Anrs Ethics and Anticorruption Dessie Branch /የአብክመ ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮ/ደ/ ቅ/

  • Home
  • Ethiopia
  • Dessie
  • Anrs Ethics and Anticorruption Dessie Branch /የአብክመ ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮ/ደ/ ቅ/

Anrs Ethics and Anticorruption Dessie Branch /የአብክመ ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮ/ደ/ ቅ/ Creating awareness of corruption prevention

ሌብነትንና ሙስናን ለመዋጋት ትልቁና የመጀመሪያው እርምጃ ከራስ መጀመር ነው!!!ሌብነት ጠቃሚ አይደለም፤ ማስረጃ ማግኘት በህግም በአስተዳደርም ርምጃ ለመውሰድ ያግዛል፤ ሌብነት ክፉ መሆኑን አ...
03/09/2026

ሌብነትንና ሙስናን ለመዋጋት ትልቁና የመጀመሪያው እርምጃ ከራስ መጀመር ነው!!!
ሌብነት ጠቃሚ አይደለም፤ ማስረጃ ማግኘት በህግም በአስተዳደርም ርምጃ ለመውሰድ ያግዛል፤ ሌብነት ክፉ መሆኑን አምነን መጀመሪያ ራስን መታገል አልፎ ሲሄድ ደግሞ በህግ የሚያስጠይቅ ማስረጃ መያዝ ጠቃሚ ይሆናል!
ሌብነትንና ሙስናን ለመዋጋት ትልቁና የመጀመሪያው እርምጃ ከራስ መጀመር ነው። ራስን በስነ-ምግባርና በታማኝነት መቅረፅ ለለውጥ መነሻ ነው፤ ከዛ አልፎ የሚፈጸሙ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ደግሞ በባዶ ጥርጣሬ ሳይሆን በተጨባጭ ማስረጃ መደገፍ ለህግና ለአስተዳደራዊ እርምጃ ወሳኝ ነው።
ለዚህ ትግል ውጤታማነት የሚከተሉት ነጥቦች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው፡
• ግንዛቤና የህሊና ዳኝነት፡ ሌብነት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውድቀትን እንደሚያመጣ አምኖ መታገል፤ በትንሹም ሆነ በትልቁ ነገር ላይ የታማኝነት ባህልን ማዳበር።
• ህጋዊና ተጨባጭ ማስረጃ፡ አንድን ህገ-ወጥ ድርጊት ለህግ አካል ወይም ለአስተዳደር ለማቅረብ ሰነዶችን፣ የገንዘብ ደረሰኞችን ወይም ሌሎች ህጋዊ ተቀባይነት ያላቸውን ማስረጃዎች በጥንቃቄ መያዝ።
• የጥቆማ ስርዓቶችን መጠቀም፡ ተቋማትና የመንግስት አካላት ለሙስና ጥቆማ ያዘጋጇቸውን ምስጢራዊ አሰራሮች በመጠቀም ለጠቋሚው ደህንነት ጥበቃ እያደረጉ ማስረጃዎችን ማቅረብ።
• የህግ የበላይነትን መከተል፡ በራስ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ አሰራርንና ህግን ተከትሎ ጥፋተኞችን እንዲጠየቁ ማድረግ ዘላቂ መፍትሔ ያመጣል።
ይህ አቋም በየትኛውም ተቋም ማህበረሰብ ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል።

03/09/2026
02/09/2026
02/09/2026

ተጠያቂነት የሌለበት አሰራር ልክ ልጓም እንደሌለው ፈረስ ማለት ነዉ ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

"ተጠያቂነት የሌለበት አሰራር ልጓም እንደሌለው ፈረስ ነው" የሚለዉ ተጠያቂነት በሌለበት ተቋም ወይም ስርዓት ውስጥ የሚፈጠረውን አደጋ እና ስርአት አልበኝነት በግልፅ የሚያሳይ አገላለፅ ነው።

