Dire dawa City

Dire dawa City voice of truth 🎤
follow me pages

28/07/2026
28/07/2026
ሣምንታዊ መልዕክት!የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት የሕዝብ አገልጋይነታቸውን በተጨባጭ ውጤት ማረጋገጥ አለባቸው።የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይ...
27/07/2026

ሣምንታዊ መልዕክት!

የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት የሕዝብ አገልጋይነታቸውን በተጨባጭ ውጤት ማረጋገጥ አለባቸው።

የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ከሀምሌ 13 እስከ 15/2018 ዓ.ም ተከታታይ ቀናት በስፋት ተካሂዷል። በዚህ መድረክ የአፈጻጸም ውጤቶችን በጥልቀት ተገምግሟል፤ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በኑሮ ውድነት ቅነሳና ገበያ ማረጋጋት ዙሪያ በንቅናቄ የተከናወኑ አበይት ተግባራት ውይይት ተደርጎባቸዋል፤ በቀጣይም የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የትኩረት አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል።

2018 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ፣ ነፃና ተዓማኒ የሆነውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ያካሄደችበት ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና ይህ ታሪካዊ ስኬት በዋናነት በመምራት አንፀባራቂ ድል ያስመዘገበ ሲሆን በመራጩ ህዝብ ዘንድ ባገኘው ቅቡልነትም ሀገርንና ህዝብን ለቀጣይ 5 ዓመታት የመምራት እድል አግኝቷል።

2019 በጀት ዓመት ደግሞ መራጩ ህዝብ የሰጠውን ታሪካዊ ኃላፊነት መወጣት የምንጀምርበት፤ ህዝቡ በተለያዩ ጊዜያት የሚያነሳውን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና ሌሎች ጥያቄዎችን ለመፍታት በትጋት የምንሰራበት እንዲሁም ፓርቲያችን የጀመራቸውን የልማት ኢኒሼቲቮች ስኬት በይበልጥ የምናረጋግጥበትና የዜጎችን ተጠቃሚነት የምናረጋግጥበት ነው። ለዚህ ስኬት ደግሞ የላቀ የአመራርና አባላት ቁርጠኝነት፤ የህዝብ የነቃ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል።

በ2018 በጀት ዓመት በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በገበያ ማረጋጋትና በኑሮ ውድነት ቅነሳ ዙሪያ የተከናወኑ ስራዎች የፓርቲያችን አቅጣጫ ትክክለኛ መሆኑን ያረጋገጡ ናቸው። በሁሉም ክልሎች በተፈጠሩ የስራ ዕድሎች፣ በምርት አቅርቦት መጨመር፣ በገበያ ማረጋጋትና በሕዝቡ የኑሮ ሁኔታ ላይ የተመዘገቡ መሻሻሎች የፓርቲያችን የሕዝብ ተጠቃሚነትን ያማከለ ፖለቲካ ውጤቶች ናቸው።

ይሁን እንጂ የተገኙት ውጤቶች የጉዟችን መጨረሻ ሳይሆኑ የቀጣይ ከፍተኛ ስኬት መነሻዎች ናቸው። ከሀገራችን አቅምና ከሕዝባችን ፍላጎት አንጻር ገና ብዙ ሊሰራ የሚገባ ስራ አለ። በመሆኑም በየደረጃው ያለው አመራር የሕዝብን ችግር ዋና የስራ አጀንዳው በማድረግ የተጀመሩ ለውጦችን ወደ ከፍተኛ ውጤት ማሸጋገር አለበት።

የስራ ዕድል ፈጠራና የኑሮ ውድነት ቅነሳ የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ዘርፍ ብቻ ኃላፊነት አይደሉም። እስከ ቀበሌ ድረስ በሁሉም የፓርቲ አደረጃጀቶች፣ በመንግሥት ተቋማትና በሕዝቡ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ሲኖር ብቻ ዘላቂ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል።

በቀጣይ የእያንዳንዱን አካባቢ እምቅ አቅም በአግባቡ በመጠቀም፣ የሕዝብ ተሳትፎንና ባለቤትነትን በማጠናከር፣ ከአሰራር፣ ከአመለካከትና ከአስተሳሰብ ጋር የተያያዙ ማነቆዎችን በመፍታት የብልፅግናን ጉዞ ወደ ከፍተኛ ደረጃ ማሸጋገር አለብን።

