Dessie City Administration Communication

Dessie City Administration Communication Government Organization works for Dessie city in Media and Communication areas.

የደሴ ከተማ የክረምት በጎፈቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ በሁሉም ክፍለ ከተማ በክረምት ወራት የተሠሩ ተግባራትን ክትትልና ድጋፍ አካሄዱ።የቴክኒክ ኮሚቴውም በ5ቱም ክፍለ ከተማው ውስጥ በሚገኙ የ17ቱን ...
05/09/2026

የደሴ ከተማ የክረምት በጎፈቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ በሁሉም ክፍለ ከተማ በክረምት ወራት የተሠሩ ተግባራትን ክትትልና ድጋፍ አካሄዱ።

የቴክኒክ ኮሚቴውም በ5ቱም ክፍለ ከተማው ውስጥ በሚገኙ የ17ቱን ቀበሌዎች በክረምት በጎፈቃድ የተሠሩ ተግባራት በመስክ ምልከታ የአዲስ ቤት ግንባታ እና ጥገና በተመለከተ፣ የተሠበሰቡ የትምህርት ቁሳቁስና አልባሳት፣ የትምህርት ቤት ጥገና ተግባራትን እና በቢሮ አጠቃላይ የተከናወኑ ተግባራትን የዶክመንት መረጃዎችን በማየት የክትትልና ድጋፍ ስራን አካሂደዋል።

በክትትልና ድጋፋ የታዩ ተግባራትን ቴክኒክ ኮሚቴው ለክፍለ ከተማው ስትሪክት ኮሚቴ በጥንካሬና በድክመት አንስተው ተወያይተዋል።

በየቀበሌው የተሠበሰቡ፣ ቃል የተገቡ የትምህርት ቁሳቁስን ወደ አንድ በማሠባሠብ በተደራጀ መንገድ ከተማ አስተዳደሩ በሚያስቀምጠው አቅጣጫ ለማሠራጨት እንዲዘጋጁ መልእክት አስተላልፈዋ።

ክፍለከተማውም የተሠጡትን አስተያየት በመቀበል በቀሪ ወራቶች የተጀመሩትን በመጨረስ እና የተሻለ ተግባራትን በመፈጸም የዜጎች በጎፈቃድ ተግባርን ለማሳካት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አደረገ፣ደሴ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ደሴ ኮሚኒኬሽን) ኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አዲሱን ዓመት ምክን...
05/09/2026

ኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አደረገ፣

ደሴ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (ደሴ ኮሚኒኬሽን) ኢትዮ ቴሌኮም የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ «በበጎነት» በሚል መሪ ቃል በደሴ ከተማ ለሚገኘው ምስክር የአረጋውያን መርጃ ማዕከል 1 ሚሊዮን 5 መቶ ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።