ልጓም ፈረስን ወደ ተፈለገው አቅጣጫ ለመምራት እና ለማቆም የሚያገለግል መሳሪያ ነው። ልጓም ከሌለው ፈረሱ በራሱ ፍላጎት፣ ያለምንም ቁጥጥር ወደ ፈለገው አቅጣጫ ይጋልባል፤ ሊሰናከል፣ ሊወድቅ ወይም የከፋ አደጋ ሊያደርስ ይችላል።

በተመሳሳይ ሁኔታ፣ በአንድ ተቋም ወይም የመንግስት መዋቅር ውስጥ ግልፅ የሆነ የተጠያቂነት ስርአት ከሌለ፣ ሰራተኞች እና ኃላፊዎች በህግ እና በደንብ ሳይሆን በራሳቸው ፍላጎት ብቻ ይመራሉ። ይህ ደግሞ ወደ ግል ጥቅም ማጋበስ፣ ብልሹ አሰራር እና ህገ-ወጥነት ያመራሉ ማለት ነዉ።

ፈረሱ ብቻውን ከሚጎዳው በላይ፣ በአካባቢው ባሉ ሰዎች፣ ንብረት እና ሌሎች እንስሳት ላይ ያልታሰበ እና ከባድ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

ተጠያቂነት የሌለው አሰራርም ኃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት እና ህግን በመጣስ ለሚከሰቱ ስህተቶች የሚጠየቅ አካል ከሌለ፣ የህዝብ ሀብት ይባክናል፣ ሙስና ይስፋፋል፣ እንዲሁም ዜጎች ተገቢውን አገልግሎት እንዳያገኙ ይሆናል። ይህ በሀገር እና በህዝብ ላይ ትልቅ ጥፋት ነው ማለት ነዉ።

ማንም ሰው ልጓም የሌለውን ፈረስ ሊጋልብ ወይም ሊያምነው አይችልም። ህዝብም ተጠያቂነት በሌለው ስርዓት ላይ እምነት አይኖረውም። ህዝባዊ አመኔታ ከሌለ ደግሞ ማንኛውም መንግስታዊም ሆነ ህዝባዊ ተቋም ስኬታማ ሊሆን አይችልም።

በአጠቃላይ ልጓም ለፈረስ አስፈላጊ እንደሆነው ሁሉ፣ ተጠያቂነትም ለአንድ አሰራር ወይም ስርዓት የጀርባ አጥንት ነው። ተጠያቂነት ሲኖር ግልፅነት፣ ፍትሃዊነት፣ ኃላፊነትን መወጣት እና በመጨረሻም መልካም አስተዳደር ይሰፍናል።

የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ፣ ዘላቂ እና አጠቃላይ እንዲሆን በሦስት ዋና ዋና መሠረታዊ ምሰሶዎች (Pillars) ላይ ይደገፋል። እነሱም፡1. የመከላከያ ሥራዎች (Prevention)• የአሠራር ...
01/09/2026

የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ፣ ዘላቂ እና አጠቃላይ እንዲሆን በሦስት ዋና ዋና መሠረታዊ ምሰሶዎች (Pillars) ላይ ይደገፋል። እነሱም፡
1. የመከላከያ ሥራዎች (Prevention)
• የአሠራር ሥርዓትን ማሻሻል፡ ለሙስና አጋላጭ የሆኑ ሕጎችን፣ ደንቦችንና አሠራሮችን ማረም እና ግልጽ ማድረግ።
• ቴክኖሎጂን መጠቀም፡ አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል (ኢ-አገልግሎት) በመቀየር የሰው እና የሰው ግንኙነትን መቀነስ።
• ግልጽነትና ተጠያቂነት፡ በመንግሥት እና በግል ተቋማት ውስጥ የፋይናንስ እና የውሳኔ አሰጣጥ ግልጽነትን ማስፈን።
2. የትምህርትና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች (Education and Awareness)
• ሥነ-ምግባርን መገንባት፡ በሕብረተሰቡ፣ በተለይም በትውልዱ ዘንድ ታማኝነትን፣ የሥራ ወዳድነትን እና የበጎ ሥነ-ምግባር እሴቶችን ማዳበር።
• ሙስናን የሚጸየፍ ሕዝብ መፍጠር፡ የሙስናን ጎጂነት ለሕዝቡ በማስረገጥ፣ ሕብረተሰቡ ሙስና ሲፈጸም ጥቆማ እንዲሰጥ እና እንዲታገል ማነቃቃት።
3. ሕግ ማስከበርና እርምጃ መውሰድ (Law Enforcement / Investigation and Prosecution)
• ጥቆማና ምርመራ፡ የሙስና ጥቆማዎችን በጥራት መመርመር እና ማስረጃ ማደራጀት።
• የሕግ እርምጃ፡ በሙስና ወንጀል የተሳተፉ አካላትን ያለአድልዎ ለፍርድ ማቅረብ እና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ።
• ሀብት ማስመልስ፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የተዘረፈውን የሕዝብና የመንግሥት ሀብት ወይም ንብረት ወሰዶ ለመንግሥት/ለሕዝብ ገቢ ማድረግ።
እነዚህ ሦስቱ ምሰሶዎች እርስ በእርስ የተሳሰሩ ሲሆኑ፣ አንዱ ያለ ሌላው ሙሉ ውጤት ማምጣት አይችልም።

