South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Dessie
  • South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት

South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት South Wollo PP

ጳጉሜ 1 "የእምረታ ቀን"በደቡብ ወሎ ዞን በአልብኮ ወረዳ "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የመስክ ሰብል ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ ተካሄደበደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ "እመርታ ለ...
06/09/2026

ጳጉሜ 1 "የእምረታ ቀን"

በደቡብ ወሎ ዞን በአልብኮ ወረዳ "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የመስክ ሰብል ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ ተካሄደ

በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው «የእምርታ ቀን» በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን፤ የግብርና ልማት ሥራዎችንና የልምድ ልውውጥን ያካተተ የመስክ ሰብል ጉብኝት ፕሮግራም ተካሂዷል።

በእለቱ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ራስን መቻልን ለማረጋገጥ፣ ለአግሮ-ፕሮሰሲንግ ፋብሪካዎች የግብርና ምርቶችን ለማቅረብ እና የውጭ ምርቶችን በመተካት ኤክስፖርት የማሳደግ ሦስት ዋና ዋና ግቦችን ታስበው የተከናወኑ ናቸው።

አቶ አህመድ አያይዘውም ባለፉት ዓመታት ከ96 ሺህ በላይ የሚሆኑ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ማስመረቅ የተቻለ ሲሆን፣ በያዝነው ዓመትም ከ261 ሺህ በላይ የሚሆኑ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ለማስመረቅ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም 14 ወረዳዎች ሙሉ በሙሉ ራሳቸውን ከምግብ ዋስትና ችግር ነፃ የሚያደርጉበት የትኩረት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

እንደ ማሾ፣ ባቄላ እና አኩሪ አተር ያሉ ኤክስፖርት የሚደረጉ ሰብሎችን የማምረት ሥራ የተጀመረ ሲሆን፤ ያልታረሱና የጋራ መሬቶችን በማረስ ለመጠባበቂያ የሚሆን ምርት የማከማቸት አሰራር ተዘርግቷል።

በዚህም በዞኑ ከ293 ሄክታር በላይ የወል መሬት በዘር የተሸፈነ ሲሆን፣ ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ እህልና 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ከማኅበረሰቡ በማሰባሰብ የራስን ችግር በራስ አቅም ለመፍታት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።

የአልብኮ ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብደላህ ሰይድ በበኩላቸው፤ በወረዳው የሕዝቡን የተረጅነት አስተሳሰብ በመቀየር የመሬት፣ የውኃና የሰው ኃይል ጸጋዎችን አቀናጅቶ ለመጠቀም ሰፊ የመግባባት ሥራ መሠራቱን ገልጸዋል። በወረዳው ከ14 ሺህ 952 ሄክታር በላይ የሚታረስ መሬት የሚገኝ ሲሆን፣ ከ553 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገመትም ጠቁመዋል።

በወረዳው ከተረጅነት ማላቀቅ ጋር ተያይዞ በ03 ፈላና ቀበሌ እስካሁን ታርሶ የማይታወቀውን 39 ሄክታር የወል መሬት ከማኅበረሰቡ ጋር በመስማማት በትራክተር የማረስ ሥራ የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት 7 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት በባቄላ፣ በጤፍ፣ በስንዴና በበቆሎ ዘር ተሸፍኖ በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል።

በምልከታው ወቅት ያናገርናቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች አራጋው ይመር እና ሰይድ ሙሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ለእንስሳት ማገጃነት ይውል የነበረውን የወል መሬት በጋራ በመስማማትና በትራክተር ማረስ መጀመራቸው ከእርዳታ ጠባቂነት ለመውጣት ትልቅ ተስፋ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

አርሶ አደሮቹ የግብርና ባለሙያዎችን ምክር፣ ኮምፖስትና ዘመናዊ ግብአቶችን በመጠቀም በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በማምረት የኑሮ ደረጃቸውን እያሻሻሉ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በቃሉ ወረዳ የጳጉሜ 1 ቀን "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ" በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።​በቃሉ ወረዳ ጳጉሜ 1 ቀን "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ መልዕክት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።
06/09/2026

በቃሉ ወረዳ የጳጉሜ 1 ቀን "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ" በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።

​በቃሉ ወረዳ ጳጉሜ 1 ቀን "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ መልዕክት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

የእምርታ ቀን!!የደጎሎ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል አጠቃላይ መሪ ሐሳብ  ጷጉሜ 1 ''የእምርታ ቀንን''   በከተማ ዉስጥ የሚገኙ በአምራ...
06/09/2026

የእምርታ ቀን!!

