Dessie City Administration Communication

Dessie City Administration Communication Government Organization works for Dessie city in Media and Communication areas.

 #ደሴ ከተማ  #ከምርጫ ድባብ ወደ  #ልማት እምርታ ማስቀጠል ተግባር እነሆ ብላለች። ለደሴ ከተማ ደጋፊ የተመደቡ የክልል አመራሮች ፣ የከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ እና ሌሎች አመራሮች የልማት...
03/06/2026

#ደሴ ከተማ #ከምርጫ ድባብ ወደ #ልማት እምርታ ማስቀጠል ተግባር እነሆ ብላለች።

ለደሴ ከተማ ደጋፊ የተመደቡ የክልል አመራሮች ፣ የከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ እና ሌሎች አመራሮች የልማት ስራን ላፍታም ሳይቆም ማስቀጠል ስራ በማወጅ የመስክ ምልከታ አድርገዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ቃሲም አበራ ስለመሰረተ ልማቱ ማብራሪያ ሲሰጡ ፤ ከሰላም ሆስፒታል በታች በወሎ ባህል አባ አዳራሽ ወጣት ማዕከል እስከ ሸል ያለው የኮሪደር ልማት ቀሪ ስራዎች አስፓልት ስራውን ጨምሮ በዚህ በጀት ዓመት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልፀዋል።

ይህን አስገራሚ የከተማችንን አይን ከፍች መንገድ ስራ በረጅሙ አስቦ ማስቀጠል አይቀሬ የቤት ስራችን ነው ፤ ያሉት የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሳሙዔል ሞላልኝ ናቸው።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"         ክቡር አረጋ ከበደየአማራ ክልል ርእ...
03/06/2026

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል"

ክቡር አረጋ ከበደ
የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት።የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ...
03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት።

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ የተሰማውን ደስታ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፀጥታ ኃይል አካላት እንዲሁም ሕዝቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተወጡት ሀገራዊ ኃላፊነት እና ላሳዩት ፅናትም ምክር ቤቱ ያለውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጿል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው፣ “ልዩነቶቻችንን እና ችግሮቻችንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመፈታት በምርጫው የታየውን ሰላም በማስቀጠል የበኩላችንን ሚና እንወጣ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ እንቁም” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

 #አንኳር"የሀገር ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በራስ አቅም ማምረት ሲቻል ነው" ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ #አሚኮ
03/06/2026

#አንኳር
"የሀገር ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በራስ አቅም ማምረት ሲቻል ነው" ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ
#አሚኮ

 #አንኳር "ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ #አሚኮ
03/06/2026

#አንኳር

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው ሕዝባችን ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል" ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
#አሚኮ

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፤ የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ  ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፤

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ያካሄደችው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት በስኬት በመጠናቀቁ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ብሏል።

ለዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ ለሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች፣ ለበጎ ፈቃደኞች፣ ለምርጫ አስፈጻሚዎች እና ምርጫው ስኬታማ እንዲኮን ጊዜያቸውን ለሰጡት ሁሉ ያላውን አድናቆት ገልጿል።

የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የታዛቢ ቡድኖች የነበራቸውን አስተዋጽኦ በበጎ እንቀበላለን ነው ያለው።

የአውሮፓ ኅብረትም ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መካሄዱን በደስታ እንቀበላለን ብሏል።

​ ለምርጫ መሳካት አስተዋጽዖ ያበረከቱትን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ዕጩ ተወዳዳሪዎችን እና የሲቪል ማኅበራት ተዋናዮችን ጥረት እናደንቃለን ነው ያለው።

​የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን ( ኢጋድ) እንደ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች የተጫወቱትን ወሳኝ ሚና እንገነዘባለን ብሏል። የታዛቢዎችን ሪፖርት በጉጉት እንደሚጠብቅም አስታውቋል።

​በግንቦት 24 ቀን ምርጫ ማካሄድ ያልቻሉ ሁሉም የምርጫ ክልሎች ምርጫውን የማካሄድ ዕድል እንደሚያገኙ ያለውን ተስፋም ገልጿል።

"7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ እና የምርጫ ዕድገት ሂደት ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተ ነው" የኢጋድ ታዛቢዎች ቡድን7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሲታዘቡ የሰነበቱት የአፍሪካ ኅብረት እና...
03/06/2026

"7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ እና የምርጫ ዕድገት ሂደት ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ የከፈተ ነው" የኢጋድ ታዛቢዎች ቡድን

7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሲታዘቡ የሰነበቱት የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ምርጫውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።