01/09/2026

25ቱ የሙስና ወንጀሎች (አዋጅ ቁጥር 881/2007)

*************************

1. በሥልጣን ያለአግባብ መገልገል (አንቀጽ 9)

2. ጉቦ መቀበል (አንቀጽ 10)

3. የማይገባ ጥቅም መቀበል (አንቀጽ 11)

4. አስታራቂ ሽማግሌዎችና ሌሎች ሰዎች የሚፈፅሙት ጉቦ የመቀበል ወንጀል (አንቀጽ 12)

5. የመንግስት ወይም የሕዝባዊ ድርጅት ሥራን በማያመች አኳኋን መምራት (አንቀጽ 13)

6. አደራ በተሠጠው ዕቃ ያለአግባብ ማዘዝ (አንቀጽ 14)

7. በሥራ ተግባር የሚፈፀም የመውሰድና የመሰወር ወንጀል (አንቀጽ 15)

8. በሥልጣን ወይም በኃላፊነት መነገድ (አንቀጽ 16)

9. በህገወጥ መንገድ መሰብሰብ ወይም ማስረከብ (አንቀጽ 17)

10. ያለአግባብ ጉዳይን ማጓተት (አንቀጽ 18)

11. ዋጋ ያለውን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ማግኘት (አንቀጽ 19)

12. ያለአግባብ ፍቃድ መስጠት ወይም ማፅደቅ (አንቀጽ 20)

13. ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ (አንቀጽ 21)

14. የሥራ ሚስጥርን መግለፅ (አንቀጽ 22)

15. መንግሥታዊ ወይም የህዝባዊ ሰነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀት፣ ወደ ሐሰት መለወጥ ወይም በሐሰተኛ ሰነድ መገልገል (አንቀጽ 23)

16. መንግስታዊ ወይም የህዝባዊ ድርጅት ስነዶችን ማጥፋት ወይም ጉዳት ማድረስ (አንቀጽ 24)

17. ጉቦ ወይም ተገቢ ያልሆነ ጥቅም መስጠት (አንቀጽ 25)

18. ዋጋ ያለዉን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ መስጠት (አንቀጽ 26)

19. ማቀባበል (አንቀጽ 27)

20. በሌለው ሥልጣን መጠቀም (አንቀጽ 28)

21. በግል ተሰሚነት መነገድ (አንቀጽ 29)

22. በምርጫ ላይ የሚሰጥ መደለያ (አንቀጽ 30)

23. ከባድ የእምነት ማጉደል (አንቀጽ 31)

24. ከባድ አታላይነት (አንቀጽ 32)

25. በሙስና ወንጀል የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና በወንጀሉ ስለመርዳት (አንቀጽ 33)

ዜጎች ሙሰኞችን በማጋለጥ በንቃት ይሳተፉ!

