South Ethiopia Regional State Water and Energy Bureau

South Ethiopia Regional State Water and Energy Bureau ንጹህ ውሃ፣ሳኒቴሽንና ታዳሽ ኃይል፤ለዘላቂ ህይወት! Clean Water,Sanitation & Renewable Energy for a Sustainable Life!

የሠራተኞች የጋራ ትብብር፣ ተነሳሽነትና አብሮነት ለተቋማዊ ስኬት ወሳኝ ነው። ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝነሐሴ 21/2018 ዓ.ም፥ዲላየአንድ ተቋም የሰው ኃይሉ የመተባበር መንፈስና ተነሳሽነት ለተ...
27/08/2026

የሠራተኞች የጋራ ትብብር፣ ተነሳሽነትና አብሮነት ለተቋማዊ ስኬት ወሳኝ ነው። ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም፥ዲላ

የአንድ ተቋም የሰው ኃይሉ የመተባበር መንፈስና ተነሳሽነት ለተቋሙ ስኬት ቀዳሚውን ሚና እንደሚጫወት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ገለጹ።

ኃላፊው ከአገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳትፎአቸው መልስ ከቢሮው አጠቃላይ ሠራተኞች ጋር በተቋሙ ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ በመወያየት አስፈላጊውን የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

ከውይይቱ አስቀድሞም አጠቃላይ የተቋሙ ሠራተኞች «የእንኳን ደህና መጡ» አቀባባል አድርገውላቸዋል።

ኢንጂነር አክሊሉ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የአገራዊ ምክክር ጉባኤው የአገሪቱን የወደፊት ተስፋ የሚያለመልም፣ የበርካታ ዜጎች ልዩ ልዩ ሐሳቦች በሰፊው የተንጸባረቁበትና በአንድነት የተቋጨበት ታላቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ የዜጎች የአንድነት ሐሳብም አገሪቱን ወደ ላቀ የዕድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችል መሆኑ በብዙዎች የታመነበት መሆኑን አስታውሰዋል።

ከዚህ ባሻገር፣ ኃላፊው በተቋሙ በተጠናቀቀው የሠራተኞች የድልድል ጉዳይ ላይ ሐሳብ የሰጡ ሲሆን፤ ሁሉም ሠራተኛ በመመሪያው መሠረት መመደቡ ለተቋሙ ስኬት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በውሃ ዘርፍ ብቻ 117 ተቋማት ተገንብተው እስከ 500 ሺህ የሚጠጉ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን ጠቅሰው፤ የዚህ ስኬት ማዕከል የሠራተኛው የላቀ ጥረት መሆኑን አድንቀዋል።

በተጨማሪም በአዲሱ የተቋሙ ሠራተኞች ድልድል መሠረት ሠራተኛው የየድርሻውን በመወጣት ለቀጣይ ተቋማዊ ድሎች በጋራ እንዲተጋ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል መንግሥት በሚከተለው «ከተረጅነት ወደ ምርታማነት» መርህ መሠረት ሠራተኛው በመደበኛ ሥራው የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል።

ከዚህም በተጨማሪ «ለአደጋ ያልተጋለጠ ማኅበረሰብ ለመፍጠር» በሚለው የመንግሥት ዕቅድና ማሻሻያ ውስጥ የሠራተኛው ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፣ እያንዳንዱ ሠራተኛ በግለሰብ ደረጃ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

የአለም አቀፋዊ የአየር ለውጥና በኤልኒኖ ሳቢያ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፈጥሮአዊ አደጋዎችን ለመመከት የሚያስችሉ ክልላዊ ቅድመ ዝግጅት ላይ ሁሉም የቢሮው ማህበረሰብ አባላት የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

ንጹህ ውሃ፣ሳኒቴሽንና ታዳሽ ኃይል፤ለዘላቂ ህይወት!
Clean Water,Sanitation & Renewable Energy for a Sustainable Life!

