Tesfatsion Daka

Tesfatsion Daka This is my official page

በሕይወታችሁ የቸኮለ ልብ እንጂ የሚዘገይ አምላክ(እግዚአብሔር) የለም። አምላካችሁ እግዚአብሔር ስለናንተ ነገር 9:00 ሰዓት ላይ ተነስቶ ምንም ዓይነት ማይክሮ ሰኮንዶች ሳይባክኑ በዚያው 9:...
01/05/2026

በሕይወታችሁ የቸኮለ ልብ እንጂ የሚዘገይ አምላክ(እግዚአብሔር) የለም። አምላካችሁ እግዚአብሔር ስለናንተ ነገር 9:00 ሰዓት ላይ ተነስቶ ምንም ዓይነት ማይክሮ ሰኮንዶች ሳይባክኑ በዚያው 9:00 ሰዓት ይደርሳል።

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!                                   ምልክታችን የስንዴ ነዶ ነው፤                                       ብልጽግናን ይ...
30/04/2026

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር! ምልክታችን የስንዴ ነዶ ነው፤ ብልጽግናን ይምረጡ!!!

28/04/2026
ይነበብ!!የቴዲ አፍሮ ሥራዎች ከወንጌል እውነት እና ከመጥመቁ ዮሐንስ ተልዕኮ አንጻር ሲመዘን፣ወንጌል የሚለው ቃል "ኢቫንጄሊዮን" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም የምስራች ማለት ነ...
27/04/2026

