South Wollo Zone Gov. Communication Dept.

South Wollo Zone Gov. Communication Dept. የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ
ደሴ

ታዛቢዎች ያለገደብ ምርጫውን መታዘብ ችለዋል - ህብረት ለምርጫአዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ህብረት ለምርጫ ታዛቢዎች 99 በመቶ ያለ...
01/06/2026

ታዛቢዎች ያለገደብ ምርጫውን መታዘብ ችለዋል - ህብረት ለምርጫ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ህብረት ለምርጫ ታዛቢዎች 99 በመቶ ያለምንም ገደብ ወደ ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ገብተው መታዘብ ችለዋል አለ።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ህብረት ለምርጫ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ ቀን 7 ሰዓት ያሉትን የትዝብት ግኝቶችን ብቻ ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርጓል።
ህብረት ለምርጫ በመግለጫው፤ ለምርጫው 2 ሺህ 258 ተቀማጭ እና 891 ተንቀሳቃሽ በአጠቃላይ 3 ሺህ 149 ታዛቢዎችን ከማለዳው 11 :30 ጀምሮ በ2 ሺህ 258 ድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ላይ አሰማርቶ እየታዘበ እንደሆነ ገልጿል።
በዚህም እያንዳንዱ ታዛቢ ቢያንስ 6 ጣቢያዎችን እንዲታዘብ መሰማራታቸውንና ታዛቢዎች 99 በመቶ ያለምንም ገደብ ወደ ድምጽ መስጫ ጣቢያዎቹ ገብተው መታዘብ መቻላቸውን አስታውቋል።
ታዛቢዎች ከተሰማሩባቸው 2 ሺህ 258 ጣቢያዎች ውስጥ 2 ሺህ 183 የምርጫ ጣቢያዎች ወይም 97 በመቶ ያህሉ የህብረቱ ታዛቢዎች በስፍራው ሲደርሱ የምርጫ አስፈፃሚዎች በቦታው እንደነበሩ አስረድቷል።
ኅብረቱ ከታዘባቸው 2 ሺህ 258 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል በ947 (42 በመቶ) ጣቢያዎች የድምፅ መስጠት ሂደቱ ከማለዳ 12 ሰዓት በፊት መጀመሩንና በ1 ሺህ 276 (57 በመቶ ) ጣቢያዎች ደግሞ ከማለዳ 12 እስከ 1 ሰዓት ባለው ጊዜ መጀመሩን ታዝቧል።
በተቃራኒው 32 (1 በመቶ ) ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ከጠዋቱ 1 ሰዓት በኋላ መጀመሩንና በ3 ጣቢያዎች ይህ መግለጫ እስከተዘጋጀበት ሰዓት ድረስ የድምፅ አ
FBC

ምስጢረ ሥላሴ ታምራት ድምጽ ሰጡየኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ምስጢረ ሥላሴ ታምራት ድምጻቸውን ሰጥተዋል።FBC
01/06/2026

ምስጢረ ሥላሴ ታምራት ድምጽ ሰጡ
የኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ምስጢረ ሥላሴ ታምራት ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
FBC

🇪🇹🗳️ "በነፃነት ድምፃችንን ሰጥተናል" የአምበር ከተማ ነዋሪዎች7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በምሥራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ አምበር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች እየተካሄደ ይገኛል።አሚኮ ያነጋ...
01/06/2026

🇪🇹🗳️ "በነፃነት ድምፃችንን ሰጥተናል" የአምበር ከተማ ነዋሪዎች

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በምሥራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ አምበር ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች እየተካሄደ ይገኛል።

አሚኮ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መብታቸውን ተጠቅመው ይመራናል ያሉትን ፓርቲ መምረጣቸውን ገልጸዋል። በዚህ ምርጫ መሳተፋቸው ለቀጣይ አምስት ዓመታት በራሳቸው ድምጽ በመረጡት ፓርቲ ለመተዳደር እንደሚያስችላቸውም ተናግረዋል።

ምርጫ የሀገርን ሰላም እና አንድነት ለማስጠበቅ ትልቅ ትርጉም ያለው መኾኑን የጠቀሱት ነዋሪዎቹ፣ የምርጫ ካርድ ያወጣ ዜጋ ሁሉ ሰዓቱ ሳያልቅ ወደ ምርጫ ጣቢያ በመሄድ የሚፈልገውን እንዲመርጥም አሳስበዋል።
አሚኮ