የቢሮው የህዝብ ግኑኝነት ዳይሬክቶሬት
የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026

የተጀመሩ የውሃ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በተያዘው ጊዜ በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በትኩረት ይሰራልየደቡብ ኢትዮጵያ ውሃ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት...
25/08/2026

የተጀመሩ የውሃ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በተያዘው ጊዜ በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል

የደቡብ ኢትዮጵያ ውሃ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ በአርባምንጭ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊና የቦርዱ ሰብሳቢ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ማጠቃለያ ባስተላለፉት መልዕክት የተጀመሩ ሥራዎችን በወቅቱ ማጠናቀቅ የተቋሙን ትርፋማነትና ውጤታማነት ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።

ኮርፖሬሽኑ በመስኖ፣ በጉድጓድ፣ በግድብና በቁፋሮ ዘርፎች የሚያከናውናቸው የውሃ ሥራዎች ለተቋሙ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘት እንዳለባቸውም አመላክተዋል።

በመንግስት የሚሰጡ ሥራዎች ላይ ብቻ ጥገኛ ከመሆን በመላቀቅ ሥራዎችን በንቃት በመፈለግ በሁሉም ዘርፎች ተወዳዳሪ ተቋም ለመሆን መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በኮርፖሬሽኑ በ2018 ዓ.ም በመጠጥ ውሃና በጉርጓድ ፋርም ዘርፍ ሰባት ፕሮጀክቶች የግንባታ ውል ተፈጽሞ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን በመስኖና በግድብ ግንባታ ዘርፍም የተሻለ የሥራ አፈጻጸም መመዝገቡ ተመላክቷል።

በመስኖና በግድብ ግንባታ ከተያዙት አምስት ኮንትራቶች አራቱ የመስኖ፣ አንዱ የጎርፍ መከላከያ ሥራ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ በደራሼ ዞን የሚገኘው የአርጎባ መስኖ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለሕብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት መጀመሩም ተገልጿል።

በተጨማሪም በጋሞ ዞንና በባስኬቶ ዞን የሚገኙ ሁለት የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ መጠናቀቁም ተብራርቷል።

የቦርድ አባላት በሰጡት አስተያየት የተጀመሩ ሥራዎች በትኩረት እንዲመሩና ፕሮጀክቶችን በጥራትና በተያዘላቸው ጊዜ ማጠናቀቅ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በቀጣይ የሥራ አመራር ሥርዓትን ማሻሻል፣ የሥራ አፈጻጸም ክትትልና ቁጥጥርን ማጠናከር እንደሚገባም ገልፀዋል።

በሁሉም የውሃ ልማት ዘርፎች ተወዳዳሪ በመሆን ተጨማሪ ሥራዎችን ማምጣት እና የተቋሙን ትርፋማነትና ተወዳዳሪነት ማሳደግ እንዳለበት አፅንዖት ተሰጥቷል።

"የክልሉን የውሃ ልማት ፍላጎት ለመመለስ ተግባራትን በጥራትና በጊዜ ማስፈጸም የተቋሙ ቀዳሚ ትኩረት መስክ ነው" የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም የክል...
25/08/2026

"የክልሉን የውሃ ልማት ፍላጎት ለመመለስ ተግባራትን በጥራትና በጊዜ ማስፈጸም የተቋሙ ቀዳሚ ትኩረት መስክ ነው" የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ ሥራዎች ኮርፖሬሽን

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም

የክልሉ ውሃ ስራዎች ኮርፖሬሽን ቦርድ አባላት የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ የምክክር መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እያካሄዱ ይገኛል

የቦርዱ ሰብሳቢና የክልሉ ዉሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት የኮርፖሬሽኑን የሥራ አፈጻጸም በመገምገም የተያዙ ዕቅዶችን በተቀናጀ ሁኔታ ለመፈጸም የሁሉም አካላት ተሳትፎና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የመድረኩ ዋና ዓላማ በቀጣይ ጊዜ የውሃ ልማትና ግንባታ ሥራዎችን በተሻለ አቅም፣ ጥራትና ቅልጥፍና ለማከናወን የሚያግዙ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን መለየት መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አብርሃም አሻ (ዶ/ር) በበኩላቸው የክልሉን የውሃ ልማት ፍላጎት ለመመለስ ተግባራትን በጥራትና በጊዜ ማስፈጸም የተቋሙ ቀዳሚ ትኩረት መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እየተገመገሙ ሲሆን የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦጰውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ፣ የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ እና የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ውሃ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም አሻ ጨምሮ የኮርፖሬሽኑ የቦርድ አባላትና የኮርፖሬሽኑ ማናጅመንት አባላት እየተሳተፉ ይገኛል።

የጎርፍ አደጋ ቅነሳ ሥራዎችን በጥናት ለመምራት ትኩረት ተሰጥቷልአርባምንጭ፦ ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም በስምጥ ሸለቆ ሐይቆችና  በኦሞ–ጊቤ ወንዝ ተፋሰሶች የሚከሰቱ የጎርፍ አደጋዎችን በዘላቂነ...
22/08/2026

የጎርፍ አደጋ ቅነሳ ሥራዎችን በጥናት ለመምራት ትኩረት ተሰጥቷል

አርባምንጭ፦ ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም

በስምጥ ሸለቆ ሐይቆችና በኦሞ–ጊቤ ወንዝ ተፋሰሶች የሚከሰቱ የጎርፍ አደጋዎችን በዘላቂነት ለመቀነስ በጥናት የተለዩ ተጋላጭና የቅድሚያ ቅድሚያ ቦታዎችን በመለየት ለመተግበር ትኩረት ተሰጥቷል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት የጎርፍ ተጋላጭ አካባቢዎችን በጥናት በመለየት የጎርፍ አደጋን ለመቀነስ የሚያስችሉ የተቀናጁ የጎርፍ መከላከል ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በአርባምንጭ ሀይሌ ሪዞርት እየተካሄደ ባለው የግምገማ ወርክሾፕ በሁለቱ ተፋሰሶች የጎርፍ አደጋ ቅነሳ ለማድረግ የተዘጋጁ ጥናቶች በባለሙያዎችና በባለድርሻ አካላት እየተገመገሙ ሲሆን፣ የተገኙ ምክረ ሀሳቦችም ለቀጣይ ሥራዎች እንደ ግብዓት እየተወሰዱ ነው።

የጎርፍ አደጋ ቅነሳ ሥራው ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ ቢሮ፣ ከአደጋ ስጋት ኮሚሽን፣ ከአማካሪዎችና ከሌሎች ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተተገበረ ይገኛል። ይህም ሥራዎቹ በሳይንሳዊ ጥናት፣ በአካባቢያዊ ተሞክሮና በአደጋ ስጋት መረጃ ላይ እንዲመሠረቱ የሚያግዝ መሆኑ ተመልክቷል።

በዚህ ትብብር ዩኒቨርሲቲዎች በጥናትና በሳይንሳዊ ትንተና፣ የክልሉ ውሃ ቢሮ በአካባቢው የውሃ ሀብትና የተፋሰስ አስተዳደር እውቀት፣ አደጋ ስጋት ኮሚሽኑ ደግሞ በአደጋ ስጋት መረጃና ምላሽ ላይ ያለውን ሙያዊ ግብዓት እያበረከቱ ነው።

የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ተመስገን ከተማ እንደገለጹት፣ የጎርፍ አደጋ ቅነሳ ከአጭር ጊዜ የአደጋ ምላሽ በተጨማሪ ዘላቂ የሆነ የተቀናጀ ዕቅድና በጥናት የተደገፈ መፍትሔ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ተጋላጭ አካባቢዎችን በመለየት ተገቢ ሥራዎችን በቅድሚያ ለመተግበር ትኩረት ተሰጥቷል።

እስካሁን በርካታ የቅድመ ጎርፍ መከላከል ሥራ በመከናወኑ፣ የሰዉ ህይወት ማዳን የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውና የእርሻ መሬትን ከጎርፍ አደጋ ለመጠበቅ መቻሉንና ሌሎች በርካታ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አብራርተዋል።

በቀጣይም በጥናት የተለዩ የጎርፍ ተጋላጭ አካባቢዎች ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የጎርፍ አደጋ ቅነሳ ሥራዎችን በማጠናከር ማህበረሰቡን፣ የእርሻ መሬቶችንና የአካባቢውን ልማት ከጎርፍ አደጋ የመጠበቅ ሥራው እንደሚቀጥል አጽንኦት ተሰጥቶበታል።

መረጃው የውሃና አነርጂ ሚኒስቴር ነው።

"ባለፉት ሦስት ዓመታት ብዝኃነትን፤ በጋራ መልማትንና የፍትሀዊ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም፤ በዋና ዋና የማህበራዊ ልማት እና የኢኮኖሚያዊ ዕድገት ዘርፎች እንዲሁም የውስጥ አቅምን በማጎልበ...
20/08/2026

"ባለፉት ሦስት ዓመታት ብዝኃነትን፤ በጋራ መልማትንና የፍትሀዊ ተጠቃሚነት መርህን በማስቀደም፤ በዋና ዋና የማህበራዊ ልማት እና የኢኮኖሚያዊ ዕድገት ዘርፎች እንዲሁም የውስጥ አቅምን በማጎልበት በራስ አቅም በተሰሩ ውጤታማ ስራዎችና ሰው ተኮር ተግባራት፤ የህዝባችንን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ አመርቂ ውጤቶች ተገኝተዋል፡፡" አቶ ጥላሁን ከበደ ፤የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

ንጹህ ውሃ፣ሳኒቴሽንና ታዳሽ ኃይል፤ለዘላቂ ህይወት!
Clean Water,Sanitation & Renewable Energy for a Sustainable Life!