አሚኮ ያነጋገራቸው በማዕከሉ የሚገኙ አረጋዊያን ተገቢውን ድጋፍና እንክብካቤ እያገኙ እንደኾነ ገልፀዋል። ኢትዮ ቴሌኮም ላደረገላቸው ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የምስክር አረጋዊያን መርጃ ማዕከል ሥራ አሰኪያጅ ምስክር ሰይድ፣ ማዕከሉ ለተከታታይ 7 ዓመታት ከ150 እስከ 200 ለሚሆኑ አረጋውያን በየቀኑ የምግብ፣ የአልባሳትና የህክምና አገልግሎቶችን ሲሰጥ መቆየቱን ገልፀዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በዓልን ምክንያት በማድረግ ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ የማዕከሉን ክፍተት የሚሞላ በጎ ተግባር ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የደሴ ከተማ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የዜጎች በጎ ፈቃድ አስተባባሪ ይሄይስ ሀይሉ፣ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ158 ሺህ በላይ ወጣቶች እና የተለያዩ ዜጎችን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲሳተፉ ለማድረግ በመሠራቱ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሌሎችም ማህበረሰቡን በሚጠቅሙ ተግባራት መሳተፋቸውን አንስተዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም የአዲስ ዓመት ስጦታ የዚሁ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል መኾኑን የገለፁት አቶ ይሄይስ፣ በርካታ አረጋውያንን ተደራሽ የሚያደርግ የገንዘብ ድጋፍ በመኾኑ ሌሎች ተቋማትም መሰል ድጋፎችን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ኢትዮ ቴሌኮም ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ማስረሻ ገበየሁ፣ ኩባንያው ከሚሰጣቸው መደበኛ አገልግሎቶች ባሻገር በጤና፣ በትምህርት፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በሌሎች የበጎ አድራጎት ተግባራት በመሳተፍ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አኗኗር ሊያሻሽሉ የሚችሉ ሰው ተኮር ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ 492 ሚሊዮን ብር ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ድጋፍ ተደርጓል ነው ያሉት። በዚህ ዓመት ደግሞ «በበጎነት» በሚል መርሃ-ግብር 50 ለሚሆኑ ተቋማት ወደ 75 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ድጋፍ መደረጉን ገልፀዋል። በዚህ ተግባርም ወደ 22 ሺህ 200 የሚኾኑ ሴቶች፣ ህፃናት፣ አረጋዊያን እና አካል ጉዳተኞች ተጠቃሚ መኾናቸውን አስረድተዋል።

በዛሬው ዕለትም በምስክር አረጋውያን መርጃ ማዕከል ለሚገኙ አረጋውያን ለበዓል መዋያ የሚኾን 1 ሚሊዮን 5 መቶ ሺህ ብር ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

መሰል ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ወይዘሮ ማስረሻ ገልፀዋል።
አሚኮ ደሴ

ወንጀልን በጋራ በመከላከል አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ ደሴ _ነሀሴ 30/2018ዓ,ምበደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪ...
05/09/2026

ወንጀልን በጋራ በመከላከል አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

ደሴ _ነሀሴ 30/2018ዓ,ም
በደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ1ኛ እና የ2ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያዎች ከማህበረሰብ ክፍሎች ጋር የውይይት መድርክ አካሄዱ።

​የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ 1ኛ እና 2ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያዎች ከየክፍለ ከተማው አጋር የፀጥታ አካላት፣ የመንግስትና የግል ድርጅቶች ጥበቃዎች ጋር የጋራ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ ያለመ ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።

​በ2ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ በሆጤ ክፍለ ከተማ ከሚኖሩ አጋር የፀጥታ አካላት ጋር በተደረገው ውይይት፣ የመወያያ ፅሁፉን የጣቢያው ወንጀል መከላከል ክፍል ሃላፊ ኢንስፔክተር አብዱ ሁሴን አቅርበዋል። መደረኩም በተለየ በቅድመ ወንጀል መከላከል፣በሰላም ግንባታና ጥላቻን በመቃወም፣የሃሰት መረጃዎችን በማጥራት መሰረተ ልማቶችን ከስርቆት በመጠበቅ ዙሪያ ትኩረት ያደረጉ ዋና ዋና ነጥቦችን አንስተዋል።

​የጣቢያው አዛዥ ኢንስፔክተር አለባቸው መለሰ በበኩላቸው "የከተማችንን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ መመካከርና በጋራ መስራት ወሳኝ ነው" ብለዋል። ህብረተሰቡና የፀጥታ ሃይሉ በቅንጅት ከሰሩ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን አስቀድሞ መከላከልና ወንጀለኞችንም ለህግ ማቅረብ ቀላል እንደሚሆን ገልፀው፣ እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶች የዚሁ የጋራ ቅንጅት ውጤት መሆናቸውን አብራርተዋል።