ይነበብ!!
የቴዲ አፍሮ ሥራዎች ከወንጌል እውነት እና ከመጥመቁ ዮሐንስ ተልዕኮ አንጻር ሲመዘን፣
ወንጌል የሚለው ቃል "ኢቫንጄሊዮን" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም የምስራች ማለት ነው። ወንጌል የሰው ልጅ በኃጢአቱ ምክንያት ከእግዚአብሔር ተለይቶ ሳለ፣ እግዚአብሔር በልጁ በኩል ሰውን ለማዳን ያደረገው መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት ነው። ይኸውም ሙሉ በሙሉ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ስለ እርሱ ሰው መሆን፣ ስለ መከራው፣ ስለ ሞቱ፣ ስለ ትንሳኤውና ዳግም ስለመምጣቱ ነው። ጠቅለል ባለ መልኩ ስንመለከት የወንጌል ማዕከላዊ ሃሳብ መተካት/ምትክነት (Substitution) ነው። ይህም እኛ ልንቀበለው የሚገባንን ሞትና ቅጣት ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተቀብሎ፣ የእርሱን ጽድቅና የዘላለም ሕይወት ለእኛ መስጠቱ የወንጌል እምብርት ነው።
"በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።" (ዮሐንስ 3:16)
የመዝሙርና ዘፈን አንድነት ሁለቱም ሙዚቃዊ መዋቅር ያላቸው መሆኑ ሲሆን፣ ሁለቱም የሰውን ስሜት የመንካት፣ መልእክትን የማስተላለፍና ባህልን የመግለጽ አቅም ያላቸው የጥበብ ውጤቶች ናቸው። ልዩነቱ ግን ሰማይ ከምድር እንደሚርቅ የተራራቁ ናቸው፤ የመዝሙር ምንጩ የእግዚአብሔር ቃል ሲሆን ግቡ ደግሞ ለእግዚአብሔር ክብርና ለአማኞች መታነጽ ነው። ዘፈን ግን ምንጩ ሰብአዊ ስሜት፣ ማህበራዊ ክስተት ወይም ፍልስፍና ሲሆን ግቡም ምድራዊ መዝናኛ ነው። ዘፈን ዓለማዊ እሴቶችን ሲያራምድ፣ መዝሙር ግን መለኮታዊ እውነትን ይሸከማል።
ከላይ ባየናቸው ሁለቱ የወንጌል ምንነት እና ከመዝሙርና ዘፈን አንድነትና ልዩነት ትርጓሜ ተነስተን ዶ/ር ደረጀ ከበደ በቴዲ አፍሮ በኢቶሪካ የዘፈን አልበም የሰጠው የግል ምልከታ ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ እና ራሱ ከዘመራቸው መዝሙሮች አንጻር ያለውን መጣረስ ለማሳየት እና ሌሎች የዶ/ር ደረጀን ምልከታ በቅንነት ተመልክተው ወደ ስህተት እንዳይሄዱ በገባኝ እውነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጭብጡን መሠረት በማድረግ ለመጠቆም ነው፡፡
መጥመቁ ዮሐንስ የክርስቶስን መምጣት ለማብሰር "የእግዚአብሔርን በግ" እያመለከተ መንገድ የጠረገ ነቢይ ነው። ዶ/ር ደረጀ ቴዲ አፍሮን ከዚህ ታላቅ ነቢይ ጋር ማነጻጸራቸው፣ የኪነ-ጥበብን ማህበራዊ ፋይዳ ከወንጌል ተልዕኮ ጋር የመቀላቀል አዝማሚያ የሚታይበት ከመጽሐፍ ቅዱስ ትክክለኛ/ልከኛ አስተምህሮ ጋር የሚጣረዝ ምልከታ ነው፡፡ ዘፈን የሞራልና የፍትህ እሴቶችን ቢይዝም፣ የደህንነት ወንጌል ግን ሊሆኑ አይችልም። ኪነ-ጥበብ የሕሊና ድምፅ ሲሆን፣ ወንጌል ግን የመንፈስ ሕይወት ነው። ወንጌል ትኩረቱ የሰው ልጅ ከኃጢአት ስለማዳንና ስለ ዘላለም ሕይወት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ንግግር እርሳቸው በዝማሬያቸው ካከበሩትና ከፍ ካደረጉት የክርስቶስ ብቸኛ አዳኝነትና የወንጌል ልዩ ባሕርይ ጋር የሚጋጭ ሃሳብ ነው፡፡
እጅግ በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ ሃሳብ ተቃርኖ የሚያነሳቸውን ግለ-ምልከታ ተቀባይነት ለማረጋገጥ በሚል "ዘመርኩ እንጂ አልኖርኩበትም" ማለታቸው ነው፡፡ ይህን ሃሳብ በግል ማንጸባረቁ ችግር ባይኖረውም ለፖለቲካ ፍጆታ በሚል በዚህ መልኩ ማቅረቡ ግን ግብዝነት ነው፤ ምክንያቱም እርሳቸው በዝማሬዎቻቸው የጸጋውን ደጋፊነት ሲመሰክሩ ቆይተው፣ ዛሬ "አልኖርኩበትም" ማለታቸው አድማጩን ግራ የሚያጋባ ክስተት ከመሆን ባለፈ የሚያስገኘውን አዎንታዊ ውጤት በግሌ ምንም አልታየኝም፤ አይታየኝምም፡፡ ይህ ንግግር አገልጋይ እንደ ሰው ሊደክም እንደሚችል ቢጠቁምም፣ ወንጌል ግን ደካማውን ሰው ቀይሮ ለክብር እንደሚያበቃው የሚገልጸውን የክርስትና መሠረታዊ እውነት ዝቅ የሚያደርግ ነው፡፡ ለዚህም ነው ትክክለኛ/ልከኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ መሠረት ያደረገ አይደለም ያልኩት፡፡
ኪነ-ጥበብ (ዘፈን) ሰብአዊ ስሜትንና ማህበራዊ ንቃተ-ህሊናን ለማነቃቃት ትልቅ መሣሪያ ቢሆንም፣ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር እኩል "እውነትን እየሰበከ ነው" ተብሎ ሊወሰድ አይችልም፤ አይሆንምም፡፡ ዶ/ር ደረጀ በዝማሬዎቻቸው ሲያስተምሩ እንደነበረው፣ የወንጌል ሰበካ ምንጩም ግቡም ክርስቶስ ብቻ ነው። ታዲያ ዛሬ ላይ ቴዲ አፍሮን እንደ ወንጌል ሰባኪ መቁጠር፣ ዓለማዊ ጥበብንና መለኮታዊ መገለጥን በአንድ ሚዛን መመዘን በየትኛው መንገድ ትክክል ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባ አይደልም፡፡ ይህም በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ውስጥ የ"ቅዱስ" እና የ"ዓለማዊ" መለያ መስመር እንዲደበዝዝ የሚያደርግ ክፉ ዘር ነው፡፡
ባጠቃላይ ወንጌል ሰውን ወደ ክርስቶስ እንጂ ወደ ሰው አድናቆት አይመራም። እርሳቸውም ቢሆኑ ባለፉት ዓመታት በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ አማኞች የነፍስ ምግብ/ስንቅ የሆኑ ዝማሬዎችን ያበረከቱት/የለገሱን፣ በራሳቸው ብቃት ሳይሆን በክርስቶስ ወንጌል ኃይል እንደነበረ ማስታወስ የተሳናቸው ይመስላል፤ ዛሬም ቢሆን እውነተኛው "ድምፅ" የሰው ልጅ ጽድቅ ሳይሆን የእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን መመስከር፣ ለራሳቸውም ሆነ ለትውልዱ የሚበጅ እውነት ወንጌልና ወንጌል ብቻ መሆኑን ተገንዘዝቦ ወደ ቀደመው እውነት እንዲመለሱ ምክሬም፣ ምኞቴም፣ ጸሎቴም ነው፡፡
ወንጌል ያሸንፋል!!
መልካም ቀን!!

