05/09/2026
በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ ታጥቀው በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀበሉ።
ደባርቅ፡ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም (የሰሜን ጎንደር ኮሙኒኬሽን)
በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በምስራቁ ቀጠና ታጥቀው በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል።
የሃገር መከላከያ ሰራዊት የ10ኛ ዕዝ ዘመቻ አመራሮችና አባላት፣ የሰሜን ጎንደር ዞን እና የደባርቅ ወረዳ አመራሮች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ በየደረጃው ያሉ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎች አካላት ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።
መረጃዉ የደባርቅ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነዉ።