳሙዔል ሞላልኝ ናቸው።