የደጎሎ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል አጠቃላይ መሪ ሐሳብ ጷጉሜ 1 ''የእምርታ ቀንን'' በከተማ ዉስጥ የሚገኙ በአምራች ዘርፍ ዉስጥ ምርት ላይ ያሉ ፣ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት እና የፓናል ዉይይት በማድረክ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ ።

06/09/2026
አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ! #ጳጉሜን1 ፦ የእመርታ ቀንጳጉሜን፤ የአሮጌው ዓመት መደምደሚያ፣ የአዲሱ ዓመት መነሻ ነው። አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ እንቀበላ...
06/09/2026

አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ!

#ጳጉሜን1 ፦ የእመርታ ቀን

ጳጉሜን፤ የአሮጌው ዓመት መደምደሚያ፣ የአዲሱ ዓመት መነሻ ነው። አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ እንቀበላለን።

በፈጠራና በፍጥነት በታጀበው ሀገራዊ ሪፎርም፣ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ ዕድገት ወደ እመርታዊ ለውጥ እየተሸጋገረች ትገኛለች።

ይህ እመርታም በተጨባጭ ውጤቶች ተገልጧል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ወደ ሥራ በመግባቱ በተፈጠረው መነቃቃት፣ የኮሪደር ልማቶች፣ በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ እውን የሆኑ ፕሮጀክቶችና የፈጠሯቸው አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች የዚህ እመርታ መገለጫዎች ናቸው።

በስንዴ አብዮትና በሌማት ትሩፋት በግብርናው፣ በትምህርትና ሥልጠና እና በጤና ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችም የዚህ እመርታ ተጨባጭ ማሳያዎች ናቸው።

በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በዲጂታላይዜሽን አዳዲስ አቅሞችን እየገነባን፣ በኢንዱስትሪ ምርትና ምርተማነትን እያሳደግን፣ በቱሪዝም ያለንን ሀብት ወደ ዕድል እየቀየርን፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ አዳዲስ የዕድገት አድማሶችን መክፈት ችለናል፡፡

ይህን እምራተዊ ለውጥ ቀጣይነት ማረጋገጥ የሚችለው የሰው ሀይላችን ነው፡፡ ስለሆነም ገበያ መር በሆነው የክህሎት ልማት እና ክህሎት መር የሆነውን የሥራ ዕድል ፈጠራ አጠናክሮ በማስቀጠል እንዲሁም ሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነቱን በማጠናከር በመስኩ የተመዘጉቡ ውጤቶችን በማላቅና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ርብርቡ በአዲሱ ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

05/09/2026
የደቡብ ወሎ ዞን የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር መዘጋጀቱን አስታወቀየደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል ...
04/09/2026

የደቡብ ወሎ ዞን የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትን በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር መዘጋጀቱን አስታወቀ

የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል አጠቃላይ መሪ ሐሳብ በዞን እና በወረዳ ደረጃ በልዩ ልዩ ሁነቶች ለማክበር ዝግጅት ማጠናቀቁን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን ገለጹ።

አቶ አሊ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበርን አስመልክተው ለደቡብ ወሎ ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ በሰጡት መግለጫ፣ ዘንድሮ ቀናቱ “የኢትዮጵያ መንሠራራት” በሚል አጠቃላይ መሪ መልዕክት በልዩ ልዩ አገር አቀፍ፣ ክልላዊና ዞናዊ ሁነቶች እንደሚከበሩ አስታውቀዋል፡፡