ትውልድን በሥነምግባር፣ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች

https://play.google.com/store/apps/details?id=com.codewaveet.ecis

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች

https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ የልማት ዕቅድ ''በጦሳ ቃል ኪዳን '' የፊርማ ስነ ስርዓት ተጠናቀቀ።ነሐሴ 22/2018 – ኮምቦልቻየአብክመ ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ምስራቅ አማራ ደሴ ቅ...
28/08/2026

የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ የልማት ዕቅድ ''በጦሳ ቃል ኪዳን '' የፊርማ ስነ ስርዓት ተጠናቀቀ።

ነሐሴ 22/2018 – ኮምቦልቻ

የአብክመ ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ምስራቅ አማራ ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ በጦሳ ቃል ኪዳን የፊርማ ሥነ-ሥርዓት አጠናቋል።

መድረኩ በኮምቦልቻ ከተማ በደመቀ ሁኔታ የተካሄደ ሲሆን፣ ከ6 ዞኖች፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት የሥነ-ምግባር መኮንኖችና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

በመድረኩም የ2018 የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ ልማት ዕቅድ በየዘርፉ ኃላፊነት በተሰጣቸው ባለሙያዎች በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

የመድረኩ ዋና ዓላማም ካለፈው ዓመት የሥራ አፈጻጸም ልምድና ተሞክሮ በመውሰድ፣ በ2019 በጀት ዓመት የተሻለ የሥነ-ምግባር ግንባታ ሥራ በማከናወን፣ ሙስናና ብልሹ አሠራርን በመቀነስ የተሻለ የሥራ አፈጻጸም ማስመዝገብና ሕዝብን በተሻለ ሁኔታ ማገልገል መሆኑ ተገልጿል።

በውይይቱ የተሳተፉ ተሳታፊዎች የትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ ሥራ በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶት መቀጠል እንዳለበት ጠቁመው፣ በተለይም አላግባብ ተጠቃሚነትንና ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የተቀናጀና ቅንጅታዊ አሠራር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስምረውበታል።

በ2018 በጀት ዓመት በሁሉም ዘርፎች የላቀ አፈጻጸም ካስመዘገቡት መካከል ጉባላፍቶ፣ ደሴ ዙሪያና ራያ ቆቦ ወረዳዎች፤ የደቡብ ወሎ ገቢዎች፣ የቦረና ማረሚያ ቤትና የደሴ ከተማ ማረሚያ ቤት እንዲሁም እንደ ዞን ሰሜን ወሎና እንደ ከተማ ወልድያ ከተማ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገባቸው ተጠቅሷል።

በሌላ በኩል ደቡብ ወሎ፣ ኮምቦልቻ ከተማና ደሴ ከተማ መካከለኛ የሥራ አፈጻጸም ደረጃ ላይ መገኘታቸው ተመላክቷል።

የምስራቅ አማራ–ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም አያሌው፣ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥር ባሉ ዞኖች፣ ወረዳዎች፣ ከተሞችና ተቋማት የታዩ የሥራ አፈጻጸም ውጤቶችና ክፍተቶችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በቀጣይም የትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ፣ የግንዛቤና ሥልጠና ሥራዎችን ማጠናከር፣ ሙስናና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል የሀብት ማስመዝገብ ሥራና የአሠራር ሥርዓት ጥናት በትኩረት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

እንዲሁም ሁሉንም ተግባራት አቀናጅቶ ለመምራት ቅንጅታዊ አሠራርን ማጎልበት እንደሚገባና የድጋፍና ክትትል ሥራውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስምረውበታል።

የአብክመ ሥነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር አቶ ማሩ ቸኮል በበኩላቸው፣ በየደረጃው ያሉ ዞኖች ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የጸጥታ ችግሮችን ሽፋን በማድረግ ሳይዘናጉ ለውጤት መትጋትና መሥራት እንደሚገባ አስረድተዋል።

