የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office "የበለጸገች ጊዶሌን የመገንባት ራዕይ ሰንቀን እንተጋለን!! - We strive to build a prosperous Gidole"

የጊዶሌ ከተማ አስተደደር ትምህርት ጽ/ቤት "ትምህርት ያለ ስስት "በሚል  መሪ ቃል የትምህርት ንቅናቄ መድረክ አካሄዴ ፡፡ሐምሌ 21/2018ዓ/ም (ጊዶሌ ከተማ አስተዳደር መ/ኮ) መድረኩ በጊ...
28/07/2026

የጊዶሌ ከተማ አስተደደር ትምህርት ጽ/ቤት "ትምህርት ያለ ስስት "በሚል መሪ ቃል የትምህርት ንቅናቄ መድረክ አካሄዴ ፡፡

ሐምሌ 21/2018ዓ/ም (ጊዶሌ ከተማ አስተዳደር መ/ኮ) መድረኩ በጊዶሌ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ት/ቤቶች ርዕሳኔ መምህራን ፣ሱፔር ቫይዘሮች ፣የት/ቤቶች ወመህ አባላት የ3ቱ ቀበሌ ሊቃነመናብርት ፣ ሥራ አስኪያጆችና ለሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል ፡፡

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ም/ከኒቲባና የት/ት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ዲማ በመክፈቻ ንግግራቸው ለትምህርት ቤቶች የክረምት ወራት ተግባራት በተሰካ ሁነታ ማከናወን ቀጣዩን የትምህርት ጊዜ ምቹ እንዲሆን ከማስቻል ባለፈ ተማሪዎች የሚገባቸውን ዕውቀት ማግኘት እንዲችሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው በዚህም በመድረኩ የተሳተፉ አካላት በተግባር ስራው ላይ ግንባር ቀደም ሆነው ለሎችን በማስተባበር በቅንጂት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል ፡፡

የ2018ዓ/ም ክረምት ወራት ተግባር ዕቅድ አፈጻጸም ሰነድ በጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ት/ጽ/ቤት ት/ቤት/መሻ/ፕ/ቪዥን ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ በሆኑት በአቶ ተካልኝ መሰለ በዝርዝር ቀርቧል፡፡

የክረምት ተግባራት ማህበረሰቡን በማስተባበርና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ሃብት በማሰባሰብ የትምህርት ተቋማት ዝግጁነት በማረጋገጥ ትምህርት ለትውልድ መርህ እንዲሳካ የትምህርት ግብአቶችን በሟሟላት ከዚህ ቀደም ያልተሳኩ የትምህርት ግቦች በላቀ ደረጃ ለመፈፀም በ2019 ውጤታማ የመማር ማስተማር ተግባራትን ለማከናወን የክረምት ተግባራት በትኩረት ማከናወን ውጤታማ ለመሆን እንደሚረዳ ተገልጿል ፡፡

በንቅናቄ መድረኩ በቀረበው ዕቅድ አተገባበር በቀጣይ ሊያጋጥሙ በሚችሉ ጉዳዮች ከተሳታፊዎች ሃሳብ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል ፡፡

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መኩርያ ሞላ ትምህርት ቤቶቻችን ካለባቸው በርካታ ጉድለቶች አሁን ላይ ላለው የትምህርት ስርዓት ጋር አብሮ ለመሄድ ፈታኝ የሆኑ ጉዳዮች እንዳሉ በመግለፅ ይህን ሁነታ ለመቀየር ሁሉም በየዘርፉ በባለቤትነት ሊረባረብ እንደሚገባ ገልፀዋል ፡፡

በመጨረሻም በተነሱ ሃሳብ አስተያየቶች ላይ ምላሽና ማብራርያ በመስጠት የትምህርት ስርዓቱ ውጤታማ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል ፡፡

#የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር መ/ኮ

የጋራ ሀገር የጋራ መፍትሔ - የኢትዮጵያውያን ድምጽ እኩል የሚሰማበት ምክክርሐምሌ 21/2018 ሀገራት የተለያየ የአኗኗር ሁኔታ፣ ማንነትና ባህል ባላቸው ግለሰቦች የሚገነቡ የማህበረሰብ ውቅር...
28/07/2026