በተለይም የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት የሕዝብ አገልጋይነታቸውን በተጨባጭ ውጤት ማረጋገጥ አለባቸው። ሕዝባችንም በልማት ስራዎች የጀመረውን ንቁ ተሳትፎና ባለቤትነት በቀጣይነት በማጠናከር የሀገራችንን የብልፅግና ጉዞ የበለጠ እንዲፋጠን የበኩሉን ሚና መወጣት ይጠበቅበታል።

በ2019 በጀት ዓመት የተቀመጡትን ዕቅዶች ከግብ ለማድረስ በአንድነት፣ በቅንጅት፣ በተጠያቂነትና በውጤት ተኮር አሰራር መስራት ይገባል። የሕዝባችንን ተስፋ ወደ ተጨባጭ ውጤት፣ የሀገራችንን አቅም ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና ለመቀየር ሁላችንም በላቀ ቁርጠኝነት ልንረባረብ ይገባል።

ብልፅግና ፓርቲ
ሀምሌ 20/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

Dire dawa City ✍️

የደመወዝ ማሻሻያ እና የፍትሐዊ ግብር ጥያቄ!​📢 ለመላው የመንግሥት ሠራተኞች እና ዜጎች የተደረሰ የድምፅ ማሰባሰቢያ ጥሪ!ለሠራተኛው ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ እፎይታ የሚሰጥ፡ የደመወዝ ማሻሻያ እ...
26/07/2026

የደመወዝ ማሻሻያ እና የፍትሐዊ ግብር ጥያቄ!​📢 ለመላው የመንግሥት ሠራተኞች እና ዜጎች የተደረሰ የድምፅ ማሰባሰቢያ ጥሪ!

ለሠራተኛው ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ እፎይታ የሚሰጥ፡ የደመወዝ ማሻሻያ እና የፍትሐዊ ግብር ጥያቄ!

​አሁን ላይ የመንግሥት ሠራተኛው የሚከፈለው ወርሃዊ ደመወዝ ከወቅታዊው የገበያ ዋጋ እና ከኑሮ ውድነቱ ጋር ፈጽሞ ሊቀራረብ አልቻለም። ያለውን ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ በመጀመሪያ የሠራተኛው ደመወዝ ከወቅቱ የኑሮ ውድነት ጋር የሚመጣጠን ማሻሻያ ሊደረግለት ይገባል!

​ከዚህም በተጨማሪ የወቅቱን የገበያ ሁኔታ ያገናዘበ የሚከተለው የፍትሐዊ ግብር ስሌት ቢተገበር ለሠራተኛው ትልቅ እፎይታ ይሆን ነበር፦
​🔹 5% 👉 በዝቅተኛ ደመወዝ (ከ 10,000 - 20,000 ብር)
🔹 10% 👉 በመካከለኛ ደመወዝ (ከ 20,001 - 35,000 ብር)
🔹 15% 👉 በከፍተኛ ደመወዝ (ከ 35,001 - 55,000 ብር)
🔹 20% 👉 በጣም ከፍተኛ ደመወዝ (ከ 55,001 - 80,000 ብር)
🔹 30% 👉 እጅግ በጣም ከፍተኛ ደመወዝ (ከ 80,001 ብር በላይ)

​💡 ይህ ጥያቄ ለምን አስፈለገ?
አሁን ባለው የስራ ግብር ተመን ዝቅተኛ ደመወዝ የሚያገኘው ሠራተኛ ላይ የሚጣለው ግብር እና አጠቃላይ የኑሮ ጫና ተመጣጣኝ አይደለም። ደመወዝ ተስተካክሎ፣ ግብር በዚህ መልኩ በፍትሐዊነት ቢሰላ፦

​1️⃣ የሠራተኛውን የመግዛት አቅም ያጎለብታል፣
2️⃣ በስራ ላይ ያለውን ተነሳሽነት ይጨምራል፣
3️⃣ የቤተሰብን መሠረታዊ ፍላጎት ለማሟላት ያግዛል።

​ይህ ሃሳብ ፍትሐዊ እና ወቅቱን ያገናዘበ ነው ብለው የሚያምኑ ከሆነ ሼር (Share) በማድረግ ለሠራተኛው ድምፅ እንሁን!!

​ #የደመወዝማሻሻያ #ፍትሐዊግብር #የመንግሥትሠራተኛ #ኢትዮጵያ

📰 ለታማኝ መረጃ እና ለነገ ተስፋ!

ተጨማሪ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የፌስቡክ ገጻችንን Follow,Like እና Share ያድርጉ!