ም/ኮሚሽነሩ አክለውም፣ ሙስናን መከላከልና የነገዋን ኢትዮጵያ መገንባት በአንድ ተቋም ብቻ የሚከናወን ተግባር ባለመሆኑ፣ ከሚመለከታቸው አካላትና አጋር ተቋማት ጋር በቅንጅትና በትብብር መሥራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ የሥራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዞንና የከተማ አስተዳደሮች፣ እንዲሁም የተቋማትና የወረዳዎች የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በመጨረሻም የ2019 ዕቅዶችን በተቀመጠላቸው ጊዜና በተፈለገው ጥራት ለማከናወን የሚያግዝ እና እንደ ጦሳ ተራራ ከፍ ባለ አስተሳሰብና እንደ ጦሳ ተራራ ከፍ ባለ ንቃተ-ህሊና ሰርቶ ውጤት ለማስመዝገብ“የጦሳ ቃል ኪዳን” ሰነድ ተዘጋጅቶ፣ ተሳታፊዎች የቃል ኪዳን የፊርማ ሥነ-ሥርዓት በማከናወን መድረኩ ተጠናቋል።

“ትውልድን በሥነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሠራር!”

ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ ፈተና እንደሆነባቸው ተሳታፊዎች ገለጹ።የአብክመ ስነምግባና ጸረ-ሙስና ምስራቅ አማራ-ደሴ ቅ/ጽ/ቤት!!ነሐሴ 21/2018-ኮምቦልቻ!!የአብክመ ስነ ምግባር  ጸረ-ሙስና ...
27/08/2026

ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ ፈተና እንደሆነባቸው ተሳታፊዎች ገለጹ።

የአብክመ ስነምግባና ጸረ-ሙስና ምስራቅ አማራ-ደሴ ቅ/ጽ/ቤት!!

ነሐሴ 21/2018-ኮምቦልቻ!!

የአብክመ ስነ ምግባር ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ምስራቅ አማራ ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዕቅድ አፈጻጸም ከቅ/ጽ/ቤቱ ባለሙያዎች እና በ6ቱ ዞኖች የሚገኙ የዞን፣ የወረዳ/ከተማ እና የተቋማት የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች በተገኙበት ግምገማ እያካሄደ ነው።

በግምገማው ጎልቶ የወጣው ህገ-ወጥ የመሬት ወረራና ተገቢ ባልሆነ መልኩ በራሱ/በትዳር አጋሩ ስም መኖሪያ ቤት እያለው እንደገና መልሶ ለመውሰድ የሚደረግ ተገቢ ያልሆነ ፍላጎት እንዳለ ተሳታፊዎቹ እያነሱ ነው።

በክልላችን ያለውን የጸጥታ ችግር እንደ ሽፋን ተወስዶ የሚደረግ ህገ-ወጥ የመሬት መቀራመት ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተመላክቷል።

ተሳታፊዎቹ እንዳነሱት በገጠር የሚገኙ ጥንስስ ከተሞች ላይም ሆነ በከተማ የመኖሪያ ቤት እያላቸው እንደሌላቸው ተደርጎ የሚጽፈው የከተማና መሰረተ-ልማት ጽ/ቤትና የሚያደረጀው ህብረት ስራ ማህበርም አሰራራቸውን መፈተሽ እንዳለባቸው አንስተዋል።

በየደረጃው ያለው ከፍተኛ አመራርም በዚህ ዙሪያ የሚሰሩ ተቋማትን ትኩረት ሰጥቶ ለሰራ ይገባል ተብሏል።
..ውይይቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው!!

ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር!!

ምስራቅ አማራ ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዕቅድ ክንውን ግምገማ እና የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ መድክ ማካሄድ ጀመረ!!ኮምቦልቻ-ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም!!የአብክመ ስ...
27/08/2026

ምስራቅ አማራ ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዕቅድ ክንውን ግምገማ እና የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ መድክ ማካሄድ ጀመረ!!

ኮምቦልቻ-ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም!!

የአብክመ ስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ምስራቅ አማራ ደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዕቅድ ክንውን ግምገማ እና የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩ የአብክመ ስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ማሩ ቸኮል የተገኙ ሲሆን ተሳታፊዎቹም ከ6ቱም ዞኖችና ወረዳ/ከተማና ተቋማት የሚገኙ የስነ ምግባር መከታተያ ክፍሎችና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

መድረኩን የአብክመ ስነ ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ማሩ ቸኮልና የምስራቅ አማራ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም አያሌው በጋራ እየመሩት ነው።

የ2018 ቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 የአሻጋሪና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ መድረኩ ለበጀት ዓመቱ የስራ መቃናት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል።

ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር!!