​በተመሳሳይ መልኩ በ1ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ የመንግስትና የግል ድርጅት ጥበቃዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል። የጣቢያው አዛዥ ኢንስፔክተር ፀጋ አባተ በጥበቃ ስራ ላይ ያሉ አካላት ከአካባቢው ኦፊሰርና ሚሊሻዎች ጋር በጥብቅ መተባበር እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ጥበቃዎች ተቋማትን በሚጠብቁበት ወቅት በአካባቢው የሚገኙ ህዝባዊ መሰረተ ልማቶች እንዳይሰረቁና ሌሎች ወንጀሎች እንዳይፈፀሙ የነቃ የቅድመ መከላከል ስራ መስራት እንደሚገባቸው አንሰተዋል።

​በሁለቱም ዋና ጣቢያዎች የተሳተፉ የውይይቱ ተካፋዮች ጥያቄና አስተያየቶችን በማንሳት ሰፊ መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩ በስኬት ተጠናቋል።
(ደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት)

ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ድንበር የለሽ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፤​የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ቡድን ከአማራ ክልል መንግ...
05/09/2026

ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ድንበር የለሽ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፤

​የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ቡድን ከአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ጋር በባህርዳር ከተማ የልምድ ልውውጥ አደረጉ።

​በልምድ ልዉዉጥ መድረኩ የተገኙት የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሄኖክ ሙሉነህ እንደገለጹት፤ የአማራ ክልል የሀገራችን የቱሪዝም የስበት ማዕከልና ከራሱ አልፎ ለሀገር የሚተርፍ ትልቅ ሀብት ያለው ክልል ነው።

በባሕር ዳር ከተማ ተዘዋውረን የተመለከትናቸው የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ጸጋዎች ለሀገራችን የወደፊት የቱሪዝም እድገት ትልቅ ተስፋ የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የባህርዳር በለዉጥ ላይ ነች የከተማዋ የለዉጥ ጉዞም የብልጽግና ጉዟችን ዋነኛ ማሳያ ምልክት ነዉ ብለዋል።

​ሃላፊዉ ክልሉ ከነበረበት የጸጥታ ችግር ወጥቶ አሁን ትኩረቱን ልማት ላይ ማድረጉን በቆይታቸው መታዘባቸውን ገልጸው፤ በቀጣይ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በጋራ እንደሚሠሩ አጋርነታቸውን አረጋግጠዋል።

​የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ትብለጥ መንገሻ በበኩላቸው፤ ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን ለመገንባት ሚዲያው ዋነኛ መሳሪያ ነዉ። ከሀረሪ ክልል ጋር የነበረውን የቆየ መልካም ግንኙነት እና የተግባራት አፈጻጸም ልምድ በመካፈልና በማዳበር፣ ለክልላችን እንዲሁም ለሀገር ገጽታ ግንባታ የሚጠቅሙ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። የልምድ ልውውጡም ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና የነበሩ ክፍተቶችን ለማሻሻል የሚረዳ መሆኑን ጠቁመዋል።

​የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ዘበነ በበኩላቸው፤ የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ ከምናሳካባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ዲጂታል ኮሙኒኬሽን መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህ የሚመጥን ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት አሁናዊ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ፤ የልምድ ልውውጡ በቀጣይ በጋራ ለሚከናወኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራዎች ጠንካራ መሠረት የጣለ ነውም ብለዋል።
Amhara Communications

የአዲስ አመት ዋዜማ ምክንያት በማድረግ  የገበያ መረጋጋት የንግድ ትርኢትና ባዛር በደሴ ከተማ ቧንቧውሀ አደባባይ ላይ ተከፈተ።ደሴ:ነሀሴ30/2018(ደሴ ኮሙኒኬሽን)የደሴ ከተማ አስተዳደር ን...
05/09/2026

የአዲስ አመት ዋዜማ ምክንያት በማድረግ የገበያ መረጋጋት የንግድ ትርኢትና ባዛር በደሴ ከተማ ቧንቧውሀ አደባባይ ላይ ተከፈተ።

ደሴ:ነሀሴ30/2018(ደሴ ኮሙኒኬሽን)
የደሴ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ ከፀሀይ መልቲ ሜዴያና ፕሮመሸን ጋር በመተባበር የአዲስ አመት ዋዜማ የገበያ መረጋጋት የንግድ ትርኢትና ባዛር ቧንቧውሀ አደባባይ ላይ ተከፈተ።

