01/09/2026
በሚቀጥሉት አስር ቀናት ለዝናብ መፈጠር ምቹ የአየር ሁኔታ እንደሚኖር ይጠበቃል።
ከምስራቅ አማራ ሜትሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በሚቀጥሉት አስር ቀናት ለዝናብ መፈጠር ምቹ የአየር ሁኔታ ይኖራል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአብዛሀኛው የምስራቅ አማራ አካባቢዎች አልፎ አልፎ ባሉት ቀናት ቀላል መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ይጠበቃል።
በተወሰኑ የምስራቅ አማራ አካባቢዎች ደግሞ እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ በተመሳሳይ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በእድገት ላይ ለሚገኙ ሰብሎች ለረዥም ጊዜ ቋሚ ሰብሎች ፣ ለእስሳት የግጦሽ ሳር ልምላሜ፣ ለከርሰ ምድር እና ገፀ ምድር ውሀ የራሱ የሆነ አስተዋጽኦም አለው።
አርሶአደሩ እና በግብርናው ዘርፍ የሚሰሩ አካላት እርጥበት አጠር በሆኑ አካባቢዎች ውሀን ለማከማቸት የሚጠቀሙበት ጊዜ በመሆኑ አስቀድመው የወትሮው ዝግጁነት እንዲኖራቸው ተጠቁሟል።
መረጃው ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 የተወሰደ ነው።