ዳግመ ትንሣኤ የደስታ መድገሚያ፣ የፍቅር ማደሻ፣ ብርሃነ ትንሣኤው በልባችን የሚጸናበት፣ በዓሉ የሰላም ብቻ ሳይሆን፣ አዳዲስ ስኬቶች በሕይወታችን የሚበቅሉበት ዳግመ ትንሣኤ ይሁንልን።
19/04/2026

ዳግመ ትንሣኤ የደስታ መድገሚያ፣ የፍቅር ማደሻ፣ ብርሃነ ትንሣኤው በልባችን የሚጸናበት፣ በዓሉ የሰላም ብቻ ሳይሆን፣ አዳዲስ ስኬቶች በሕይወታችን የሚበቅሉበት ዳግመ ትንሣኤ ይሁንልን።

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ! የትንሣኤው ብርሃን ቤታችሁን በደስታ፣ ልባችሁን በፍቅር ይሙላው። መልካም በዓል!!!!!
12/04/2026

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ! የትንሣኤው ብርሃን ቤታችሁን በደስታ፣ ልባችሁን በፍቅር ይሙላው። መልካም በዓል!!!!!

መስቀሉ የፍቅር መግለጫ ነው! ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳም ልጆች ሁሉ ያለውን ጥልቅ ፍቅር በመስቀል ላይ በከፈለው መስዋዕትነት የገለጠበት ታላቅ ቀን ነው። ይህ ዕለት የሰው ...
10/04/2026

መስቀሉ የፍቅር መግለጫ ነው!
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳም ልጆች ሁሉ ያለውን ጥልቅ ፍቅር በመስቀል ላይ በከፈለው መስዋዕትነት የገለጠበት ታላቅ ቀን ነው። ይህ ዕለት የሰው ልጅ ከኃጢአት ቀንበር ያረፈበት፣ ሞት በሕይወት የተሸነፈበት፣ የመዳናችን፣ የነፃነታችን እና የሰላማችን መሠረት ነው። ዛሬ በመስቀል ላይ የተከፈለው ዋጋ ለእኛ የዘላለም ተስፋ ሆኖናል።
"አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" ያለው ጌታ፣ ዛሬም ለእኛ የይቅርታንና የትህትናን መንገድ ያሳየናል። በዚህ ቅዱስ ዕለት እኛም በልባችን ያለውን ቂም በይቅርታ፣ ጥላቻን በፍቅር የምንቀይርበት ይሁንልን።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የሰላም እና የጸሎት ቀን ይሁንልን፡፡ ቸሩ አምላክ በመስቀሉ ላይ ያፈሰሰው ደሙ ለሀገራችን ሰላምን፣ ለሕዝባችን ፍቅርን ያብዛልን፡፡
መልካም ስቅለተ-በዓል ይሁንልን!

"ማንኛውም ሰው በሐሰት የፈለገውን ሊናገርብኝና ሊሠራብኝ ይችላል።  ሌላ ሰው እንድሆን ሊያደርግ ግን አይችልም።"  አቤ ጉበኛ
22/03/2026

"ማንኛውም ሰው በሐሰት የፈለገውን ሊናገርብኝና ሊሠራብኝ ይችላል። ሌላ ሰው እንድሆን ሊያደርግ ግን አይችልም።" አቤ ጉበኛ

ለመላው እሰልምና እምነት ተከታዮችእንኳን ለ1447ኛዉ ለዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!!ዒድ ሙባረክ
20/03/2026

ለመላው እሰልምና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለ1447ኛዉ ለዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!!

ዒድ ሙባረክ

በጋሞ ዞን ደጋማ አካባቢዎች በደረሰው የመሬት ናዳና የጎርፍ አደጋ የ30 ወገኖቻችን ህይወት በማለፉ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ፥ ለሟቾች የዘላለም እረፍት፣ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ...
10/03/2026

በጋሞ ዞን ደጋማ አካባቢዎች በደረሰው የመሬት ናዳና የጎርፍ አደጋ የ30 ወገኖቻችን ህይወት በማለፉ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ፥ ለሟቾች የዘላለም እረፍት፣ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለሁ።

Address

Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tesfatsion Daka posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share