03/07/2026
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር ዜጎችን አሰልጥኖ በማብቃት ወደ ካናዳ መላክ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ፡፡
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል፣ በኢትዮጵያ የካናዳ አምባሳደር ክቡር ኒኮላስ ሪቻርድሰን እና የፊቸር ፊት ኢንተርናሽናል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አብይ ራይሞንድ ተገኝተዋል።
ክብርት ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በወቅቱ እንደገለጹት ይህ ስምምነት ወጣቶች በክህሎት በቅተው በስነ-ምግባር ታንጸው ውጤታማ የሚያደርጋቸውን የሥራ ስምሪት ማገኝት የሚያስችላቸው ነው፡፡
ሚኒስቴሩ ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ለመስጠት ለመጀመሪያ ግዜ በህጋዊ መንግድ የተፈራረመው ከዚህ ድርጅት ጋር መሆኑን ገልጸው ምዝገባም ሆነ ስምሪት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ የሚደረገው በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በለማው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት(E-Lmis) አማካኝነት ብቻ ነው ብለዋል፡፡
አምባሳደር ክቡር ኒኮላስ ሪቻርድሰን በበኩላቸው፤ ስምምነቱ ካናዳ ከአፍሪካ አገራት ጋር የጀመረችው አዲስ ስትራቴጂ አካል መሆኑን ጠቅሰው በካናዳ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን (ዳያስፖራ) ለሁለቱ አገራት ግንኙነት መጠከር ያላቸውን ሚና አድንቀዋል።
የፊቸር ፊት ኢንተርናሽናል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አብይ ራይሞንድ፤ ዓላማችን ዜጎችን ካናዳ መላክ ብቻ አይደለም ዜጎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፈላጊና ብቁ እንዲሆኑ ማድረግ ዋና ዓላማው ነው ብለዋል፡፡
ፕሮሰሱን ለመጀመር የሚያስፈልጉ መስፈርት
- መታወቂያ ወይም የታደሰ ፓስፖርት
- በሙያ ሰርተፊኬት ወይም የትምህርት ማስረጃ
- ስልክ ቁጥር እና ኢሜል
- ፎቶግራፍ
ለመመዝገብ በዚህ ይላኩልን https://t.me/
ስምምነቱ የዜጎችን መብትና ደህንነት ባከበረ መልኩ ሕጋዊነት ለመዘርጋት ገልጸዋል።