የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Dessie
  • የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ Welcome to Dessie City Woman Children and Social Affair Organization FB Page.

የአብክመ ሴቶች፤ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በ2018 በጀት አመት የላቀ የስራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና የሰጠ ሲሆን በዚህም      በከተማ  አስተዳደር  ደ...
03/09/2026

የአብክመ ሴቶች፤ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በ2018 በጀት አመት የላቀ የስራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና የሰጠ ሲሆን በዚህም
በከተማ አስተዳደር ደረጃ
1ኛ. ደሴ ከተማ አስተዳደር
2ኛ. ኮቦልቻ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም
3ኛ. ጎንደር ከተማ አስተዳደር ሲሆኑ

በዞን ደረጃ ደግሞ
1ኛ. ማዕከላዊ ጎንደር ዞን
2ኛ . ምዕራብ ጎጃም ዞን
3ኛ. ደቡብ ወሎ ዞን ናቸው።


ነሀሴ 27/ 2018 ዓ.ም
‎ ባህር ዳር

“ብዝሀ የወጣቶች እውቀት፤ ለጋራ ትልም!” በሚል መሪ መልእክት ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በደሴ ከተማ ተከበረ።የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከYNSD ጋር በ...
21/08/2026

“ብዝሀ የወጣቶች እውቀት፤ ለጋራ ትልም!” በሚል መሪ መልእክት ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በደሴ ከተማ ተከበረ።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከYNSD ጋር በመተባበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ26ተኛ ጊዜ በሃገር ዓቀፍ ደረጃ ለ23ተኛ ጊዜ የተከበረው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በፓናል ውይይት ተከብሯል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኅላፊ ወ/ሪት ትእግስት አበበ እንደገለጹት ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በየዓመቱ ነሀሴ 12 ቀን የሚከበር ሲሆን፣ ዓላማውም የወጣቶችን ጉዳዮች ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት ማድረስ እና በዛሬው ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ውስጥ ወጣቶች እንደ አጋር ያላቸውን አቅም ለማክበር ነው።

ወጣቱ የነገዋን ዲሞክራሲያዊትና የበለጸገች ኢትዮጵያን ዛሬ ላይ ቆሞ በጋራ የሚቀርጽ፣ የሚያንጽና የሚመራ ግንባር ቀደም አምራችና ባለቤት መሆን ይኖርበታል ብለዋል።

በመምሪያው እና በYNSD ፕሮጀክት የ2018 ዓ.ም አለማቀፍ የወጣቶች ቀንን ለማክበር በሰላም እና የክረምት በጎፈቃድ ተግባር አሰጣጥ የተዘጋጀ መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም
ደሴ

የደሴ ከተማ አራዳ ክ/ከተማ አይጠየፍ ቀበሌ የዜጎች የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባር የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ተካሄደ።የ2018 ዓ.ም የዜጎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር የአራዳ...
21/08/2026

የደሴ ከተማ አራዳ ክ/ከተማ አይጠየፍ ቀበሌ የዜጎች የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባር የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ተካሄደ።

የ2018 ዓ.ም የዜጎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር የአራዳ ክ/ከተማ አይጠየፍ ቀበሌ ለ3 አቅመ ደካማ አባወራዎች አዲስ ቤት ግንባታ ተካሂዷል።

በግንባታ ስራውም የደሴ ከተማ ባህል አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሪት ትእግስት አበበ፣ የደሴ ከተማ ወጣት ክንፍ አክሊሉ ሰለምን፣ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ አቢዬት ጋሻው፣ የክፍለ ከተማ አመራርና የክረምት በጎፈቃድ ሰጭ ወጣቶች ተገኝቸው ግንባታውን አስጀምረዋል።

ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም
ደሴ

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!» በሚል መሪ ቃል የደሴ ከተማ ወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቀደኛ ወጣቶች በሀይቅ ከተማ በመገኘት ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ተግባራት አከናውነዋል።​በመርሀ ግብሩ ከተከናወኑ...
21/08/2026

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!» በሚል መሪ ቃል የደሴ ከተማ ወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቀደኛ ወጣቶች በሀይቅ ከተማ በመገኘት ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ተግባራት አከናውነዋል።

​በመርሀ ግብሩ ከተከናወኑት አበይት ተግባራት መካከል ​የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር፣ የጽዳት ዘመቻና ​ የአዲሱን የትምህርት ዘመን ምክንያት በማድረግ አቅም ደካማ ለሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን በማስረከብ ለነገ ሀገር ተረካቢዎችን ወገንተኝነት አሳይተዋል።

​ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በወሰን ወይም በአካባቢ የማይወሰን የጋራ እሴታችን መሆኑ ተገልጿል።

ይህ ተግባር በወጣቶች መካከል የመረዳዳት፣ የትብብር እና የእህትማማችነት/ወንድማማችነት ባህልን በፅኑ የሚያጎለብት መሆኑም ተመላክቷል።