የቢሮ ህዝብ ግኑኝነት ዳይሬክቶሬት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ በዩኒሴፍ ድጋፍ የሚገነቡ የውሃ ፕሮጀክቶች የግንባታ አፈፃፀም የመስክ ምልከታ ተካሄደ።ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም፦ዲላምልከታውን የቢሮው ምክትል ኃላፊና...
19/08/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ በዩኒሴፍ ድጋፍ የሚገነቡ የውሃ ፕሮጀክቶች የግንባታ አፈፃፀም የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም፦ዲላ
ምልከታውን የቢሮው ምክትል ኃላፊና የመጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ ግንባታና ተቋማት አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ በአቶ እልጎ እንጄ የተመራ ቡድን በደቡብ ኦሞ ዞን እና ጂንካ ከተማ በመገኘት አካሂዷል ።

በምልከታው ሂደት በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የመርመርቲ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አቶ እልጎ ገልጸዋል።

ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው ይህ ፕሮጀክት የአካባቢውን ህብረተሰብ የውሃ ችግር በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም በዞኑ የዲመካ እና ካንጋቴን የጥልቅ ጉድጓድ ፕሮጀክቶች ወደ ሶላር ኃይል የመቀየር ሥራ ወደ መጠናቀቅ የተቃረበ መሆኑ ተገልጿል።

ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚፈጁት እነዚህ ፕሮጀክቶች 85% በላይ መጠናቀቃቸው ተመላክቷል።

በሌላ በኩል ከ36 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የሚገነባው የጂንካ ሆስፒታል የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ ገደብ የማጠናቀቅ የማጠናቀቅ ሂደት ላይ መሆኑም ተገልጿል።

ምክትል ቢሮ ኃላፊውን ጨምሮ የፌደራል እና የክልል የፕሮግራሙ ተጠሪዎች፣ ከዞንና ከወረዳ የተገኙ ሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በምልከታው ተገኝተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ በብሔራዊ ዋሽ ፕሮግራም ህብረተሰቡን በይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሠራ አስታወቀነሐሴ 8/2018 ዓ.ም፦ዲላበቢሮው የፕሮግራሙ ሦስተኛ ምዕራፍ የመ...
14/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ በብሔራዊ ዋሽ ፕሮግራም ህብረተሰቡን በይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሠራ አስታወቀ

ነሐሴ 8/2018 ዓ.ም፦ዲላ
በቢሮው የፕሮግራሙ ሦስተኛ ምዕራፍ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ጥናት ሰነድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተገምግሟል።

በመድረኩ የተገኙት የቢሮው ምክትል ኅላፊና የመጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ ግንባታና ተቋማት አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ አቶ እልጎ እንጄ እንደገለጹት ላለፉት ጊዜያት በዋሽ ፕሮግራም በርካታ የክልሉ ህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ሆነዋል።

ይሁን እንጅ የክልሉ ውሃ ሽፋን ከአገር አቀፍ ስታንዳርድ አንጻር ገና ብዙ መሥራትን የሚያመላክት በመሆኑ የፕሮግራሙን ዓላማ እና የህብረተሰባችንን ፍላጎት በማጣጣም እንሰራለን ብለዋል።

ይህንን ለማሳካት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ወሳኝ በመሆናቸው የጥናት ሰነዶች ከቴክኒክ፣ ከቦታው ነባራዊ ሁኔታ፣ከወጪ አዋጭነት እንድሁም ዘሌቄታዊ አገልግሎት አኳያ ሊረጋገጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የክልሉ ዋሽ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሣለኝ ዳቼ እንደገለጹት በብሔራዊ ዋሽ ፕሮግራም ሁለተኛው ምዕራፍ ባለፉት 6 ዓመታት ከ1.1 ሚሊዮን የሚበልጥ የክልሉ ህብረተሰብ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ልማት ተጠቃሚ ሆኗል።

