Dessie PP Youth Wing

Dessie PP Youth Wing የደሴ ከተማ ብልፅግና ፖርቲ ወጣቶች ክንፍ የወጣቶች ፓለቲካዊ:ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንሰራለን!

01/06/2026
ወጣት ይምረጥ፤ ሀገር ትፅና !በቧንቧ ውሃና በመናፈሻ ክፍለ ከተሞች "ወጣት ይምረጥ፤ ሀገር ትፅና" በሚል መሪ ቃል በአደባባይ የቡና ጠጡ ፕሮግራምና በኪነጥበብ ምሽት  የምርጫ ቅሰቅሳ መርሀ-...
22/05/2026

ወጣት ይምረጥ፤ ሀገር ትፅና !

በቧንቧ ውሃና በመናፈሻ ክፍለ ከተሞች "ወጣት ይምረጥ፤ ሀገር ትፅና" በሚል መሪ ቃል በአደባባይ የቡና ጠጡ ፕሮግራምና በኪነጥበብ ምሽት የምርጫ ቅሰቅሳ መርሀ-ግብር ተካሂዷል።

የዚህ ዘመን ወጣት የነገዋን ኢትዮጵያ ተረካቢ ብቻ ሳይሆን የዛሬዋን ሀገር በፅኑ መሰረት ላይ የሚገነባ ኃይል ነው።

ሀገር እንድትጸና ወጣቱ ትውልድ በኃላፊነት ስሜት መነሳት አለበት። እያንዳንዱ ወጣት የሚመርጠው መንገድ፣ የሚሰጠው ድምፅ እና የሚከተለው አላማ የነገዋን ሀገር መልክ ይወስናል። ስለዚህ "ወጣት ይምረጥ" ሲባል ለሀገር የሚበጀውን፣ ለትውልድ የሚተርፈውን እና ሰላምን የሚያረጋግጠውን ይምረጥ ማለት ነው።

ኢትዮጵያን በኢኮኖሚ የፈጠነች፣ በማኅበራዊ መስክ የበለጸገችና በፖለቲካዊ ምኅዳር የጎለመሰች "ተምሳሌት ሀገር" የማድረግ ትልቁ ኃላፊነት በወጣቱ ትከሻ ላይ ያረፈ ነው።

ይህ ራዕይ ከቃል ባለፈ ወደ ተግባር የሚቀየረው ወጣቶች በየአካባቢያቸው ለሚያጋጥሙ ችግሮች አዎንታዊ ምላሽ ሲሰጡ፣ በልማትና በሰላም ግንባታ ሂደት ላይ ንቁ ተሳትፎ ሲያደርጉ እና ለሀገር አንድነት የሚበጁ አማራጮችን አጥርተው መምረጥ ሲችሉ ብቻ ነው።

የኪነ ጥበብ ምሽት መርሀ ግብሩ ትናንት ማታ የተካሄደ ሲሆን የቡና ጠጡ ፕሮጋራሙ በዛሬው እለት ተከናውኗል።

ብልጽግናን ይምረጡ!
ምልክታችን የስንዴ ነዶ ነው!


#ምርጫ2018

!!

!!

"ወጣቱ ትውልድ የነገዋን ጠንካራና የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚደረገው ጉዞ ውስጥ  በቁርጠኝነትና በባለቤትነት ስሜት ግንባር ቀደም መሆን አለበት" አሸናፊ ዓለማየሁየደሴ ከተማ ብልጽግና...
20/05/2026

"ወጣቱ ትውልድ የነገዋን ጠንካራና የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚደረገው ጉዞ ውስጥ በቁርጠኝነትና በባለቤትነት ስሜት ግንባር ቀደም መሆን አለበት" አሸናፊ ዓለማየሁ

የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ ተጽዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮችና በመጭው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

​ በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደሴ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለማየሁ እንደገለፁት ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶችን የለውጡ ቀዳሚ ሞተርና የሀገር ግንባታ የጀርባ አጥንት አድርጎ እንደሚመለከት ገልጸዋል።

አክለውም ፓርቲው የያዘውን ሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ የወጣቶች የፖለቲካ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን እንደሚያምን አስገንዝበዋል።

​ወጣቶች የፓርቲውን ራዕይና ተልዕኮ በመረዳት ረገድ ግንባር ቀደም መሆን እንዳለባቸውና በየአካባቢያቸው የሰላምና የልማት አምባሳደር እንዲሆኑ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

ምርጫው ዲሞክራሲያዊና ሰላም ሆኖ እንዲጠናቀቅ እና ብልጽግና ፓርቲ በአብላጫ ድምፅ እንዲያሸንፍ ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው በመድረኩ ተመላክቷል።

የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አዝመራ ማስረሻ በበኩላቸው ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶችን የፖለቲካና የነፃነት እድል ከማስፋት ባለፈ ለኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው መሰረት የጣለ ሀገር በቀል ትልቅ ፓርቲ መሆኑን ተናግረዋል።

ወጣቱ ክፍል የቀጣይ የተጠቃሚነት እድሉን ለማስፋት በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበትም ወ/ሮ አዝመራ አሳስበዋል።

ብልፅግና ፓርቲ ለሀገራዊ ለውጥ ያበረከተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን በመግለፅ በለውጡ ሂደትም የወጣቱ ተሳትፎ ሚና ከፍተኛ እንደነበር ጠቁመዋል።

የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ግርማ እሸቱ የወጣቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማፅናት ሁለንተናዊ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚያስፈልግ እና በሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ብልጽግናን በመምረጥ የቀጣይ የኢትዮጵያን እጣ ፈንታ መወሰን ያስፈልጋል ብለዋል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያን የእድገት ግስጋሴ ለማስቀጠል ድምፃችንን ለብልጽግና በመስጠት ሀገራዊ ሀላፊነታችንን መወጣት እንደሚጠበቅ ለወጣቱ ጥሪ አቅርበዋል።

ተሳታፊ ወጣቶቹ የለውጡ መንግስት ለወጣቶች የሰጠውን የተጠቃሚነት እድል ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲ ምልክት የሆናውን የስንዴ ነዶ እንደሚመርጡ ተናግረዋል።



በደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በወጣትና በሴት ክንፍ አስተባባሪነት በተዘጋጀ የኪነጥበብ ምሽት  የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ተወዳዳሪ እጩዎችን፣ የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅና የምር...
19/05/2026

በደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በወጣትና በሴት ክንፍ አስተባባሪነት በተዘጋጀ የኪነጥበብ ምሽት የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ተወዳዳሪ እጩዎችን፣ የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅና የምርጫ ቅስቀሳ መርሀ-ግብር ተከናውኗል።

በልዩ ልዩ የኪነጥበብ ምሽት ፕሮግራም የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ የምርጫ ምልክትና እጩዎች ተዋውቀዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዓለማየሁ በፓርቲው ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴዎችና ስኬቶች ውስጥ ወጣቶች የማይተካ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ከፍታ በሁሉም መስኮች ለማረጋገጥ ተግቶ እየሠራ የሚገኝ ፓርቲ መሆኑን አውስተው፣ መጪው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና አሳታፊ እንዲሆን ወጣቶች በትጋት መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫም በላቀ የሕዝብ ተሳትፎ እንዲሳካና ፓርቲው በአብላጨ ድምፅ እንዲያሸንፍ አሁንም ወጣቶች በባለቤትነት መንፈስ በትጋት ሊሳተፉ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በፕሮግራሙ የተለያዩ የባህል ሙዚቃዎች፣ውዝዋዜዎች፣ሰርከስ፣ጭውውቶችና ግጥሞች ቀርበዋል።

ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ፣ፍትሀዊ፣ነፃ፣ተዓማኒና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቱ የድርሻውን እንዲወጣ ተጠይቋል።

በመርሃ ግብሩ የክልል ደጋፊ አመራሮች፣የከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ወጣቶች፣ሴቶችና የኪነጥበብ ሰዎች ተገኝተዋል።
#ምርጫ2018

16/05/2026

የተከበሩ አቶ ሳሙዔል ሞላልኝ

በ7ኛው አገራዊ ምርጫ በደሴ ምርጫ ክልል ፓርቲያችን ብልፅግናን ወክለው ለክልል ም/ቤት እጩ ሆነው ቀርበዋል።

!!
!!
!!

"ወጣቱ በምርጫ ሂደት ውስጥ ያለውን ቁልፍ ሚና በመገንዘብ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ አለበት" አቶ አሸናፊ ዓለማየሁኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ...
12/05/2026

"ወጣቱ በምርጫ ሂደት ውስጥ ያለውን ቁልፍ ሚና በመገንዘብ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ አለበት" አቶ አሸናፊ ዓለማየሁ

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ቃል የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከከተማው ወጣት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አቶ አሸናፊ አለማየሁ እንደ ከተማ የሰከነ ወጣት በመፈጠሩ የወል ትርክትን የሚገነባና ነጠላ ትርክትን የማይቀበል በመሆኑ ከተማችን ባለፉት አመታት በርካታ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

ባለፉት አምስት ዓመታት ከወጣቶች ጋር በልማትና በሰላም ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ የተሳካ ልማት ማከናወንና ሰላምን ማስጠበቅ መቻሉን ገልጸዋል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ነፃ፣ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በህዝብ ተቀባይነት ያለው ምርጫ በሰላም፣ በነፃነትና በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲከናወን ወጣቱ የሰላም ዘብ በመሆን የድርሻውን ሊወጣ ይገባልም ብለዋል ።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ውይይቱ ተገኝተው እንደተናገሩት ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ በስኬት እንዲጠናቀቅ የወጣቱ ሚና ከፍተኛ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

​ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ሽቤ ክንዴ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ለማሳካት ወጣቱ የብጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶን በመምረጥ አሻራውን ማስቀመጥ እንደሚገባው አመላክተዋል።

በደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በወ/ሮ አዝመራ ማስረሻ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ተሳታፊ ወጣቶችም በበኩላቸው በምርጫው ሂደት ንቁ ተሳትፎ ለማድረግና ለሀገራዊ አንድነት እንደሚሰሩና ብልጽግና ፓርቲ በአብላጫ ድምፅ እንዲያሸንፍ ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል።

የምርጫው ሂደት በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

በመድረኩ የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙዔል ሞላልኝ፣የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ሽቤ ክንዴ፣ወ/ሮ ንፁህ ሽፈራው አማራ ክልል ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ም/ኃላፊ እና የደሴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ አለማየሁን ጨምሮ የከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።



#ብልፅግናፓርቲንይምረጡ

11/04/2026

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው ለሰው ልጆች ሁሉ የዘላለም ሕይወትንና ተስፋን ለመስጠት ነው። ይህ በዓል ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከጥል ወደ ይቅርታ የምንሻገርበት ይሁንልን።
በተለይም ወጣቶች በዚህ የትንሳኤ ብርሃን ተመርታችሁ፣ ለሀገራችን ሰላምና ለወገኖቻችን ፍቅር የምታበስሩ እንድትሆኑ እመኛለሁ።
መልካም በዓል!

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dessie PP Youth Wing posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share