​ይህ የደሴ ከተማ ወጣቶች በጎ አድራጎት ከአንድ ከተማ አልፎ በዙሪያው ባሉ አካባቢዎች ሁሉ ፍቅርንና አንድነትን መዝራት እንደሚቻል ማሳያ ሲሆን፣ የመደጋገፍና አብሮ የመስራት አገራዊ እሴትን በተግባር ያሳየ ሞዴል ተግባር እንደሆነ ተገልጿል።

የደሴ ከተማ ሴቶች፣ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሀይቅ ከተማ አስተዳደር ላደረገለት ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርቧል።

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"​"በደሴ ከተማ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፦ ተማሪዎች ጌዜያቸውን አልባሌ ቦታ እንዳይውሉ ለመታደግ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን የማዘጋጀት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል"።...
11/08/2026

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"
​"በደሴ ከተማ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፦ ተማሪዎች ጌዜያቸውን አልባሌ ቦታ እንዳይውሉ ለመታደግ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን የማዘጋጀት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል"።

​በደሴ ከተማ በክረምቱ ወቅት ተማሪዎች ጊዜያቸውን በአልባሌ ቦታዎች እንዳያሳልፉ እና ለቀጣዩ ትምህርት ዘመን ብቁ ሆነው እንዲዘጋጁ ያለመ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ ዘርፎች በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።

​በዚህ በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ተማሪዎችን በዕውቀት ለማበልጸግና የትምህርት እውቀታቸውን ለማሻሻል የሚያስችል የማጠናከሪያ ትምህርት (Tutorial class) እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ጎን ለጎንም ምቹ የትምህርት አካባቢን እና የመማሪያ ክፍልን ለመፍጠር የትምህርት ቤቶች ወንበር፣ ጥቁር ሰሌዳ፣ አጥር ጥገና፣ የእድሳት ስራዎች እና የችግኝ ተከላ በመከናወን ላይ ናቸው።

​ከዚህ በተጨማሪም አቅመ ደካማ እና ችግረኛ ለሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ደብተር፣ እስክርቢቶ እና የትምህርት ቤት ዩኒፎርም የማሰባሰብና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሴት ተማሪዎቻችን የሚሆኑ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን የማሰባሰብ ስራ በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል።

ተማሪዎች በእረፍት ጊዜያቸውን የአካባቢያቸውን ታሪክ ለማወቅ በደሴ ሙዚየም የሚገኙ ቅርሶችን እንዲጎበኙ እየተደረገ ነው።

​ይህ በጎ ፈቃድ ተግባር ተማሪዎች ክረምቱን በጥሩ ስነ-ምግባር እና በእውቀት እንዲያሳልፉ ከማድረጉም በላይ፣ የማህበረሰቡን መደጋገፍ እና ትብብር ያጠናከረ ተግባር መሆኑ ተገልጿል።

በደሴ ከተማ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተያዘው ዕቅድ እስከአሁን  ውጤታማ ሥራ መከናወኑን የክልሉ ሱፐርቪዥን ቡድን ገለጸ​በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገል...
07/08/2026

በደሴ ከተማ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተያዘው ዕቅድ እስከአሁን ውጤታማ ሥራ መከናወኑን የክልሉ ሱፐርቪዥን ቡድን ገለጸ

​በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሱፐርቪዥን ቡድን በደሴ ከተማ አስተዳደር ያደረገውን የመስክ ምልከታ በማጠናቀቅ ከከተማው አስተባባሪ ስቲሪንግ ኮሚቴ ጋር የማጠቃለያ መድረክ አካሂዷል።

​ቡድኑ እስከ ሃምሌ 29/2018 ዓ.ም ድረስ የተከናወኑ የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን አፈጻጸም በዝርዝር የገመገመ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ በተለዩት 17ቱም የክረምት የተግባር መስኮች ከተጠበቀው በላይ የተሻለና አበረታች ሥራ መከናወኑን አረጋግጧል።

​በዘንድሮው የክረምት ወራት የዜጎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ማሳተፍ ተችሏል።

ይህም የበጎ ፈቃድ ባህልን በማህበረሰቡ ዘንድ የበለጠ ለማስረጽና የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

​የሱፐርቪዥን ቡድኑ በምልከታው ያረጋገጣቸውን ዋና ዋና ስኬቶችና የትኩረት አቅጣጫዎች ​የ17ቱ ተግባራት አፈጻጸም፡ ከአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ እስከ አቅመ-ደካሞች ቤት እድሳት፣ የደም ልገሳ፣ ማህበራዊ ድጋፍና የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰብ ባሉት ሙሉ 17ቱ የተግባር መስኮች የተቀናጀና ውጤታማ እንቅስቃሴ ተደርጓል።

​የህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነት ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በጉልበትና በእውቀቱ ያደረገው ንቁ ተሳትፎ ለስራው ስኬታማነት ዋና ምክንያት መሆኑ ተጠቅሷል።

​በየደረጃው ያሉ የአመራር አካላትና የስትሪንግ ኮሚቴው ያደረጉት ቅርብ ክትትልና ድጋፍ በስራው ላይ ግልጽ ለውጥ ማምጣቱ ተመላክቷል።