የስነ-ምግባር ግንባታን ለማጠናከር እና ሙስናን ለመከላከል ያለመ የአሰልጣኞች ስልጠና በኮምቦልቻ ከተማ ተሰጠደሴ፡ነሐሴ20/2018 የአብክመ ስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን ደሴ ቅ/ቤትየአማራ ብ...
26/08/2026

የስነ-ምግባር ግንባታን ለማጠናከር እና ሙስናን ለመከላከል ያለመ የአሰልጣኞች ስልጠና በኮምቦልቻ ከተማ ተሰጠ

ደሴ፡ነሐሴ20/2018 የአብክመ ስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን ደሴ ቅ/ቤት
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ደሴ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ባዘጋጀው በዚህ መድረክ፤ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።

​በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የደሴ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም አያሌው እንደገለጹት፤ አገልጋይነትን በተላበሰ መንገድ ህዝብን ማገልገልና ለሙስና በር የሚከፍቱ አሰራሮችን መዝጋት እንደሚገባ ገልፀዋል።

​"የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች የተቋማትን የአሰራር ባህል በማጠናከር ረገድ ግንባር ቀደም መሆን ይገባቸዋል ብለዋል ።

ሀላፊው አክለውም በስልጠና የሚገኘውን እውቀት ወደ መሬት በማውረድ ማህበረሰብቡ ሙስናን በመታገል ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል።

የአስቸኳይ ሙስና ጥናት አማካሪ ወ/ሪት ራህመት አደም እንደገለፁት በመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ማነቆዎችን በፍጥነት በመለየት ረገድ የጥናት አስፈላጊነትን አብራርተዋል።

አሰራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል የሙስና ስጋቶችን አስቀድሞ መግታት እንደሚያስፈልግ እና ለአስቸኳይ ሙስና ጥናቶች አፋጣኝ ምላሽ መስጠት እንደሚገባም ገልፀዋል።

​የሀብት ምዝገባና ማሳወቅ ባለሙያ አቶ አህመድ ይመር በበኩላቸው የሀብት ምዝገባ ግልፅነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን ሙስናን በመከላከል ረገድ የሚጫወተው ሚና የጎላ ነው ብለዋል ። የመንግስት ተሾሚዎችና ሰራተኞች ሀብታቸውን በጥንቃቄ ማስመዝገብ እንዳለባቸውም ገልፀዋል።

​የስነ-ምግባር ግንባታና ስልጠና ባለሙያ አቶ አብዱ ሙሀመድ እንደገለጹት፤ በየደረጃው በሚገኙ ተቋማት ውስጥ ጠንካራ የስነ-ምግባር እሴቶችን መገንባት የረጅም ጊዜ የሙስና መከላከያ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል።

የስልጠናው ዋና አላማም ሰልጣኞች በቂ እውቀትና ክህሎት ጨብጠው ወደየ ተቋሞቻቸው ሲመለሱ በተመሳሳይ መልኩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀት ተከታታይ የስነ-ምግባር ግንባታ ስራ እንዲሰሩ ማስቻል እንደሆነም አስረድተዋል።

​የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በስልጠናው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ሙስናን በመታገል እና በመከላከል ህዝባዊ አመኔታን ለመገንባት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል።

​"የተሰጠንን ኃላፊነት በመወጣት ተቋማችንን በአሰራር፣ ትውልዱን ደግሞ በስነ-ምግባር ለመቅረጽ ዝግጁ ነን" ሲሉ ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።

የስልጠና መርሃ-ግብሩ በተለያዩ ርዕሶች ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ ሰልጣኞቹ ወደየተቋሞቻቸው ሲመለሱ ተመሳሳይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በየደረጃው እንደሚያዘጋጁ ተገልጻል።

Address

Shel
Dessie

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Anrs Ethics and Anticorruption Dessie Branch /የአብክመ ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮ/ደ/ ቅ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Anrs Ethics and Anticorruption Dessie Branch /የአብክመ ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮ/ደ/ ቅ/:

Shortcuts

Share