ከዚህ ቀደም ተግባራዊ በሆኑ ምዕራፎች ፕሮግራሙ በ3 ከተማዎችና በ25 ወረዳዎች ባስገነባቸው መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ከ490 ሺህ በላይ ህዝብ ተጠቃሚ መሆኑንም አቶ ደሳለኝ ገልጸዋል።

በተጨማሪም በ120 የትምህርት እና 90 በሚደርሱ የጤና ተቋማት የሙሉ ፓኬጅ ሳኒቴሽንና ሀይጂን ፕሮጀክቶች እውን በመሆናቸው ከ620 ሺህ በላይ የክልሉ ህዝብ ተጠቅሟል ።

በቀጣይ በምጀመረው ሶስተኛ ምዕራፍ ደግሞ በክልሉ ዝቅተኛ የውሃ ሽፋን እና ከፍተኛ ችግር ያለባቸው 1መካከለኛና 2 አነስተኛ ከተማዎች፤ እንድሁም 8 ወረዳዎች ለሚቀጥሉት 10 ዓመታት የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አቅርቦት ትግበራ እንደሚካሄድባቸው አቶ ደሳለኝ ገልጸዋል።

በዚህ መነሻነት የ12 የገጠር መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እንድሁም የ2 ከተማዎች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች የጥናት ሰነድ ቀርበው ተገምግሟል።

በግምገማው የተነሱ ህብረተሰቡን በይበልጥ ተጠቃሚ የሚያደርጉ እና ሙያዊ አስተያየቶችና ሀሳቦች የፕሮጀክቶቹ ጥናት ሰነድ እንደሚያዳብሩ ተጠቁሟል።

የቢሮው የዘርፍ ኃላፊዎች፣ ከዞን ማዕከል የተወጣጡ የመምሪያ ኃላፊዎች እንድሁም ከክልል፣ ከዞኖችና ከከተማ ውሃ አገልግሎቶች የሚመለከታቸው የዘርፉ ከፍተኛ ባለሙያዎች በመድረኩ ተሳታፊዎች ናቸው።

ንጹህ ውሃ፣ሳኒቴሽንና ታዳሽ ኃይል፤ለዘላቂ ህይወት!
Clean Water,Sanitation & Renewable Energy for a Sustainable Life!

የቢሮው የህዝብ ግኑኝነት ዳይሬክቶሬት
የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026

በውሃና ኢነርጂ ቢሮ ከክልል ተቋማት ለተወጣጡ ግዥ ባለሙያዎች የቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ በሆነው በዲጂታል ድህረ-ገጽ ግዥ ሥርዓት (KPIs) ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም፦ዲላ ...
12/08/2026

በውሃና ኢነርጂ ቢሮ ከክልል ተቋማት ለተወጣጡ ግዥ ባለሙያዎች የቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ በሆነው በዲጂታል ድህረ-ገጽ ግዥ ሥርዓት (KPIs) ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም፦ዲላ
በተቋማት የግዥ ሥርዓቱን ውጤታማነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት በይበልጥ ለማሳደግ ዓላማ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ለግዥ ባለሙያዎቹ ተሰጠ።

በስልጠናው መክፈቻ ላይ በክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የግዥና ንብረት አስተዳደር ባለሥልጣን ዋና ኃላፊ ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሣዬ ተገኝተው እንደገለጹት፤ በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ሁሉም ፕሮጀክቶች የታቀደላቸውን ግብ በታቀደላቸው ጊዜ፣ ጥራትና በጀት እንዲያጠናቅቁ የግዥ ሂደቱን በቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች (KPIs) መምራትና መገምገም ወሳኝ ነው።

ኃላፊዋ አያይዘውም ስልጠናው ሠራተኞች የግዥ ሂደቱን በዘመናዊና በመረጃ ላይ በተመረኮዘ መልኩ እንዲመሩ የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር አፅንዖት ሰጥተዋል።

በዓለም ባንክ በኩል የሚመደቡ ፕሮጀክቶች ግዥ ሥርዓት በ KPI ተመዝግቦ መተገበር ግዴታ በመሆኑ ትግበራውም ልጠናከር እንደሚገባም አመላክተዋል።