ዋና አስተዳዳሪው በሰጡት መግለጫ፣ የጳጉሜን ወር ያለፈውን ዓመት ስኬትና ጉድለት መገምገሚያ፣ የመጪውን አዲስ ዓመት ዕቅድ ለመተግበር የዝግጅት ምዕራፍ ማጠቃለያ እንዲሁም የትግበራ ምዕራፍ ዋዜማ ሆኖ የሚያገለግል ልዩ ወቅት መሆኑን ጠቁመዋል።

የአከባበሩ ዐቢይ ዓላማም ኢትዮጵያ ከአግድሞሽና ከዝቅታ ጉዞ ተላቃ በሁሉም ዘርፎች ወደ ላቀ ከፍታ ማንሠራራት መጀመሯን በማብሰር፣ ለበለጠ ሀገራዊ ውጤት በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ መነሳሳትንና የተስፋ መንፈስ መፍጠር እንደሆነ ዋና አስተዳዳው አብራተዋል።

እንደ አቶ አሊ መኮንን ማብራሪያ፣ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ሁነቶችና ተያያዥ ጭብጦች ይከበራሉ፦

ጳጉሜን 1 (እመርታ ቀን)፦ ሀገራችን ከተረጂነትና ጥገኝነት ተላቃ ወደ አምራችነት እያደረገች ያለችውን ታሪካዊ ሽግግር ለማብሰር፣ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬቶች፣ የምግብ ሉዓላዊነት ድሎች እና የ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄ ውጤቶች በሰፊው ይታወቃሉ።

ጳጉሜን 2 (መንሠራራት ቀን)፦ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ ሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደቶችና ማኅበራዊ ዕድገቶች በዜጎች የዕለት ተዕለት ሕይወት ላይ ያመጧቸው አዎንታዊ ተፅዕኖዎች ይበልጥ ይጎላሉ።

ጳጉሜን 3 (ጽናት ቀን)፦ የፀጥታ ተቋማትን ዘመናዊ ቁመናና ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ሉዓላዊነት የተከፈለውን የጀግኖች መስዋዕትነት በመዘከር፣ የሀገር መከላከል ዓቅማችንና ሀገራዊ ፅናት ለሁለንተናዊ ዕድገት መሠረት መሆናቸው ይበሰራል።

ጳጉሜን 4 (ኅብር ቀን)፦ ኅብረብሔራዊ አንድነትን፣ አብሮነትን፣ መረዳዳትንና በጎነትን ማዕከል ያደረጉ ሁነቶች በመከወን የወል ትርክትን የማጠናከርና ብዝኃነትን የማጎልበት ሥራዎች ይከናወናሉ።

ጳጉሜን 5 (ነገ ቀን)፦ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የሳይበር ሉዓላዊነት፣ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የ«5 ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ» ስኬቶችን በማሳየት ዲጂታልና በራስ አቅም የምትቆም አዲሷን ኢትዮጵያ የሚያመላክቱ ሁነቶች ይካሄዳሉ ሲሉም በዝርዝር አብራርተዋል።

በመጨረሻም ዋና አስተዳዳሪው “መንሠራራት” የሚለው መሪ ሐሳብ ሀገራችን ችግሮችን ከመቋቋም ወደ ፈጣንና ዘላቂ የከፍታ ምዕራፍ የምትሸጋገርበትን ስትራቴጂካዊ ሂደት የሚያመለክት በመሆኑ፣ የዞኑ ማኅበረሰብና የመንግሥት አካላት ቀናቱን በላቀ ተነሣሽነትና በተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርበዋል።
*****

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!​የ 2018 ዓ.ም ጳጉሜን ቀናት፤​-ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)-ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)-ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)-ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን)-ጳጉሜን 5 (የነገ...
04/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!
​የ 2018 ዓ.ም ጳጉሜን ቀናት፤
​-ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)
-ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)
-ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)
-ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን)
-ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን)
​በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል፡፡
~•~•~•~•

Address

Dessie

Telephone

+251911875396

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share