ባዛሩን የከፈቱት የደሴ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ሰይድ አሊ እንደገለጹት ለአዲስ አመት ዋዜማ የተዘጋጀው ባዛር በከተማችን አስተማማኝ ሠላምን በመፍጠር በአጭር ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረገና የኑሮ ውድነትን ለመቅረፍ ታስቦ በቅንጅት የተሠራ ነው ብለዋል።

በቅድመ ዝግጅት ስራም ከአቅራቢ ድርጅቶች ጋር ሰላማዊና የተረጋጋ የግብይት እንዲሆን ድርጅቶች ማድረግ ያለባቸውን ጥንቃ በመወያየትና በመመካከር የተዘጋጀ ነው ብለዋል።

የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ የወናስ እንዳለ በበኩላቸው፤ ባዛሩ ሸማቹንና የንግዱን ማህበረሰብ ለማገናኘት የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከግብርና እስከ ኢንዱስትሪ ምርቶች የሚያቀርቡ ከ140 በላይ አምራቾችና ጅምላ አከፋፋዮች መሳተፋቸውን አስታውቀዋል።

በባዛሩም የቀረቡት ምርቶችና ሸቀጦች ለህብረተሠቡ ቅናሽ በማድረግ በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረቡን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በፒያሳ አደባባይ ተመሳሳይ የጎዳና ላይ ግብይት መከፈቱን ጠቁመው፣ በበዓሉ አጋጣሚ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ አሳስበዋል።

በባዛሩ የተሳተፉ የኢንዱስትሪና የግብርና ምርት አቅራቢዎች (የኤልፎራን የዶሮና እንቁላል ምርቶች ጨምሮ) ምርቶቻቸውን ከመደበኛ ዋጋ ቅናሽ በማድረግ ለሸማቹ በቀጥታ እያቀረቡ እንደሚገኙ ገልጸው፣ የገበያ ማረጋጋት ሥራውን በሌሎች ቦታዎችም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

​የከተማዋ ሸማቾችም የቀረቡት ምርቶችና ሸቀጦች ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውና አስፈላጊ በመሆናቸው ተጠቃሚ በመሆናቸው የተሠማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከደሴ ኮሙኒኬሽን የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ !!
ድረ ገጽ፦
#ፌስቡክ፤-https://www.facebook.com/DessieCityAdministrationCommunicationAffairsOffice/
#ቴሌግራም፡-t.me/dessiecityadminstration
#ቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMkdcEx16/
.communicat
#ዩቲዩብ ፦
https://youtube.com/?si=1Rg_R4LPQYQV-G3h
#ዋትሳፕ። ደሴ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን
https://chat.whatsapp.com/CosS5afsqLH1OtlwPaNrNa

የደሴ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር  ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ​በደሴ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ መንሠራራ...
05/09/2026

የደሴ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ

​በደሴ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር ዝግጅት መጠናቀቁን የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙዔል ሞላልኝ ገልጸዋል።

​አቶ ሳሙዔል የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበርን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ዘንድሮ ቀናቱ “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በልዩ ልዩ አገር አቀፍ፣ ክልላዊና ከተማዊ ሁነቶች እንደሚከበሩ አስታውቀዋል፡፡

የጳጉሜ ቀናት በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ልዩ ቦታ ያላቸው ሲሆን ከአንድ ዓመት መጠናቀቅ እና ከአዲስ ዓመት መጀመር መካከል የሚገኙ የሽግግር ቀናት ናቸው ያሉት ከንቲባው በእነዚህ ቀናት ሰዎች ያለፈውን ዓመት በመመልከት የተሠሩ ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን፣ ያጋጠሙ ችግሮችንና የተገኙ ትምህርቶችን ይገመግማሉ። ይህም በቀጣይ ዓመት የተሻለ ውጤት ለማምጣት የሚያግዝ ጠንካራ መነሻ ይፈጥራል ብለዋል።