የጋራ ሀገር የጋራ መፍትሔ - የኢትዮጵያውያን ድምጽ እኩል የሚሰማበት ምክክር

ሐምሌ 21/2018

ሀገራት የተለያየ የአኗኗር ሁኔታ፣ ማንነትና ባህል ባላቸው ግለሰቦች የሚገነቡ የማህበረሰብ ውቅር ውጤት ናቸው፡፡

በዚህም ምክንያት በአንድ ጉዳይ ላይ የተለያየ እይታ ቢኖራቸው ወይም ጥያቄዎቻቸውም የተለያዩ መሆናቸው የሚጠበቅ ጉዳይ ነው፡፡

እናም የአንዱ ችግር ለሌላው ላይታየው ይችላል፤ የሌላኛውን ጥያቄ አግባብነትና መሰረታዊነት ሁሉም በእኩል ላይገነዘበው ይችላል፡፡

እነዚህ ልዩነቶች ተፈጥሯዊ ቢሆኑም በሀገር ጉዳይ የጋራ መግባባትን መፍጠር ወሳኝ በመሆኑ ኢትዮጵያ ለዓመታት ሲንከባለሉ የመጡና ለግጭት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡

በዚህም ገለልተኛ ኮሚሽን በማቋቋም አካታችና አሳታፊ በሆነ መንገድ ባለፉት ዓመታት የሁሉንም ጥያቄና አጀንዳ የማሰባሰብ ስራዎች ተከናውነዋል።

እስከ ወረዳ ድረስ በመውረድ አጀንዳ ማሰብሰብ፣ የአጀንዳ ልየታ እና የተሳታፊዎች ልየታ የተከናወነ ሲሆን፥ በዚህ ሂደት በተለያዩ ምክንያቶች መድረስ ባልተቻለባቸው አካባቢዎች የሕብረተሰብ ተወካዮችን በአዲስ አበባ በማወያየት አጀንዳ ማሰባሰ ተችሏል፡፡

ሂደቱ በሀገሪቱ በሁሉም የስራ መስኮች የሚገኙ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ተወካዮች እንዲሁም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአካል እንዲሁም በበይነመረብ አማካኝነት ያለምንም ልዩነት እንዲሳተፉና አጀንዳዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ተደርጓል፡፡

በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ያሉ ኢትዮጵውያን ካሉበት ቦታ ሀሳብ መስጠት እንዲችሉ ኮሚሽኑ የዲጂታል አማራጭ አዘጋጅቷል፡፡

ከዚህም ባለፈ ከተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪክ ማኅበራት፣ ከሃይማኖት ተቋማትና ከምሁራን በርካታ አጀንዳዎች ተሰብስበዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን ባቀረቧቸው አጀንዳዎች ላይ ለሀገር የሚበጅ መግባባት ላይ ለመድረስ በአዲስ አበባ ተሰባስበው መምከር ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡

በዚህ ዋናው የምክክር ምዕራፍ የተበላለጠ እድል የሚኖረው አካል አይኖርም፤ ይልቁንም ሁሉም እኩል የመወሰን እድል ይሰጠዋል፡፡

ምክክሩ የተወሰኑ ሰዎችን ፍላጎት ለማስፈፀም ሳይሆን ትክክለኛ የህዝብ ችግሮችን ለመረዳት የሚያስችል ሲሆን፥ ተሳታፊዎቹ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የመጡ በመሆናቸው አንዱ የሌላውን ቁስል፣ ህመምና ስጋት እንዲረዳ እድል ይፈጥራል፡፡

ሀገር የእነዚህ ሁሉ ውቅር በመሆኗ የእያንዳንዱ የማህበረሰብ ክፍል ጥያቄ ልዩነት በሌለው መልኩ ሲስተናገድ፣ ለውይይት ሲቀርብና ሲፈታ የሀገር ባለቤትነትን ስሜት ለማጎልበትና እርስ በርስ የመግባባትና የመተማመን መንፈስ ይጠናከራል፡፡

ከዚህም በላይ የማህበረሰብን ችግር በመረዳት በተደረጉ የውይይት መድረኮች የሚደረሱ የጋራ ውሳኔዎች በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት የሚኖራቸው በመሆኑ ለዘላቂ ሰላምና ሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ ናቸው፡፡

04/01/2026

# የመጨረሻ ማስታወቂያ #
!!አስቸኳይ ማስታወቂያ!!

ለጊዶሌ ነባር የከተማ ቦታ ጣሪያና ግድግዳ ግብር ከፋዮች ÷
ከተማ ሊዝ ቦታ ተጠቃሚዎችና ግብር ከፋዮች እንዲሁም ማስፋፊያ አከባቢ መሬት ያላቸው በሙሉ:-