የቀድሞ የዩጋንዳ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድን መሪ ዋዲራ ሰፔሲዎሳ (ዶ.ር) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ እና የምርጫ ዕድገት ሂደት ውስጥ ትልቅ ምዕራፍን የከፈተ ነው ብለዋል።

ምርጫው በርካታ አዳዲስ አሠራሮች የታዩበት ምርጫ ተብሎ ይገለጻልም ነው ያሉት። ለዚህም ምክንያቱ መጠነ ሰፊ የኾኑ ተቋማዊ፣ አሥተዳደራዊ እና የቴክኖሎጂ ማሻሻያዎች ሥራ ላይ በመዋላቸው እንደኾነም አንስተዋል።

ዘርፈ ብዙ ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር በደሴ ከተማ የመጀመሪያ ዙር የደም ልገሳ አካሄደ።ደሴ፦ ግንቦት 26/2018ዓ.ም (ደሴ ኮሙኒኬሽን) ዘርፈ ...
03/06/2026

ዘርፈ ብዙ ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር በደሴ ከተማ የመጀመሪያ ዙር የደም ልገሳ አካሄደ።

ደሴ፦ ግንቦት 26/2018ዓ.ም (ደሴ ኮሙኒኬሽን)

ዘርፈ ብዙ ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር በ2012ዓ.ም ተመስርቶ ለበርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ አሰፋ ፈንታው ማህበሩ ከመደበኛ ስራው ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፤ በዋናነት ደም መለገስ የሰው ህይወትን ማዳን መሆኑን በመገንዘብ የዕለቱን ፕሮግራም በማዘጋጀት ማህበራዊ ሃላፊነታችንን ለመወጣት ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸው በቀጣይ ማህበረሰብ ተኮር ተግባራት ላይ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ደም እየለገሱ ካገኘናቸው አመራሮች መካከል የደሴ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ነስረዲን ሃይሌ እና የደሴ ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ ኢንተርፕራይዝ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ሽመልስ አበባው በሰጡት አስተያየት ደም መለገስ የሚችል ሁሉ ደም በመለገስ የእናቶችንና የወገኖችን ህይወት በመታደግ ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት ይገባል ብለዋል።

አንድም እናት በደም ማጣት ምክንያት ከሞት መታደግ ከፍተኛ የህሊና እረፍት እንደሚሰጥ የጠቆሙት ደምለጋሾች ይህንን ችግር ለመታደግ ሁሉም ሠው ሊተባበር እንደሚገባ ገልፀዋል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊ፣ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ። ያነጋገርናቸው የደሴ ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ እና በተረጋጋ መንፈስ ይበ...
03/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍትሐዊ፣ ሰላማዊ፣ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።

ያነጋገርናቸው የደሴ ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ እና በተረጋጋ መንፈስ ይበጀናል ያሉትን ፓርቲ በነፃነት መምረጣቸውን ተናግረዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡት ወይዘሮ መቅደስ ጋሸው የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ አላማና ፕሮግራም በመረዳት ድምፃቸውን መስጠታቸውን ተናግረዋል።

ምርጫ ቦርድ ይፋ በሚያደርገው ውጤት መሠረት ከሚመሠረተው መንግሥት ጋር ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ እንደሚሠሩም ገልፀዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ እንድሪስ መሀመድ እንደገለጹት ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ምርጫ ወሳኝ መኾኑን ጠቅሰው የከተማዋ ነዋሪዎች ለምርጫው ስኬት የዜግነት ኀላፊነታቸውን መወጣታቸውን ጠቅሰዋል።

የምርጫ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ዜጎች በጸጋ በመቀበል የዴሞክራሲ ባሕልን ሊያሳድጉ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ህይወት ተፈራ ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና በሠለጠነ መንገድ የተከናወነ እንደነበር አስታውሰዋል።

ምርጫዉ የሀገሪቱን የዴሞክራሲ ጉዞ ከፍ እንደሚያደርገዉም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የምርጫውን ውጤት በጸጋ መቀበል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግድ መኾኑን አስተያየት የሰጡን ደግሞ ወይዘሮ ሱሴ ዳምጠው ናቸው።

ከምርጫው በኋላ ከሚመሠረተው መንግሥት ጋር ሕዝቡ በልማት እና በሰላም ዙሪያ ተባብሮ መሥራት እንደሚገባም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ነዋሪዎቹ አሸናፊ ከሚኾነው ፓርቲ ጋር ለሀገር ልማት በትጋት ለመስራት ቁርጠኛ መሆን እንደሚገባም ጠቁመዋል።

Address

Dessi

Telephone

+25133111787

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dessie City Administration Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dessie City Administration Communication:

Share