በመሆኑም የዘንድሮው የጳጉሜ ቀናት አከባበር ሁላችንም በንቃት የምንሳተፍበት፣ ያለፈውን በአግባቡ የምንገመግምበት፣ ዛሬን በተግባር የምናሳልፍበት እና ነገን በተስፋ የምንገነባበት ሊሆን ይገባል። ጳጉሜን በአንድነት፣ በትብብር፣ በበጎ ተግባርና በመልካም ተስፋ በማክበር አዲሱን ዓመት በአዲስ አቅም እንቀበል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በዚህም የጳጉሜን ቀናት አከባበር እና ስያሜ እንደሚከተለው ተቀምጠዋል።

​ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፦ ሀገራችን ከተረጂነትና ጥገኝነት ተላቃ ወደ አምራችነት እያደረገች ያለችውን ታሪካዊ ሽግግር ለማብሰር፣ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬቶች፣ የምግብ ሉዓላዊነት ድሎች እና የ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄ ውጤቶች በሰፊው ይታወቃሉ።

​ጳጉሜን 2 (የመንሠራራት ቀን)፦ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ ሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደቶችና ማኅበራዊ ዕድገቶች በዜጎች የዕለት ተዕለት ሕይወት ላይ ያመጧቸው አዎንታዊ ተፅዕኖዎች ይበልጥ ይጎላሉ።

​ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፦ የፀጥታ ተቋማትን ዘመናዊ ቁመናና ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ሉዓላዊነት የተከፈለውን የጀግኖች መስዋዕትነት በመዘከር፣ የሀገር መከላከል ዓቅማችንና ሀገራዊ ፅናት ለሁለንተናዊ ዕድገት መሠረት መሆናቸው ይበሰራል።

​ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን)፦ ኅብረብሔራዊ አንድነትን፣ አብሮነትን፣ መረዳዳትንና በጎነትን ማዕከል ያደረጉ ሁነቶች በመከወን የወል ትርክትን የማጠናከርና ብዝኃነትን የማጎልበት ሥራዎች ይከናወናሉ።

​ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን)፦ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የሳይበር ሉዓላዊነት፣ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የ«5 ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ» ስኬቶችን በማሳየት ዲጂታልና በራስ አቅም የምትቆም አዲሷን ኢትዮጵያ የሚያመላክቱ ሁነቶች ይካሄዳሉ።

በመጨረሻም በከተማችን ባለፉት ዓመታት የተከናወኑት የጳጉሜን ቀናት አከባበር ተግባራት መልካም መሠረት የጣሉ መሆናቸው ይታወሳል፡፡ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር እና ሳቢ በሆኑ ኩነቶችና ንቅናቄ የሚመራ ይሆናል።

በደሴ ከተማ በሚሊዮን የሚቆጠር የመሠረተ ልማት ንብረት የዘረፉ ተጠርጣሪ ከነዕቃዎቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉደሴ _ነሀሴ 29/2018ዓ,ም(ደሴ ኮሙኒኬሽን)​በደሴ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ የመ...
04/09/2026

በደሴ ከተማ በሚሊዮን የሚቆጠር የመሠረተ ልማት ንብረት የዘረፉ ተጠርጣሪ ከነዕቃዎቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ

ደሴ _ነሀሴ 29/2018ዓ,ም(ደሴ ኮሙኒኬሽን)
​በደሴ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ የመብራት ሃይል ትራንስፎርመር እና የቴሌ የመሠረተ ልማት እቃዎች ስርቆት ሲፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች፣ ተበታትነው ከተደበቁበት ቦታ ከተያዙት ንብረቶችና ከነግብረአበሮቻቸው ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ።

​የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ከ4ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ጋር በመሆን ባካሄደው ከፍተኛ የምርመራ እርብርብ፣ ተበታትነው በአንድ ግቢ ውስጥ ተደብቀው የነበሩ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር የሚያወጡ ትራንስፎርመሮችንና የቴሌ እቃዎችን መያዝ እና ማስመለስ ተችሏል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ደህንነት መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ሰይድ አሊ በበኩላቸው ልማትን ለማደናቀፍ የተደራጀን የዘራፊ ቡድን መያዝ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ድርጊቱ ማንም ወንጀለኛ ከህግ እንደማያመልጥና የፀጥታ አካላት ቅንጅት ውጤት እንደሚያመጣ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ፣ ህዝቡ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር ያለው ትብብር እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።

​የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጥላሁን ታደሰ እንደገለጹት፤ ድርጊቱ አገርን ከማጥፋት የማይተናነስና ህዝብን ከፀጥታ ኃይሉ ለመለየት የተደረገ እኩይ ተግባር ነው። መምሪያው ልዩ የምርመራ ቡድን በማዋቀር ወደ ስራ በመግባቱ ውጤቱ ሊገኝ መቻሉን የጠቆሙት ኮማንደሩ፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚደረገው ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለስኬቱ አስተዋጽኦ ላደረጉ የፖሊስ አባላት፣ የፀጥታ ኃይሎችና ማህበረሰብ ምስጋና አቅርበዋል።

​በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደሴ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ሀብቱ አበበ ከሐምሌ ወር ጀምሮ ይፈጸም የነበረውን ስርቆት ለማስቆም እና የመልካም አስተዳደር ችግር የሆነውን የንብረት ውድመት ለመታደግ ለተደረገው ከፍተኛ ትብብር ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

​የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ሴኩሪቲ ማናጀር ኮሎኔል ገዛህኝ አለባቸው እንደገለጹትም፣ ተቋሙ ጉዳዩን ከአጋር የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በትኩረት እየሰራበት ይገኛል።
ምንጭ፦ደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት)

በደሴ ከተማ በ12 ቡድኖች መካከል  ሲካሄድበት የቆየው የፉትሳል እግርኳስ ጨዋታ  ውድድር እሁድ ጷጉሜ 1 ፍፃሜውን ያገኛል። 🏟️ደሴ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም በደሴ ከተማ በ12 ቡድኖች መካ...
04/09/2026

በደሴ ከተማ በ12 ቡድኖች መካከል ሲካሄድበት የቆየው የፉትሳል እግርኳስ ጨዋታ ውድድር እሁድ ጷጉሜ 1 ፍፃሜውን ያገኛል። 🏟️

ደሴ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም በደሴ ከተማ በ12 ቡድኖች መካከል ጥሩ ጨዋታና ፉክክር ሲካሄድበት የቆየው የፉትሳል ውድድር እሁድ ጷጉሜ 1 ፍፃሜውን ያገኛል። ወጣቶች ክረምቱን በስፓርት እንዲያሳልፉ እና ልምድ ካላቸው ተጨዋቾች ተሞክሮ እንዲያገኙ መርሀግብሩ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደነበረው የመርሃግብሩ አዘጋጅና አሠልጣኝ ብርሀኑ በላይ ለአሚኮ ተናግረዋል።
ከውድድሩ ለተጨዋቾች ብቻ ሳይኾን ለመላው እግርኳስ ወዳድ የከተማዋ ነዋሪዎች ጥሩ መዝናኛና የእረፍት ጊዜ ማሳለፊያ ኾኖ መቆየቱም ተመላክቷል።

እሁድ ጷጉሜ 1 በተስፋ ድርጅት ት/ቤት የሚደረገውን የፍፃሜና የደረጃ ጨዋታዎች የስፖርቱ ቤተሠብ እንዲታደምም ጥሪ ቀርቧል።

#አሚኮ #ደሴ #የፉትሳል እግርኳስ ውድድር #
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደሴ ኮሙኒኬሽን የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ !!
ድረ ገጽ፦
#ፌስቡክ፤-https://www.facebook.com/DessieCityAdministrationCommunicationAffairsOffice/
#ቴሌግራም፡-t.me/dessiecityadminstration
#ቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMkdcEx16/
.communicat
#ዩቲዩብ ፦
https://youtube.com/?si=1Rg_R4LPQYQV-G3h
#ዋትሳፕ። ደሴ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን
https://chat.whatsapp.com/CosS5afsqLH1OtlwPaNrNa

በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገነባው ሙዚየም የኢትዮጵያን የፍትሕ ሥርዓት በዲጅታልና በቁስ ሰንዶ የያዘ ነው።የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተገበራቸው ካሉ የተቋምና የሰው ኃይል ...
04/09/2026

በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገነባው ሙዚየም የኢትዮጵያን የፍትሕ ሥርዓት በዲጅታልና በቁስ ሰንዶ የያዘ ነው።

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እየተገበራቸው ካሉ የተቋምና የሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና የዘመናዊ ዳኝነት አገልግሎት መስጫ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ በተጨማሪ የሀገሪቱን እና የክልሉን የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ከጥንታዊ አሠራር እስከ ዘመናዊው ሥርዓት የሚዳስስ የፍትሕ ሙዚየም ግንባታ ይገኝበታል።

ለሙዚየሙ የሚሆን ዘመናዊ ሕንጻ ከመገንባት እስከ ማደራጀት እና ለጎብኝዎች ክፍት ማድረግ በርካታ ሂደቶችን አልፏል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ። ሙዚየሙ ርዕሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ፣ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ እና ሌሎችም መሪዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ለጎብኝዎች ክፍት ሆኗል።

በመረሀግብሩ ላይ የሙዚየሙን መገንባት እና መደራጀት አስፈላጊነት ለእንግዶቹ ያስረዱት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው፣ የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓቱ የሀገሪቱ ታሪክ አንድ አካል መሆኑን ገልጸው ፣ ይህንን ታሪክ አደራጅቶ ለትውልድ ለማስተላለፍ፣ ትውልዱ የሀገሪቱን የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ከጅማሮው እስከ አሁን ድረስ መረዳት እንዲኖረው ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሙዚየሙን ለማደራጀት ዘመናዊ ሕንጻ ከመገንባት ጀምሮ፣ ለሙዚየሙ ግብዓት የሚሆኑ ታሪካዊ ሰነዶችን፣ መዛግብትን፣ የፎቶ፣ የድምጽ እና የቁሳቁስ ግብዓት ለመሰብሰብ እና ለማደራጀት ከክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ጨምሮ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሌሎች የሥራ ክፍል ኀላፊዎችን ያካተተ ቡድን ተቋቁሞ ዓመቱን ሙሉ ሲሠራ መቆየቱን አብራርተዋል።

ሙዚየሙ በሀገሪቱ የዳኝነት እና የፍትሕ ሥርዓት ላይ ምርምሮችን ለሚያካሂዱ ተመራማሪዎች፣ የሕግ ተማሪዎች፣ ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ተቋማትና ግለሰቦች በማጣቀሻነት የሚያገለግሉ የሰነድና የምስል ክምችቶች አሉት። ለፖሊሲ እና ሌሎች የዳኝነት እና የፍትሕ ስትራቴጂክ ሰነዶች ዝግጅት የሚያገለግሉ ግብዓቶች የሚገኙበት ማዕከልም ነው ብለዋል።

የፍትሕ ሙዚየሙ በከፊል ዲጂታል ሆኖ የተደራጀ ሲኾን፣ የሕግ ተማሪዎች እና እጩ ዳኞች የሚለማመዱበት ምስለ ችሎት ጨምሮ መደበኛ ችሎት መከታተል የሚችሉበትን የዲጂታል አገልግሎት የያዘ ነው። ሙዚየሙ ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት ተደርጓል።

#አሚኮ

Address

Dessi

Telephone

+25133111787

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dessie City Administration Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dessie City Administration Communication:

Shortcuts

Share