በሥልጠናው የባለሙያዎችን ግንዛቤና ክህሎት የሚያሳድጉና በግዥ ዘርፍ ሊተገበሩ የሚገባቸው ዋና ዋና የKPI ቴክኒካል ጉዳዮች በተግባር ተዳስሰዋል።

በተጨማሪም የመተገበሪያ ሶፍትዌሩና የሥርዓቱ ፋይዳም በስልጠናው የተዳሰሰ ሲሆን፥ ለመንግስት ግዥ የተመደበው በጀት ያለብክነት በሥራ ላይ መዋሉን እና ከተመደበው በጀት ጋር ሲነጻጸር የሚገኘውን የወጪ ቁጠባ መጠን በመለካት የበጀት አጠቃቀም ቅልጥፍናን ማሳደግ የሚቻልበት አሰራር ተብራርቷል።

የግዥ ሂደቱ ከመንግስት የግዥ አዋጆች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች ውጪ ሳይወጣ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለውድድር ክፍት ሆኖ እንዲካሄድ የሚደረገውን ክትትል ለማቀላጠፍ እንደሚረዳም ተገልጿል።

በሌላ በኩል ሥርዓቱ አሸናፊ ተቋራጮችና አቅራቢዎች ዕቃዎችንና አገልግሎቶችን በውል ስምምነቱ መሠረት በሰዓቱ እና ተፈላጊውን የጥራት ደረጃ ጠብቀው እንዲያቀርቡ ለማድረግ መለኪያ መሆኑም ተመላክቷል።

ተቋማቱ ለዘርፉ ባለሙያዎች የተሰጠውን ሥልጠና በስራ ላይ በማዋል በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ፍጥነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻሻለ ለመሄድ የሚያስችለውን አቅም ማጎልበት እንዳለባቸውም ተጠቁሟል።

ሥልጠናው ከፌደራል ግዥ ባለስልጣን ከመጡ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን ከክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ፣ከትራንስፖርትና መንገድ ልማት፣ ከግብርና፣ ከትምህርት፣ ከጤና እና ከፋይናንስ ቢሮዎች የተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የቢሮው የህዝብ ግኑኝነት ዳይሬክቶሬት
የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026
Ticktock:
https://www.tiktok.com/.ethiopia.wa?_r=1&_t=ZS-98RVriCOrKe

በወላይታ ዞን ‎በ2018 በጀት ዓመት ከ20 በላይ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸው ተገለጸ‎ነሐሴ 3/2018 ዓ.ምዞኑ በሚያካሂደው የምክር ቤት ጉባኤ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለምክ...
09/08/2026

በወላይታ ዞን ‎በ2018 በጀት ዓመት ከ20 በላይ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸው ተገለጸ

ነሐሴ 3/2018 ዓ.ም
ዞኑ በሚያካሂደው የምክር ቤት ጉባኤ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለምክር ቤት አባላት ባቀረቡት ሪፖርት መሠረት በበጀት ዓመቱ 20 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት ጀምረዋል።

በዚህም በ2017 በጀት ዓመት የዞኑ አጠቃላይ የውሃ ሽፋን 47.34% ከነበረበት ወደ 53% ከፍ እንዲል ተደርጓል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በ2018 በጀት ዓመት የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ የሆነው ህዝብ ቁጥር 371,672 መደረሱንም ገልፀዋል።

‎ በበጀት ዓመቱ የተጠናቀቁ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እነሱም ደሚከተለው ተገልፀዋል።

እነዚህም፦
‎👉የሆብቻ ወረዳ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ150 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የሻንቶ ከተማ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት፤ በ220 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የዳ/ሶሬ ወረዳ መሬ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት፤ በ27 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የቦ/ሶሬ ወረዳ ሌጋማ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት፤ በ64 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የጉኑኖ ሐሙስ ከተማ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት፤ በ61 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ዳዳ ካሬ መጠጥ ውሃ ፕሮጀከት፤ በ2ዐ ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የአበላ አባያ ወረዳ አባያ ጫውካሬ ንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀከት፤ በ12 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የድምቱ ከተማ small scale treated መ/ው/ፕሮጀክት 4.8 ሚሊዮን ብር ተገንብቷል

‎👉የአ/አባያ ወረዳ ጥታ ሰፈራ ጣቢያ-2 መ/ው/ፕሮጀከት፤ ጠቅላላ በጀት 3.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የዱ/ፋንጎ ወረዳ ዱ/ኪንዶ ዱ/ሶሬና ፋ/ኮይሻ መ/ው/ፕ፤ ጠቅላላ በጀት 8.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የዱ/ፋንጎ ወረዳ ደንዶ ክላስተር መ/ው/ፕሮጀክት 12 ሚሊዮን ብር