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ነባር የጣርያና ግድግዳ ግብር የ2018ዓ. ም ግብር ያልከፈላችሁ ÷
ከዚህ ቀደም በተለያዬ ዙር የሊዝ ቦታ በጨረታ ተወዳድራችሁ በማሸነፍ የሊዝ ቦታ ውል የገባችሁና ተደጋጋሚ ጥሪ የቀረበላችሁ የ2018 ዓመታዊ ጨምሮ ውዝፍ የግብር ክፍያ ግዴታቸሁን ያልተወጣችሁ መኖራችሁ ይታወቃል።

በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም በከተማው ማስፋፊያ አከባቢዎች ሳይፈቀድ የተያዙ ቦታዎችና ግንባታዎችን ስርዓት ለማስያዝ፣ ለመቆጣጠርና ለመከላከል በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ቦታ ወስዳችሁ እስከ አሁን ድረስ ቅጣትና የሊዝ ቅድመ ክፍያ ያልፈፀማችሁ እንዲሁም የሊዝ ቅድመ ክፍያ ፈፅማችሁ
የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ያልወሰዳችሁ ከሰኞ ታህሳስ 27/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 30/2018 ዓ.ም ብቻ የማዘጋጃ ቤታዊ ክፍያችሁን እንድትፈፅሙ ለመጨረሻ ጊዜ ለማሳወቅ ይወዳል።

ሆኖም በተጠቀሰው ጊዜ አመታዊና ውዝፍ የሊዝ ቦታ ክፍያን ያለፈፀሙ እና ክፍያ ፈፅመው ካርታ ያልወሰዱ አካላት አስተዳደሩ በተሰጠው ስልጣንና ህግና ደንብ በሚፈቀድለት መሠረት ይዞታውን ወደ መንግሥት የመሬት ባንክ ተመላሽ እንደሚደረግ በጥብቅ ያሳስባል።

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት

 #‎ዜና ሹመት‎‎የቀድሞ የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ  የጋርዱላ ዞን ከተማና መሠረተ-ልማት መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።‎‎በዛሬው የምክር ቤት ውሎ የጋርዱላ ዞን ዋና አ...
01/12/2025

#‎ዜና ሹመት

‎የቀድሞ የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ የጋርዱላ ዞን ከተማና መሠረተ-ልማት መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

‎በዛሬው የምክር ቤት ውሎ የጋርዱላ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ግንኙነት ኪታሞ የቀድሞ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ ካላቸው እምቅ አቅምና ልምድ አንጻር እያደገ የመጣውን የከተመነት ምጣኔ በመምራት በጋርዱላ ዞን ሌሎች ከተሞችን ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሳሉ። የከተማና መሠረተ-ልማት ሥራዎችን ባላቸው ከፍተኛ ልምድ ይመራሉ በማለት ወደ ዞን በዕድገት የከተማና መሠረተ-ልማት መምሪያ ኃላፊ በመሆን እንዳደጉ ገልጸው የአዲሱን ከንቲባ ሹመት አቅርበዋል።

‎የጊዶሌ ከተማ ህዝብ ምክር ቤትም ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ በወጣትነታቸው ትልቅ ሸክም በመሸከም ውጤታማ ሥራ በመሥራታቸው በተለይም አከባቢው ከነበረበት የጸጥታ ሁኔታ ወጥቶ ወደ ልማት እንዲሸጋገር፤ ህዝባዊ አንድነት እንዲፈጠር፤ በከተማው ከፍተኛ የልማት መነቃቃት እንዲፈጠር፤ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ሥራዎችን በመምራት ላሳዩት የላቀ ትጋት አመስግኗቸው መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው የምክር ቤት አባላት ተመኝተውላቸዋል።

‎ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖም በቀጣይ ከተማውን በሚችሉት አቅም እንደሚደግፉ ቃል ገብተው በቆይታቸው ከህዝብ ምክር ቤቱ፣ ከከተማው ህዝብ፣ ከሐይማኖት አባቶችና ከሀገር ሽማግሌዎች ለተደረገላቸው አበረታች ድጋፍ አመስግነዋል።

‎የጊዶሌ ከተማ መንግስት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎትም ለቀድሞ ከንቲባችን መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተናል።

 #‎ዜና ሹመት‎የተከበሩ አቶ አሸናፊ ታዬ የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል::
01/12/2025

#‎ዜና ሹመት

‎የተከበሩ አቶ አሸናፊ ታዬ የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል::

Address

Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share