​በመድረኩ ማጠቃለያ የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለማየሁ እንደገለፁት ያሉት ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ከተሰጡት ግብረ-መልሶች በመነሳት የቀሩትን የክረምት ወራት ተግባራት በተመሳሳይ ትጋትና ጥራት በማጠናቀቅ የታቀዱትን ግቦች ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ከተማ አስተዳደሩ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

ነሃሴ 1/2018 ዓ.ም
ደሴ

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያና የደሴ ከተማ ሴቶች ማህበራት ፌደሬሽን ከሜዲካል ቲምስ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር "የወሎ ደሴ ብሩህ ስኬት አረብ ሃገር ...
06/08/2026

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያና የደሴ ከተማ ሴቶች ማህበራት ፌደሬሽን ከሜዲካል ቲምስ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር "የወሎ ደሴ ብሩህ ስኬት አረብ ሃገር ተመላሾች ማህበር" አንደኛ አመት የምስረታ በዓል እና የአደረጃጀት ጥቅምና አስፈላጊነትን በተመለከተ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በማዘጋጀት የግንዛቤ ፈጠራ ስራ ተሰራ።

በመድረኩ የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሪት ትዕግስት አበበ መደራጀት ለሴቶች ያለውን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ገልፀው የማህበሩ አባላት ማህበሩ እንዲጠናከር የበኩላቸውን እንዲወጡና ሴቶቹ በስነ ልቦና ረገድ ጠንካራ እንዲሆኑ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም
ደሴ

06/08/2026
የደሴ ከተማ አስተዳደር የክረምት የበጎ ፈቃድ አስተባባሪ ስቲሪንግ ኮሚቴ እስካሁን የተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን ገመገመ።​በክረምት ወቅት የሚከናወኑ የተለያዩ የማህበረሰብ አገል...
04/08/2026

የደሴ ከተማ አስተዳደር የክረምት የበጎ ፈቃድ አስተባባሪ ስቲሪንግ ኮሚቴ እስካሁን የተከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን ገመገመ።

​በክረምት ወቅት የሚከናወኑ የተለያዩ የማህበረሰብ አገልግሎቶች እና የበጎ ፈቃድ ሥራዎች አፈፃፀምን አስመልክቶ የበጎ ፈቃድ አስተባባሪ ስቲሪንግ ኮሚቴ አጠቃላይ የሥራ ሂደቱን፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመገምገም ጥልቅ ውይይት አካሂዷል።

​ይህ በየዓመቱ የሚካሄደው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶችንና ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማስተባበር የዜግነት አለኝታን ለማረጋገጥና የሕዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለማቃለል ታስቦ የሚከናወን አገር አቀፍ እንቅስቃሴ ነው።

​በግምገማ መድረኩ እንደተመላከተው እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ የታቀዱ በርካታ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች በጥሩ ሁኔታ መከናወናቸው ተገልጿል።

​ስቲሪንግ ኮሚቴው ቀሪውን የክረምት ወቅት ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማጠናቀቅ የተጀመሩ የቤት እድሳት እና የችግኝ ተከላ ሥራዎች እንዲሁም ሌሎች ልዩ ልዩ ተግባራቶችን የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት ሙሉ በሙሉ እንዲጠናቀቁ ማድረግና የተተከሉ ችግኞችን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ ገልጿል።

​ስቲሪንግ ኮሚቴው በስተመጨረሻም መላው ማህበረሰብ እና አጋር ድርጅቶች ቀሪውን የክረምት ወቅት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በስኬት ለማጠናቀቅ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል።

በግምገማ መድረኩ በሰላም ሚንስቴር የደሴ ከተማ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች አስተባባሪ አቶ ገዛኸኝ ጭናሶ ተገኝተዋል።

ሀምሌ 28/2018 ዓ.ም
ደሴ

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ2018 ዓ.ም አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ተካሄደ። በመድረኩ ላይ የክ/ከተማ የማህበራዊ ዘርፍ ሃላፊዎች ...
29/07/2026

የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ2018 ዓ.ም አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ተካሄደ።
በመድረኩ ላይ የክ/ከተማ የማህበራዊ ዘርፍ ሃላፊዎች ቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች: የወጣትና የሴት ክንፎች የአረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ማህበራት አመራሮች እንዲሁም የመምሪያው ጠቅላላ ሠራተኞች ተገኝተዋል።
የመምሪያው ሃላፊ ወ/ሪት ትዕግስት አበበ የተቋሙን አፈፃፀም አቅርበው የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ያስተዋወቁ ሲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካል እቅዱን ለማሳካት የበኩሉን አስተዋፅዖ እንዲወጣ አሳስበዋል።
በመጨረሻም በዓመቱ መልካም አፈፃፀም የነበራቸው 3 ክፍለ ከተሞች የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

ሀምሌ 22/2018 ዓ.ም
ደሴ

Address

Dessie

Telephone

+251331124287

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደሴ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share