‎👉የኪንዶ ድዳዬ ወረዳ ሼላ ሳዴ ቀበሌ መ/ው/ፕ ከ3 ሚሊዮን ብር

‎👉የኦፋ ወረዳ ያክማ ቀበሌ መ/ው/ፕ ከ2.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የኦፋ ወረዳ ጥዳ ማዜ ቀበሌ መ/ው/ፕ ከ3.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የቦ/ሶሬ ወረዳ ሹዬ ሆምባ ቀበሌ መ/ዉ/ፐ ከ3.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የካ/ኮይሻ ቀረዳ ዛና ቀበሌ መ/ው/ፕ ከ2.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የካ/ኮይሻ ወረዳ ላሾ ዐ1 ቀበሌ መ/ው/ፕ ከ2.5 ሚሊዮን ብር

‎👉የቦ/ሶሬ ወረዳ አድማንቾ አርፍጣ ቀበሌ ምንጭ በቦታው ከ2 ሚሊዮን ብር

‎👉የዳ/ሶሬ ወረዳ ሶሬ ቅሌና ቀበሌ ምንጭ በቦታው ከ2 ሚሊዮን ብር

‎👉የኪንዶ ድዳዬ ወረዳ ቦሳ ቦርቶ መ/ው/ፕ ከ13 ሚሊዮን ብር

‎በግንባታ ሂደት በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን በመገለጽ፥ እነዚህ ፕሮጀክቶች ተጠናቅቆ ለህዝቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ልዩ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋልም ብለዋል። ዘገባው የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው።

ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የመኖሪያ ቤትና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመረቁነሐሴ 2/2018 ዓ.ምበጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ቡርዳ ቀበሌ በናዳ ምክንያት ከመኖሪያ...
08/08/2026

ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የመኖሪያ ቤትና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመረቁ

ነሐሴ 2/2018 ዓ.ም

በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ቡርዳ ቀበሌ በናዳ ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው ለተፈናቀሉ የቀበሌው ነዋሪዎች የተገነቡ 88 የመጠለያ መኖሪያ ቤቶችና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በኬንቾ ቡርዳ ቀበሌ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በፕሮግራሙ የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ፣ የHabitat for Humanity Ethiopia ግብረ ሰናይ ድርጅት ማናጀሮች፣ የዞኑ ሥራ አስተባባሪዎችና አመራሮች፣ የገዜ ጎፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም ብርሃኑ እና የሥራ አስተባባሪያቸው እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው እነዚህ ፕሮጀክቶች በናዳ ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው ለተፈናቀሉ የቡርዳ ቀበሌ ነዋሪዎች የተገነቡ ሲሆን፣ የተረጋጋ መኖሪያና የንፁህ መጠጥ ውሃ በማቅረብ የተፈናቃዮቹን የመልሶ ማቋቋም ሂደት ለማጠናከር የሚያግዙ መሆናቸው ተገልጿል።

የመጠለያ መኖሪያ ቤቶቹና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ በHabitat for Humanity Ethiopia የተከናወኑ ሲሆን፣ ድርጅቱ በተፈናቀሉ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ያተኮረ የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ አካል መሆኑ ተመላክቷል።

በፕሮጀክቱ 88 የመጠለያ መኖሪያ ቤቶች የተገነቡ ሲሆን፣ ከንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ጋር በመደመር ከ735 በላይ የማህበረሰብ አባላት ተጠቃሚ ይሆናሉ።

የውሃ ፕሮጀክቱ ከ41.5 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ የውሃ መስመር ዝርጋታን ያካተተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ውሃ በቀላሉ እንዲያገኝ ባለ አራት ጡት የውሃ ቧንቧ ማፋሰሻ ያለው ቦኖም ተገንብቷል።

የፕሮጀክቶቹ ምረቃ በተፈናቃዮች የመኖሪያ ችግርን በመቅረፍና የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን በማሻሻል ከፕሮጀክት ምረቃ በላይ የሰዎችን ሕይወት ወደ መደበኛ ኑሮ የሚመልስ የተግባር ውጤት መሆኑን አሳይቷል።

መረጃው የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው።

Address

Dila
153

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Regional State Water and Energy Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share