Dire dawa City ✍️

22/07/2026
19/07/2026
05/07/2026

በባልና ሚስት መካከል መባል የሌለባቸው ዋና ዋና ነገሮች
======================================

በትዳር ውስጥ ጤናማ ግንኙነት እንዲኖር የቃላት አጠቃቀም ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። በንዴትም ሆነ ባለማወቅ በባልና ሚስት መካከል መነገር የሌለባቸው ጎጂ ቃላት እና ሀሳቦች የሚከተሉት ናቸው፦

🙏1. የፍቺ ዛቻ ማቅረብ

"ከዚህ በኋላ አብረን መቀጠል አንችልም" ወይም "እንፋታ" የሚሉ ቃላት።
ጉዳቱ፦ በትዳሩ ላይ ያለውን የመተማመን ስሜት እና ደህንነት ያጠፋል። ምንም እንኳን በንዴት ቢነገርም፣ የትዳር አጋርን ሁልጊዜ በስጋት ውስጥ እንዲኖር ያደርጋል።

🙏🏼2. ከሌሎች ጋር ማወዳደር

"ለምን እንደ እገሌ ባል/ሚስት አትሆንም?" ወይም የሰዎችን ኑሮ አምጥቶ ማነጻጸር።
ጉዳቱ፦ የትዳር አጋር የዝቅተኝነት ስሜት እንዲሰማው ያደርጋል። ትዳር የሁለት ሰዎች ልዩ ጉዞ በመሆኑ የሌላውን ሰው ህይወት መመዘኛ ማድረግ ቂምን ይወልዳል።

🙏3. "ሁልጊዜ" እና "በፍጹም" የሚሉ ቃላትን መጠቀም

"ሁልጊዜ ችላ ትለኛለህ/ትይኛለሽ" ወይም "በፍጹም አትረዳኝም/አትረጂኝም"።
ጉዳቱ፦ እነዚህ ቃላት የትዳር አጋርን ጥሩ ጎን ሙሉ በሙሉ የሚክዱ እና የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማቸው በማድረግ ለመከላከል (defensiveness) የሚያነሳሱ ናቸው። በምትኩ "ይሄን ስታደርግ ቅር ይለኛል" ማለት ይመረጣል።

🙏4. ያለፈን ስህተት ደጋግሞ ማንሳት

ይቅርታ የተደረገበትን ወይም ያለፈን የድሮ ስህተት አሁን በተፈጠረ ጠብ ውስጥ መልሶ ማምጣት።

ጉዳቱ፦ ይቅርታው ከልብ እንዳልነበረ ያሳያል፤ እንዲሁም የትዳር አጋር ወደፊት እንዳይራመድ እና መተማመን እንዳይኖር ያደርጋል።

🙏5. ማንጓጠጥ፣ ንቀት እና ስድብ
መሳደብ፣ የማሰብ ችሎታን፣ ቤተሰብን ወይም አካላዊ ገጽታን ማንቋሸሽ።

ጉዳቱ፦ በራስ መተማመንን የሚጎዳ እና ጥልቅ የስነ-ልቦና ጠባሳ የሚተው ተግባር ነው። ንቀት (Contempt) ለትዳር መፍረስ ትልቁ መንስኤ እንደሆነ የስነ-ልቦና ባለሙያዎች ይናገራሉ።

🙏6. ስሜትን ማጣጣል

"ለምን ታካብዳለህ/ታካብጃለሽ?" ወይም "ይሄ እኮ ምንም የሚያስከፋ ነገር የለውም" ብሎ መገምገም።

ጉዳቱ፦ የትዳር አጋር ስሜቱ ቦታ እንደሌለውና ሀሳቡ እንደማይከበር እንዲሰማው ያደርጋል።

ጤናማ ትዳር ለመገንባት መግባባት፣ መከባበር እና ግልጽነት ወሳኝ ናቸው። አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በችግሩ ላይ እንጂ በግለሰቡ ላይ ትኩረት አለማድረግ ትልቅ ለውጥ ያመጣል።

ከእነዚህ ከተጠቀሱት ነጥቦች ውስጥ በተለይ የቱ ጉዳይ በትዳር ግንኙነት ውስጥ ትልቅ ተጽዕኖ ይፈጥራል ብለው ያስባሉ?

Bini Girmachew የስነልቦና ባለሞያ

Address

Governments
Dire Dawa

Telephone

+251715267078

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire dawa City posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dire dawa City:

Shortcuts

Share