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነዉ! በደቡብ ወሎ ዞን የለጋምቦ  ወረዳ ነዋሪዎች ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጮች ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነዉ!
በደቡብ ወሎ ዞን የለጋምቦ ወረዳ ነዋሪዎች ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጮች ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!በምዕራብ ጎንደር ዞን ሁሉም ወረዳ እና ከተማ አስተዳድሮች በ7ኛው አገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በርካታ መራጮች ድምጽ የመስጠቱ ሂደቱ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ።
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
በምዕራብ ጎንደር ዞን ሁሉም ወረዳ እና ከተማ አስተዳድሮች በ7ኛው አገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በርካታ መራጮች ድምጽ የመስጠቱ ሂደቱ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ።

በደቡብ ወሎ ዞን ሀርቡ ከተማ አስተዳደር ዜጎች ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ ናቸው።
01/06/2026

በደቡብ ወሎ ዞን ሀርቡ ከተማ አስተዳደር ዜጎች ይበጀኛል ያሉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ ናቸው።

ኢትዮጵያ🇪🇹 እየመረጠች ነው!በምስራቅ ጎጃም ዞን በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ በቀራንዮ ንዑስ ከተማ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነዋሪዎች ድምፅ እየሰጡ  ነው።
01/06/2026

ኢትዮጵያ🇪🇹 እየመረጠች ነው!
በምስራቅ ጎጃም ዞን በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ በቀራንዮ ንዑስ ከተማ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነዋሪዎች ድምፅ እየሰጡ ነው።

ከኃይል እርምጃ ወደ ሰላማዊ ምርጫ ! ብቸኛ የሥልጣን ምንጭ የሕዝብ ድምጽ ሊኾን እንደሚገባ የሰላም አማራጭን የተቀበሉ መራጮች ተናግረዋል።የኃይል አማራጭን በመጠቀም በትጥቅ ትግል ሲንቀሳቀሱ ...
01/06/2026

ከኃይል እርምጃ ወደ ሰላማዊ ምርጫ !
ብቸኛ የሥልጣን ምንጭ የሕዝብ ድምጽ ሊኾን እንደሚገባ የሰላም አማራጭን የተቀበሉ መራጮች ተናግረዋል።
የኃይል አማራጭን በመጠቀም በትጥቅ ትግል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለው በምርጫ ሂደቱ እየተሳተፉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ከኃይል አማራጭ ይልቅ ሰላምን በማስቀደም ድምጻቸውን ይወክለኛል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ መስጠታቸውን ነው የተናገሩት።
ምርጫ በሕዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው መንግሥት ለመመስረት የሚያግዝ እና የሕዝብን የሥልጣን ባለቤትነት የሚያረጋግጥ በመኾኑ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል በምርጫው ሊሳተፍ እንደሚገባም ገልጸዋል።

በዳዋ ጨፋ ምርጫ ክልል ገርቢ 1 ምርጫ ጣቢያ  ድምፃቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች 'ለቀጣይ ዓመታት ይበጀናል ያልነውን አካል መርጠናል' አሉ።
01/06/2026

በዳዋ ጨፋ ምርጫ ክልል ገርቢ 1 ምርጫ ጣቢያ ድምፃቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች 'ለቀጣይ ዓመታት ይበጀናል ያልነውን አካል መርጠናል' አሉ።

''በሀገር ላይ ድርሻ ስላለን የምንፈልገውን ፓርቲ መርጠናል'' አካል ጉዳተኞችየቡሬ ከተማ ነዋሪዎች ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። በምርጫው አካል ጉዳተኞች እየተሳተፉ ነው።  ለአሚኮ አስተያየታ...
01/06/2026

''በሀገር ላይ ድርሻ ስላለን የምንፈልገውን ፓርቲ መርጠናል'' አካል ጉዳተኞች
የቡሬ ከተማ ነዋሪዎች ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። በምርጫው አካል ጉዳተኞች እየተሳተፉ ነው።
ለአሚኮ አስተያየታቸውን የሰጡት ፍሬው አልማው እና ወንድሙ ታደሰ ምርጫው እስኪደርስ በጉጉት ሲጠብቁ መቆየታቸውን አንሰተዋል። ''እኛ አካል ጉዳተኞች በሀገር ላይ ድርሻ ስላለን የምንፈልገውን ፓርቲ መርጠናል'' ብለዋል።
በቀጣይም ከሚመሠረተው መንግሥት ጎን በመኾን የበኩላቸውን እንደሚወጡ ነው የጠቆሙት።
አሚኮ

Address

Dessie

Telephone

+251331117687

Website

http://www.southwollocommunication.gov.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Wollo Zone Gov. Communication Dept. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to South Wollo Zone Gov. Communication Dept.:

Share